15/06/2026
በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ደቡብ ኢትዮጵያ ሰበካ መሃል ወላይታ ቅርንጫፍ ሰበካ ላድሳ ንዑስ ሰበካ 2ኛው ዙር ወጣቶች ኮንፈረንስ በነፍሳት ትርፍ ተጠናቀቀ።
ዕለት አርብ በእግር ጉዞ በተጀመረው በዚህ ኮንፈረንስ ቅዳሜና እሁድ ሙሉ ቀን በላድሳ 01 አጥቢያ ቅጥር ግቢ ውስጥ የእግዚአብሔር ቃል በኃይል ተሰበከ።
በቅዳሜ ዕለት ዶክተር [ቄስ] ቸርነት ለቃ ለወጣቶች ይህን እውነት ወንጌል ሚስጥር በሚገባ አስተማሩ።
ለብዙዎች ይህ ወንጌል የተሰወረ ከመሆኑ የተነሳ በሰው አእምሮ ለመወሰን በተለያዩ ጉባኤ እየወሰኑ እንዳመጡ ታሪክ ይናገራል ለመሆኑ ለእኛ ግን ይህን የእውነት ወንጌል ሚስጥር ተገለጠልን ብዙዎች የእኛን መገለጥ ይጠበቃሉ እኛም መገለጥ እንዳለብን የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ወጣቶች ኃላፊ ቄስ አሸናፊ ሀመሎ:- ተኛችሁ ወይስ ነቅታችሁ ነው ያላችሁ ኢየሱስ ልመጣ ነው በሚል ርዕሰ ያስተማሩ ስሆን ፥የደቡብ ኢትዮጵያ ሰበካ ኃላፊ ቢሾፕ ብራሃኑ:- በፊትህ ስላለው ደስታ በዙሪያው ያለው ነውረኛ ንቄ ኢየሱስ ተመልከተህ ወደፊት ሩጥ በሚል ርዕሰ ወጣቶችን አስተማሩ።
በጉባኤ ከተገኙ የእግዚአብሔር ሰዎች መካከል የሶዶ እናት አጥቢያ ምክትል መጋቢት ቄስ አሉላ ኩሳም ለወጣቶች ገንቢ የሆኑ ትምርህት አስተማሩ እግዚአብሔር ለሁሉም ፀጋ ያብዛላችው።
በሌላው በኩል በዚህ ቀን በተደረገው የነፍሳት ጥሪ አጠቃላይ 39 ነፍሳት በሐዋርያት ትምህርት የተጨመሩ ስሆን 33 አድስ ነፍሳት እግዚአብሔር አንድ ነው ስሙም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በማለት አምኖ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተጠመቁ ስሆን 6 ነፍሳት በንስሐ ወደ አባታቸው ቤት ተመለሱ ክብር ምስጋና ለአንዱ ለእሥራኤል አምላክ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን።
አሜን
ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።
ማቴዎስ 24:14
ወንድማችሁ ነኝ