Areka Central Kale Hiwot Church Youth Official

Areka Central Kale Hiwot Church Youth Official የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤ በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ

 😭  :-ኑናራ ድያጌ ኡባ ጦንያጋ በሚል ድንቅ መዝሙር የሚታወቁ አባታችን የወንጌል አርበኛ ከዝህ አለም ድካም አረፉ😭😭😭የወንጌል አርበኛ ወንጌላዊ አባባ ማርቆስ ሄቫና ከዚህ ምድራዊ ህይወት ...
01/05/2026

😭
:-ኑናራ ድያጌ ኡባ ጦንያጋ በሚል ድንቅ መዝሙር የሚታወቁ አባታችን የወንጌል አርበኛ ከዝህ አለም ድካም አረፉ😭😭😭

የወንጌል አርበኛ ወንጌላዊ አባባ ማርቆስ ሄቫና ከዚህ ምድራዊ ህይወት ወዳጌለገሉት ጌታ በክብር ተጠሩ።
ወንጌላዊ አባባ ማርቆስ ሄቫና ቀደምት የወንጌል አርበኛ አባት እና ለወንጌል ብዙ ዋጋ የከፈሉ ፡ የታሰሩ ፡ እየተገረፉ እንዲሁም በመላዉ ኢትዮጵያ ወንጌል ያስፋፉ አባት ናቸዉ።
ሩጫውን በድል አጠናቅቆዋል

ልዩ የአምልኮ ግዜ እሁድ ከ8:00 ጀምሮ
30/04/2026

ልዩ የአምልኮ ግዜ እሁድ ከ8:00 ጀምሮ

29/04/2026

እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ ንስር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፥ አይታክቱም፤ ይሄዳሉ፥ አይደክሙም። ት/ኢሳ 40:31

ፍትህ ለአረካ ቁ-1 ቃ/ሕ/ቤ/ያን
25/04/2026

ፍትህ ለአረካ ቁ-1 ቃ/ሕ/ቤ/ያን

                   ++++++በመጽሐፍ ሮሜ ምዕራፍ 3:11–31 ያለው ክፍል በአጠቃላይ ሰው ሁሉ በኃጢአት እንዳለ፣ በሕግ ሥራ እንደማይዳንና በእምነት በጸጋ እንደሚዳን ይገልጻል። ...
25/04/2026


++++++

በመጽሐፍ ሮሜ ምዕራፍ 3:11–31 ያለው ክፍል በአጠቃላይ ሰው ሁሉ በኃጢአት እንዳለ፣ በሕግ ሥራ እንደማይዳንና በእምነት በጸጋ እንደሚዳን ይገልጻል። እነሆ አጭር መግለጫ፦

1. ሰው ሁሉ ኃጢአተኛ ነው (3:11–18)
“የሚፈልግ የለም፣ ጻድቅ የለም” ብሎ ይናገራል።
ሰዎች በሐሰት፣ በክፉ ነገር፣ በክፉ መንገድ ተሞልተዋል።
👉 መልእክቱ: ሰው በራሱ ጻድቅ መሆን አይችልም።

2. በሕግ ሥራ መጽደቅ አይቻልም። (3:19–20)
ሕግ ሰውን ለማዳን አይችልም፤ ኃጢአቱን ብቻ ያሳያል።
👉 መልእክቱ: በሥራ ወይም በሕግ ማንም አይጸድቅም።

3. ጽድቅ በኢየሱስ ክርስቶስ እምነት ይመጣል (3:21–26)
የእግዚአብሔር ጽድቅ ከሕግ በስተቀር ተገልጦአል።
ሰው በእምነት በክርስቶስ ይጸድቃል።
እግዚአብሔር በጸጋው እና በክርስቶስ መስዋዕት ሰዎችን ያድናል።
👉 መልእክቱ: ድነት የሚመጣው በጸጋ እና በእምነት ነው።

4. መኩራት የለም (3:27–31)
ማንም በራሱ መኩራት አይችልም።
እግዚአብሔር የሁሉ አምላክ ነው፤ አይሁድና አሕዛብ ሁሉ በእምነት ይጸድቃሉ።
እምነት ሕግን አያጠፋም፤ ይፈጽማል።
👉 መልእክቱ: ድነት ለሁሉ ነው እና መኩራት ቦታ የለውም።

✅ አጠቃላይ ዋና ሐሳብ:
ሰው ሁሉ ኃጢአተኛ ነው፤ በራሱ ሥራ መዳን አይችልም። ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ በእምነት በእግዚአብሔር ጸጋ ይጸድቃል።

ሚሺኔሪ ታምራት ቦንጋ

  ‼😭በአረካ ከተማ በቤተክርስቲያን ይዞታ ዙሪያ እየተከሰተ ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ የቀረበው አቤቱታ በግልጽ እና በዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦ጉዳዩ፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የታሰሩ የቤተክር...
18/04/2026

‼😭

በአረካ ከተማ በቤተክርስቲያን ይዞታ ዙሪያ እየተከሰተ ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ የቀረበው አቤቱታ በግልጽ እና በዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ጉዳዩ፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የታሰሩ የቤተክርስቲያን መሪዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እና ለይዞታ ጥያቄው ተገቢው ምላሽ እንዲሰጥ ስለመጠየቅ

ቤተክርስቲያኒቱ ካላት ነባር ይዞታ ጋር በተያያዘ፣ ከዞኑ መንግሥት በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ጉዳዩ በውይይት እንዲፈታ እስከ ላይኛው የመንግሥት መዋቅር ድረስ የመብት ጥያቄዋን በሰላማዊ መንገድ እያቀረበች ትገኛለች።

ይሁን እንጂ፣ ይህ ሕጋዊ ሂደት እየተከናወነ ባለበት ሁኔታ፣ የከተማው አስተዳደር ዛሬ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም (እንደ ወቅቱ አቆጣጠር) ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የቤተክርስቲያኒቱን መሪዎች ያለምንም ጥያቄና በግፍ በአረካ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አስሮ አቆይቷቸዋል።

ይህ በቤተክርስቲያን መሪዎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ኢ-ፍትሐዊ እስር በአስቸኳይ እንዲቆም፣ የታሰሩትም እንዲፈቱ እና ለቀረበው የይዞታ ጥያቄ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ፈጣንና ፍትሐዊ ምላሽ እንዲሰጥ አጥብቀን እንጠይቃለን።

🙏

ልዩ የስኔ-ጹሁፍ እና አምልኮ ግዜ በአረካ መሐል ከተማ ቃ/ሕ/ቤ/ያን በቀን 7/08/2018 ዕሮብ ከ9:00 ጀምሮሁላችሁም ተጋብዛችኋል ...share it
14/04/2026

ልዩ የስኔ-ጹሁፍ እና አምልኮ ግዜ በአረካ መሐል ከተማ ቃ/ሕ/ቤ/ያን በቀን 7/08/2018 ዕሮብ ከ9:00 ጀምሮ
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ...share it

11/04/2026
 ?‎‎1. በሥነ-መለኮታዊ እውነታ አንጻር (Theological Truths)‎‎👉 የቃሉ ሁለንተናዊነት፦ እግዚአብሔር ቃሉን ለአይሁድ የሰጠው እንደ "አደራ ጠባቂ" እንጂ እንደ "ባለቤት" አይደ...
08/04/2026

?

‎1. በሥነ-መለኮታዊ እውነታ አንጻር (Theological Truths)

‎👉 የቃሉ ሁለንተናዊነት፦ እግዚአብሔር ቃሉን ለአይሁድ የሰጠው እንደ "አደራ ጠባቂ" እንጂ እንደ "ባለቤት" አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠ የእግዚአብሔር ራስ-መገለጥ (Self-Revelation) ነው።

‎የልጅነት ሥልጣን፦ አማኝ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ የመሆን "ሥልጣን" አለው (ዮሐ 1:12)። ልጅ የአባቱን ቃል "የእኔ ነው" የማለትና ለቃሉ ክብር የመቆርቆር መብት አለው።

‎2. በቤተ ክርስቲያን ታሪክ አንጻር (Church History)

‎👉 የመስዋዕትነት ታሪክ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ዛሬ በእጃችን የገባው በብዙ አባቶችና ሰማዕታት መስዋዕትነት ነው። በታሪክ መጽሐፍ ቅዱስን የወሰዱ ወይም ያቃለሉ ወገኖች ላይ ቤተ ክርስቲያን የጸና ተቃውሞ ስታደርግ ኖራለች።

‎የኢትዮጵያ ክርስትና፦ ኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስን ከተቀበሉ ቀዳሚ አገራት አንዷ ስትሆን፣ ቃሉን በቋንቋዋ በመተርጎም የራሷ "ርስት" አድርጋዋለች። ይህንን ታሪካዊ ባለቤትነት መካድ የሀገሪቱን መንፈሳዊ ቅርስ መካድ ነው።

‎3. በዕቅበተ እምነት አንጻር (Apologetics)

‎👉 የቃሉን ቅዱስነት መከላከል፦ ዕቅበተ እምነት ቃሉን ከስህተት ትምህርት ብቻ ሳይሆን ከማናቸውም ንቀትና ቅሌት መከላከልን ይጨምራል። መጽሐፍ ቅዱስ ሲቀደድ "የእኔ አይደለም" ብሎ ማለፍ፣ እምነትን ለመናቅ ለሚፈልጉ ወገኖች መንገድ መክፈት ነው።

‎4. በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት አንጻር (EKHC Doctrine)

‎👉 የቃሉ የበላይነት፦ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን "የእምነትና የተግባር ብቸኛ መመሪያ" አድርጋ ትቀበላለች። ቤተ ክርስቲያኒቱ ለቃሉ ክብር የምትቆም እንጂ ቃሉ ሲዋረድ ምእመናንን "ዝም በሉ" የምትል አስተምህሮ የላትም።

‎ #የአገልጋይነት ተጠያቂነት፦ አገልጋዮች የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተምህሮ የመጠበቅና ምእመናንን በቃሉ የማነጽ ግዴታ አለባቸው።

‎5. ከአገልጋይነት ደረጃና ኃላፊነት አንጻር (Ministry Responsibility)

‎👉 መንጋውን የመጠበቅ ግዴታ፦ አንድ "መጋቢ"
‎አርአያነት፦ አገልጋይ ለቃሉ ቅዱስነትና ክብር ግንባር ቀደም ተቆርቋሪ መሆን አለበት።

‎6. ክርስቲያኖች ለቃሉ ካላቸው ባለአደራነት አንጻር (Stewardship)

‎👉 የቃሉ ጠባቂነት፦ ክርስቲያኖች ቃሉን እንዲጠብቁ፣ እንዲያከብሩና እንዲያስከብሩ አደራ ተሰጥቷቸዋል። መጽሐፍ ቅዱስ ሲቃለል የሕግና የሞራል ክርክር ማድረግ "ትምክህት" ሳይሆን "ታማኝነት" ነው።

‎7. የመጽሐፍ ቅዱስ "ባለቤትነት" vs "ምንጭነት" (Origin vs. Ownership)

‎እውነታው፦ መጽሐፍ ቅዱስ በታሪክ የመጣው በአይሁድ በኩል ቢሆንም፣ ልክ ፀሐይ ከምሥራቅ እንደምትወጣና ብርሃኗ ግን ለዓለም ሁሉ እንደሆነ ሁሉ፣ መጽሐፍ ቅዱስም የመጣው ከአይሁድ ቢሆንም ብርሃኑና ባለቤትነቱ ግን የዓለም ሁሉ አማኝ ነው።
‎8. የሕግ እና የዜግነት መብት (Legal and Civil Rights)

‎እውነታው፦ መጽሐፍ ቅዱስ ሲቀደድ "የመብት ጥያቄ ሊቀርብ አይችልም" ማለት፣ በሀገሪቱ ሕግ የተቀመጠውን "የእምነት ተቋማትና ቁሳቁሶች የመከበር መብትን" መናቅ ነው።

‎ዲ/ን ስንታየሁ ንጋቱ

 _ህጎች 🏠🔥❤‎‎ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ቅዱስ ስፍራ ነው፣ በቤቱ ስርአትና አክብሮት ሊኖር ይገባል!‎‎1. ፕሮግራም አታርፍድ ⏰ እግዚአብሔር ለቀጠሮው አይዘገይም፤ አንተስ ለምን ታረፍዳ...
05/04/2026


_ህጎች 🏠🔥❤

‎ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ቅዱስ ስፍራ ነው፣ በቤቱ ስርአትና አክብሮት ሊኖር ይገባል!

‎1. ፕሮግራም አታርፍድ ⏰ እግዚአብሔር ለቀጠሮው አይዘገይም፤ አንተስ ለምን ታረፍዳለህ? በጊዜ መገኘት በረከትን ቀድሞ መቋደስ ነው። 📖 "ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ" (መዝሙር 122:1)

‎2. ድምፅህን ጠብቅ፤ አታውራ 🗣️ በአምልኮና በትምህርት ሰዓት ወሬና ጨዋታ ለእግዚአብሔር ቤት አይመጥንም። ስፍራው የዝምታና የጸሎት ነው። 📖 "ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌሶን 4:29)

‎3. ስልክህን እረፍት ስጠው 📱 በስብከት ወቅት ሶሻል ሚዲያ መጠቀምና ስልክ መነካካት መንፈሳዊ ትኩረትን ይሰርቃል። ስልክህ ሲደወልም አንስተህ አታውራ፤ ቅዱሱን ድባብ አታናጋ። 📖 "በላይ ያለውን አስቡ" (ቆላስይስ 3:2)

‎4. አለባበስህ ስርአት ይኑረው 👗 ሰውነትን ገልጦ የሚያሳይና ሌሎችን ለፈተና የሚዳርግ አለባበስ ከቤተክርስቲያን ቅድስና ጋር አይሄድም። ይህ ወንዶችንም ይመለከታል።

‎📖 "ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን" (1 ቆሮንቶስ 14:40)

‎5. አትተኛ፤ ንቃ! 😴 ቤተክርስቲያን የመንፈስ መታደሻ እንጂ መኝታ ቤት አይደለችም። ንቁ ሆነህ ቃሉን ተከታተል። 📖 "አንተ የምትተኛ ንቃ..." (ኤፌሶን 5:14)

‎6. ተመልካች ብቻ አትሁን፤ በመንፈስ ተሳተፍ 👀🔥 ሌሎች ሲያመልኩና በረከት ሲቀበሉ አንተ ዝም ብለህ አትመልከት። ዘምር፣ አምልክ፣ ስገድ፤ በመንፈስና በእውነት ከፈጣሪህ ጋር ተገናኝ። 📖 "እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል።" (ዮሐንስ 4:24)

‎7. ቂም ይዘህ አትቆም ቂም ይዘህ አትጸልይ! ልብህ በቂምና በነገር ተሞልቶ አምልኮ የለም። አስቀድመህ ለበደሉህ ይቅርታ አድርግ፤ በንጹህ ልብም ፊትህ ቁም። 📖 "አስቀድመህ ከወንድምህ ጋር ታረቅ" (ማቴዎስ 5:24)

‎8. ተስፋ ሰንቀህ ቅረብ ከእግዚአብሔር እጅ አንድ ነገር እንደምትቀበል አምነህ ሂድ። የምትጠብቀው ነገር ከሌለ የምታገኘውም አይኖርም። 📖 "አፍህን በሰፊው ክፈት እኔም እሞላዋለሁ" (መዝሙር 81:10)

‎9. አገልጋዮችን አታቅልል 🙅‍♂️
‎ከአገልጋዮች ጋር ባለህ መቀራረብ የተነሳ ቅጥ የሌለው ድፍረት አታሳይ። የእግዚአብሔርን ቅቡዓን ማክበር ለራስህ ስኬት መቆለፊያ ነው። 📖 "የቀባሁትን አትንካ" (መዝሙር 105:15)

‎10. ለዲያቆናትና ለአገልጋዮች ታዘዝ 🙏 ዲያቆናት የሚተጉት ስርአትን ለማስጠበቅና አንተን ለማገልገል ነው። ትህትናንና ትብብርን አሳያቸው። 📖 "ሁሉን አክብሩ፥ ወንድሞችን ውደዱ..." (1ኛ ጴጥሮስ 2:17)

‎11. ፕሮግራም ሳያልቅ አትውጣ በጸሎትና በስብከት መሃል ጥሎ መውጣት ስርአተ አልበኝነትና ሌላውን መረበሽ ነው። እስከ መጨረሻው ታግሰህ በረከቱን ይዘህ ውጣ።

‎📖 "ወደ እግዚአብሔር ቤት በገባህ ጊዜ እግርህን ጠብቅ" (መክብብ 5:1)

‎ #ተመስገን🙏 #ተባረኩ
‎ለሌሎች እንድደርስ like share ያድርጉ !!

ልዩ የአምልኮ ግዜዕሮብ 11:30
12/01/2026

ልዩ የአምልኮ ግዜ
ዕሮብ 11:30

06/01/2026

እንኳን ለ2018 ዓ.ም ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

" ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።" ሉቃ 2:11

እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ከላይ ከአሪያም ክብሩን ትቶ ፍጹም ሰው ሆኖ ወደ ምድር የመጣው እና ውርደታችንን የተዋረደበት ዋናው ዓላማ የእኛ በምቾት እንድንኖር ወይም ታዋቂ እንድንሆን አልነበረም፤ በስሙ የንግድ አብዮት አቀጣጥለን በአጭሩ ወደ ዲታነት የምንከረበትበት የብልጣብልጥነት ንግድ እንድናጧጥፍም አይደለምም፤ አልነበረምም።
ይልቁን የመጣዉማ ከብዙ ዘመናት በፊት በኤድን ገነት ባለማስተዋል በሰይጣን አታላይነት ያጣነውን ሁለንተናዊነታችንን “. . . ሕይወት ኢንዲሆንላችሁና እንዲበዛላችሁ መጣሁ . . . ” እያለ የጠፋነውን እኛን የሰው ልጆች በሰባራ ልባችን እያነከስን ከገባንበት ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከዘላለም መንፈሳዊ ሞት ወደ ዘላለም ሕይወት የመቀላቀል ሁለንተናዊነታችንን የመመለስ ዘላለማዊ የማዳን ተልዕኮ ነበር።
ይሁን እንጂ ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ ሁልጊዜም የቅዱሳን ደመኛ ጠላት የሆነው ዲያብሎስ በተለይ በዘመናችን እንደ አሸን በፈሉ እውነት መሰል ሻካራ የሞት መንገድ ለገዛ ተድላቸው የተገዙ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች በሰበኩት ቆልማማ የመጽሐፍ ቅዱስ ተቃራኒ የሆነ የፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ ትምህርት የድጥ ጉዞ መጨረሻው ውድቀት መሆኑን ባለመገንዘብ በርካታ ምዕመናን ስተው በሚያስቱ ራሳቸውን በራሳቸው በሾሙ አገልጋይ ነን ባዮች የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና አገልጋዮች ከሚያስተምሩት እውነት ይልቅ እነኚህን በመስማት ተሰናክለው የወደቁ እስከ ትዳር መፍረስ እና አልፎ ተርፎም በሐኪም የታዘዘን መድሃኒት አቁሙ ተብለው ሕይወታቸውን እስከማጣት የደረሱ በርካቶች ስለመሆናቸው ምስክር አያሻም።
ስለዚህም እኛ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና አገልጋዮች “ከየት እንደመጣ የማያውቅ ትውልድ የት እንደሚሄድም አያውቅም።” እንደሚባል ወጣቱ ትውልድ ትናንት አባቶቻችን ያለፉበትን እውነተኛ የክርስትና መንገድ እና የሚያስከፍለውንም ዋጋ በሚገባ ባለማወቅ ለብልጭልጭ ነገርና ባዶ ሆይሆይታ በቀላሉ ልቡ እንዳይሳብ በጋራ የጀመርነው የተሃድሶ ጉዞ ፍሬ እንዲያፈራ የክርስትና መንገድ የስሜት ዝላይ ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱሳዊ የብስለት ሕይወት መንገድ መሆኑን ያለመሰላቸትና መታከት በሚገባ በማስተማር ቤተ ክርስቲያንን መታደግ ይጠበቅብናል።
በተጨማሪም በምንኖርበት ዓለም በክርስትና ጉዞ አለመግባባት ድንቅና ተዓምራታዊ ክስተት ሳይሆን ያለ፣ የነበረና የሚኖር ሆኖ ሳለ በቀና ልቦና ይቅር ለእግዚአብሔር ከመባባል ይልቅ አንደበቱን ሳይገታ ልቡን ለሚያስት የማህበራዊ ሚዲያ ሞገደኛ አወቅሁ ባይ በአሕዛብ መንገድ የቤተ ክርስቲያንን ገበና ማስጣት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እንደሚያመዝን ካለፈው በመማር በሰከነ መንፈስ ሐዋሪያው ጳውሎስ እንደመከረን የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ በቤተ ክርስቲያን መጨረስ በረከት ነው።
በዚህ ዓመት ባሳለፍናቸው ጥቂት ወራት ነገ ድርግም ብለው ሊጠፉ ባሉ ተራ ሆይሆይታና ዳንኪራ እንዲሁም ጥቂት አለመግባባትን መሰረት አድርገው ምዕመናንን ለመረበሽ ሰይጣን የሚያስነሳቸውን ተራ ጉዳዮች ከመሰረቱ በመገንዘብ ድንጋይ ከመወራወርና ጣት ከመቀሳሰር ይልቅ በአንድ ልብ እንደ አንድ ቤተሰብ እየተደማመጥን ቅዱስ ቃሉንና ስርዓቷን የጠበቀች ንጽሕት ቤተ ክርስቲያንን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ የጀመርነውን በይሉኝታ ያልተሸበበ የተሃድሶ ጉዞ በጋራ እጅ ለእጅ ተያይዘን ተግባራዊ ማድረጉን እንድንቀጥል በጌታ ፍቅር አሳስባለሁ።
በመጨረሻም ከሰማይ ሰማያት ክብሩን ጥሎ መጥቶ በከብቶች በረት የተወለደውን መድሃኒታችንን ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እየተመለከትን የተሰጠንን አገልግሎት ክብራችንንና ማንነታችን ለጌታ ጥለን ዝቅ ብለን በትህትና እንድናፈገለግል እግዚአብሔር ጸጋውን እንዲያበዛልን በትጋት እንድንጸልይ ጥሪዬን እያስተላለፍኩ በዓሉ እግዚአብሔር የሚከብርብትን እያደረግን ድሆንችን እየመገብን በጋራ ሃሴት የምናደርግበት የተከፈለልንን የመዳን መንገድ ዋጋ እያሰብን በደስታ የምናሳልፍበት የሰላም በዓል እንዲሆንልን አያሳሰብኩ በድጋሚ እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ አመሰግናለሁ።

የጌታችንና የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔር አብ ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን።
ወንጌል ለወላይታ ወላይታም ለወንጌል!

መጋቢ አብርሃም ቦታ
የወላይታ ቀጣና ዋና ፀሐፊ

Address

Areka

Telephone

+251908279351

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Areka Central Kale Hiwot Church Youth Official posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Areka Central Kale Hiwot Church Youth Official:

Share