Apostolic church of Areka

Apostolic church of Areka Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Apostolic church of Areka, Religious organisation, Areka.

ማርቆስ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁹ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ ከትእዛዛቱ ሁሉ ፊተኛይቱ፦ እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፥
³⁰ አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት

ጥያቄ ለሥላሴ አማኞች እሁድ ቤተክርስቲያን ሄዳችሁ ስታመሰግኑ ለየትኛው እግዚአብሔር ነው የምታቀርቡት? ለእግዚአብሔር አብ፣ ለእግዚአብሔር ወልድ ወይስ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ? ከ 3ቱ ለ...
24/05/2026

ጥያቄ ለሥላሴ አማኞች እሁድ ቤተክርስቲያን ሄዳችሁ ስታመሰግኑ ለየትኛው እግዚአብሔር ነው የምታቀርቡት? ለእግዚአብሔር አብ፣ ለእግዚአብሔር ወልድ ወይስ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ? ከ 3ቱ ለአንደኛው ካላችሁ የቀሩት 2ቱ አይቀየምባችሁም?? እንዴት ነው የምታደርጉት እስቲ ንገሩኝ..!

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

23/05/2026

ሥላሴ አሁንም ወደፊት 1+1+1=3 or 1???
ንገሩኝ እስቲ.

ኢየሱስ ያድናል! ከተባለ ማዳን የሚችል አንድ አምላክ ብቻ ነው ። ኢሳ 43፥11 እኔ፥ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔ ሌላም የሚያድን የለም። ኢየሱስ አብ ካልሆነ ማዳን አይችልም። ከታች ያለው...
23/05/2026

ኢየሱስ ያድናል! ከተባለ ማዳን የሚችል አንድ አምላክ ብቻ ነው ።

ኢሳ 43፥11 እኔ፥ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔ ሌላም የሚያድን የለም።

ኢየሱስ አብ ካልሆነ ማዳን አይችልም።


ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

 ። ? እንግዲህ፦  ? አሉት። ኢየሱስ መልሶ፦ እኔንም ወይም አባቴንም አታውቁም፤ እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር አላቸው።  ዮሐንስ 8፥19✔️ግልፅ ጥያቄ  "የኢየሱስ አባት ...
22/05/2026


?

እንግዲህ፦ ? አሉት። ኢየሱስ መልሶ፦ እኔንም ወይም አባቴንም አታውቁም፤ እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር አላቸው። ዮሐንስ 8፥19

✔️ግልፅ ጥያቄ "የኢየሱስ አባት ዬት ነው?" የሚለው ነው። ቀጥለን የኢየሱስን ቀጥተኛ መልስ እንይ፣ በትኩረት!!

የኢየሱስ መልስ፦ እኔንም አባቴንም አታውቁም፣ እኔን ብታውቁኝ አባቴንም ታውቁ ነበር አላቸው። ግን እንዴት?

ኢየሱስን ቢያውቁት ብረዱት አብ ግልጽ ነው፣ አብ በኢየሱስ በሙላት ተገልጦ ስለሚኖር።

#እንቀጥል፦ ዮሐ 8:20

²⁰ ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር በግምጃ ቤት አጠገብ ይህን ነገር ተናገረ፤ ጊዜው ገና አልደረሰምና ማንም አልያዘውም።

✔️ ይህ ቁጥር 20 ላይ ያለው ከጥያቄው ጋር አይገናኝም፣ ኢየሱስ ዬት ሆኖ እያስተማረ እንዳለ የሚገልጽልን ነውና፣ እስካሁን ኢየሱስ ጥያቄን የአብ አድራሻ አልጠቆመላቸውም። አብ ወዴት ነው? ለሚለው።

²¹ ኢየሱስም ደግሞ፦ እኔ እሄዳለሁ ትፈልጉኛላችሁም በኃጢአታችሁም ትሞታላችሁ እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም አላቸው።

✔️እዚህ ከጥያቄአቸው አንጻር " " የሚለውን ከባዱን ቃል ተናገረባቸው። ሆኖም አሁንም ጥያቄአቸው "አብ ወዴት ነው? የሚለው አብ ማን እንደሆነ አልጠቆመላቸውም።

#እንቀጥል፦ “አይሁድም፦ እኔ ወደ ምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም ማለቱ ራሱን ይገድላልን? እንጃ አሉ።”
ዮሐ 8፥22

✔️ #22 ላይም፣ ለጢያቄያቸው መልስ በቀጥታ አልተመለሰም፣ እርስ በርሳቸው እየተጠያየቁ ተነጋገሩ እንጅ ጥያቄያቸው አሁንም " ? የሚለው ነው።

#እንቀጥል፦ “እናንተ ከታች ናችሁ፥ እኔ ከላይ ነኝ፤ እናንተ ከዚህ ዓለም ናችሁ፥ እኔ ከዚህ ዓለም አይደለሁም።”
ዮሐ 8፥23

✔️አሁንም ? ለሚለው ጥያቄ ይህ ቀጥተኛ መልስ ሳይሆን መንደርደሪያ የሚሆን የኢየሱስ ማንነት ነው።

✔️እርሱ ከላይ ነው፣ እርሱ ከዚህ አለም አይደለም። ስለዚህ ጥያቄያቸውን አሁንም በቀጥታ አልተመለሰም። ጥያቄው " ?" የማለው ነው።

#እንቀጥል፦ “እንግዲህ፦ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ አልኋችሁ፤ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁና አላቸው።”
ዮሐ 8፥24

✔️እዚህ ግን መልስ ተገኝቷል።

ጥያቄ፦ ነው? ለሚለው

መልሱ፦ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ የሚለው ሆነ።

በቁጥር 19 ለጠየቁት ጥያቄ መልስ ሳይሰጥ፣ ነገር ግን ለመልሱ መንደርደሪያ የሆኑ ማብራሪያዎችን እየሰጠ በቁጥር 24 ላይ ብሎ ኢየሱስ ራሱ አብ መሆኑን አስረድቷቸዋል።

ይህን ክፍል በእንግሊዝኛው እንየው።

“I said therefore unto you, that ye shall die in your sins: for if ye believe not that , ye shall die in your sins.”
John 8:24 (KJV)

ምን ማለት ነው? " (አብ) እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ ነው። ስለዚህ ኢየሱስ አብ ነው።

#እንቀጥል፦ “እንግዲህ፦ ነህ? አሉት። ኢየሱስም፦ ነኝ። ዮሐ 8፥25

ኢየሱስ ማን ነው? ከመጀመሪያው ከጥንት(From Beginning) የተናገረው ራሱ ኢየሱስ ነው። ስለዚህ የጥንቱ የመጀመሪያው አምላክ እንጅ ሌላ እግዚአብሔር ተወልዶ የመጣ አይደለም።


ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

21/05/2026

“እግዚአብሔርም በምድር ሁሉ ላይ ይነግሣል፤ በዚያ ቀን እግዚአብሔር አንድ፥ ስሙም አንድ ይሆናል።”
— ዘካርያስ 14፥9

ጥያቄ ለሥላሴ አማኞች የዛኔ የምነግሠው ከ 3ቱ ማነው?

✅ወደ አብርሃም ቤት የመጡት :  #መላእክት ናቸው ወይስ  #እግዚአብሔሮች ናቸው??👉ዘፍ18:…ላይ አብርሃም አይኑን አንስቶ ያያቸው  #ሶስት  #ሰዎችን ነው እንጅ ሶስት እግዚአብሔርን አይደለ...
20/05/2026

✅ወደ አብርሃም ቤት የመጡት : #መላእክት ናቸው ወይስ #እግዚአብሔሮች ናቸው??

👉ዘፍ18:…ላይ አብርሃም አይኑን አንስቶ ያያቸው #ሶስት #ሰዎችን ነው እንጅ ሶስት እግዚአብሔርን አይደለም ::
⭕መላእክት ሰዎች ተብለው ልጠሩ ይችላሉ :: ለምሳሌ:-ዘፍ 19:…ላይ ወደ ሎጥ ቤት የመጡት ሰዎች ተብሎዋሉ : ስለዚህ ወደ አብርሃም ቤት የመጡት ሰዎች ተብለው የተጠሩ #መላእክት ናቸው ::

⛔ወደ አብርሃም ቤት ከመጡ ከሶስቱ አንደኛው ሰው(መልአክ ) : በእግዚአብሔር ስም የመጣ ነው ::ይህ ማለት መልአኩ እግዚአብሔር ነው ማለት ሳይሆን በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ መልአክ እንዳለ ይገልፃል::👉ዘጸ 3:…ላይ ለሙሴ በእሳት ነበልባል የታየው #መልአክ ነው : ከእሳት ነበልባል ዉስጥ የተናገረው ግን #እግዚአብሔር ነው : ስለዚህ እዚህ ቦታ : የእግዚአብሔር መልአክ በእግዚአብሔር ስም እንደመጣ ያሳያል ::
👉 #በእግዚአብሔር ስም የሚገለጥ #መልአክ እንዳለ ✅ዘፃ23:20-21 ያስተምራል::

🧲ስለዚህ ወደ አብርሃም ቤት የመጡት ሶስት መላክቶች ናቸው : ከሶስቱ አንዱ በእግዚአብሔር ስም የተገለጠ ነው :: ከዛ ሁለቱ ወደ ሰዶም ወደ ሎጥ ቤት ሲሄዱ(ዘፍ18:16 ዘፍ18:22) አንዱ በእግዚአብሔር ስም የመጣው ደግሞ ከአብርሃም ጋር ነበረ (ዘፍ18:22)::

⭕አብርሃም ቤት የመጡት መላእክቶች ስለመሆናቸው ማረጋገጫ :-

1) እግዚአብሔርን ያየ ማንም የለም (ዮሐ1:18) ስለዚህ አብርሃም ያያቸው መላእክትን ነው : ምክንያቱም እግዚአብሔርን ያየ ማንም(አንድም ) የለምና ደግሞ ሶስቱን ሰዎች አብርሃም አይቷል::
2) አብርሃም የተቀበላቸው መላእክትን ነው (ዕብ13:1-2)
3)ከአብርሃም ቤት ተነስተው ዘፍ19…ላይ ወደ ሎጥ ቤት የሄዱት መላእክት ናቸው ::
4) መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውም (ሉቃስ24:39) ስለዚህ በአካል ሶስተኛ ሆኖ ሊመጣ አይችልም : ምክንያቱም አይታይም: ስለዚህ ወደ አብርሃም ቤት ከመጡት ሶስተኛዉ መንፈስ ቅዱስ አይደለም::
5)በብሉይ ኪዳን ክርስቶስ አልተወለደም : ስለዚህ ክርስቶስ ከመወለዱ በፊት ወደ ምድር በአካል አልመጣም : ስለዚህ ወደ አብርሃም ቤት ከመጡት ሶስተኛዉ ክርስቶስ አይደለም::
⭕እነዚያ ሰዎች ከአብርሃም ቤት ወጥተው ሰዶም ሄደው መላእክት ተባሉ : ሰዎችም ተባሉ::


ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

19/05/2026
19/05/2026

ኢየሱስ ጌታ ነው።
ስንተኛ ጌታ ነው ሥላሴ አማኞች?

18/05/2026

ይደመጥ

ተጠናቀቀ ፥ ለቀጣዩ በሰላም ያደረሰን።በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ስዳማ ሰበካ በሃዋሳ ሚሊኒየም አደባባይ ከ ዕለት ሐሙስ 06_09/09/2018  ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፈረንስ ተካሄደ።ኮ...
18/05/2026

ተጠናቀቀ ፥ ለቀጣዩ በሰላም ያደረሰን።

በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ስዳማ ሰበካ በሃዋሳ ሚሊኒየም አደባባይ ከ ዕለት ሐሙስ 06_09/09/2018 ታላቅ መንፈሳዊ ኮንፈረንስ ተካሄደ።

ኮንፈረንሱ በዛሬው ዕለት ግንቦት 9/2018 ዓ.ም የተጠናቀቀ ስሆን በአጠቃላይ በነበረው ቀናት ውስጥ #575 ሰዎች በሐዋርያት ትምህርት ተጨመሩ።
ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የእሥራኤልም ንጉሥም ነው ። አሜን
በሰማይ በምድርም አንድ ንጉሥ አለን።
ግንቦት /9/ 2018ዓ.ም

ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

ኢየሱስ አብ ነው ቢለን እንደምንሰብክ ያህልም  ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅም ነው ቢለን እንሰብካለን።በመጽሐፍ ቅዱስ አባባልም ሆነ በሐዋርያት እምነት  ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነ...
17/05/2026

ኢየሱስ አብ ነው ቢለን እንደምንሰብክ ያህልም ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅም ነው ቢለን እንሰብካለን።

በመጽሐፍ ቅዱስ አባባልም ሆነ በሐዋርያት እምነት ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው በማለት ማመን እግዚአብሔርን ከአንድ በላይ አያደርግም።

በሰዎች ትምህርት ግን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ማለቱ ሌላ አባት በአካል አለ በማለት ይታመናል።

በእግዚአብሔር ቃል ከሆነ ግን ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ማለቱ የአምላክ መታያ, አማኑኤል መሆኑን ያ የማይታይ እግዚአብሔር በሚታየው ሰውነት ከእኛ ጋር መሆኑን ይናገራል።

በሐዋርያት እምነት ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ተብሎ ሌላ አምላክ ወይም አባት መፈለግ አይቻልም ያ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ የተባለው የዘለዓለም አባት, ኃያል አምላክ ነው ተብሎ ይታመናል።

ይህን የተረዱ ሐዋርያት ወንጌል ስለ ልጁ ነው በማለት ተናገሩ
እኛም ይህን ስለተረዳን ወንጌል ሰለ እርሱ ሀሉ በሁሉ የሆነው ስለ ልጁ ነው እንላለን።

ወንጌሉ ደግሞ ያ ሰዎች የሰቀሉ ያ ሰዎች የቀበሩት ስለ እኛ በሥጋው ሰውነት በመስቀል የተሰቀለው እርሱ ኢየሱስ የእሥራኤል አምላክ አንዱ መሆኑን ለዓለም ማወጅ ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ ወልድ ብቻ ነው ከተባለ ይህ ወንጌል አይደለም ይህን ሁሉ ሰው ያውቃል ሐዋርያ ጳውሎስ ለወንጌል የተከደነ፥ በሰውኛ ቋንቋ የማይታይ ነገር እንዳለ ነገር ግን በመንፈሳዊ ዓይን የሚታይ ነገር ስላለ እንዲህ አለ:-

👉 ወንጌላችን የተከደነ ቢሆን እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉ ነው። ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ። ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታ እንደ ሆነ እንጂ ራሳችንን አንሰብክምና፥ ስለ ኢየሱስም ራሳችንን ለእናንተ ባሪያዎች እናደርጋለን። [2ኛ ቆሮንቶስ 4:3_5]

ሰው ሁሉን ለማዳን በመስቀሉ የራሱን ፍቅር ያሳየው ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬም በደሙ ይጠራቸዋል ኑ ልጆቼ እያለ ነው።
አሜን

ወንድማችሁ ነኝ
ከታች ያለውን የ Telegram channel join አድርጉ በየቀኑ single መዝሙሮች በኮንፈረንስ የተሰበኩ ስብከቶች እና የፅሁፍ ትምህርት ይለቀቃል
join አድርጉ
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka
👉https://t.me/ApostolicchurchofAreka

Address

Areka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Apostolic church of Areka posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share