Areka No.1 kale hiwot church youth officially

Areka No.1 kale hiwot church youth officially ወልድ ያለው ሕይወት አለው

በሰሞኑ በቤተክርስቲያን ይዞታ ጋር በተያያዘ ከከተማው መንግሥት ጋር በነበረው አለመግባባት በዋናነት የዞኑ መንግሥት ጉዳዩን ወደ መድረክ በማምጣት በማወያየት የነበረውን አለመግባባት በሠላማዊ ...
27/04/2026

በሰሞኑ በቤተክርስቲያን ይዞታ ጋር በተያያዘ ከከተማው መንግሥት ጋር በነበረው አለመግባባት በዋናነት የዞኑ መንግሥት ጉዳዩን ወደ መድረክ በማምጣት በማወያየት የነበረውን አለመግባባት በሠላማዊ መንገድ በእርቅ ሠላም መጭረሱን እና የክስ ሁኔታና እገዳ መነሳቱን እየገለጽን የዞኑን መንግሥት እያመሰገንን በግልም ይሁን በቤተክርስቲያን ደረጃ በፀሎትም በሐሳብም እንዲሁም በተለያዩ ሚዲያ ድምፅ የሆናችሁ፥ አለኝታነታችሁን ያሳያችሁ በሙሉ ቤተክርስቲያኒቱ ታመሰግናለች።
ቀጥሎ ያለውን ህደት በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል።

የእውነት ምስክርነት ከብዙ በጥቅቱ፦ ስለ አረካ ቁጥር 1 ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ ፋይዳቤተ ክርስቲያኒቱ ለከተማውና ለሕዝቧ ያበረከተችውን ታላቅ አስተዋጽኦ በተደጋጋሚ ስንዘግብ ቆ...
26/04/2026

የእውነት ምስክርነት ከብዙ በጥቅቱ፦ ስለ አረካ ቁጥር 1 ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ማኅበራዊ ፋይዳ
ቤተ ክርስቲያኒቱ ለከተማውና ለሕዝቧ ያበረከተችውን ታላቅ አስተዋጽኦ በተደጋጋሚ ስንዘግብ ቆይተናል። ይህን የምናደርገው እውነታውን እያወቁ የተኙትን ለማሳሰብ፣ ላላወቁት መረጃ ለመጠቆም፣ እንዲሁም ጉዳዩን ካላስተዋሉት ጋር ለማጋራት ነው። የከተማው መስተዳድር በዚህች ቤተ ክርስቲያን የሥራ ውጤት ምክንያት በዞንና በክልል ደረጃ በተደጋጋሚ ተሸላሚ ሲሆን ቆይቷል። ይህንንም በማስረጃ አስደግፈን በሚከተሉት ስድስት ዋና ዋና ክፍሎች አቅርበነዋል፤ ፍርዱን ደግሞ ለእናንተ ለቅን ልቦናችሁ እንተዋለን።
ይህች ቤተ ክርስቲያን ልትደነቅና ልትሸለም ይገባታል እንጂ፣ አንዳንድ በክፋት የተነሳሱ ሰዎች አማካኝነት ስም የማጥፋት ዘመቻ ሊከፈትባት አይገባም ነበር።
1. በትምህርት ዘርፍ፦
በትምህርት ዘርፍ በክልል ደረጃ አንደኛ መውጣታችን የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። በተጨማሪም፣ በከተማው ከሚገኙ የመንግሥትም ሆኑ የግል ትምህርት ቤቶች በተለየ መልኩ፣ ለማኅበረሰቡ ያለምንም የሃይማኖት፣ የጾታና የዘር ልዩነት ሳይኖር ከ10 ዓመታት በላይ ነፃ የክረምት ትምህርት አገልግሎት ስንሰጥ ቆይተናል። ስለዚህ ትምህርት ቤቱ በክልል ደረጃ መሸለም የቤተክርስቲያኒቱ ብርቱ የሆነ ጥረትና ትግል ውጤት መሆኑ የገሃድ ምስጥር ነው።
2. በበጎ አድራጎት ዘርፍ፦
ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት በመገንባትና በመጠገን ረገድ ለተከታታይ 10 ዓመታት አገልግለናል። እንደዚሁም አሁንም ብዙ አቅሜ ደካሞችን በልዩነት እየደገፍን እንገኛለን። በየዓመቱ መስከረም 1 ቀን በቤተ ክርስቲያኒቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚካሄደው "የማዕድ ማጋራት" መርሐ ግብር ሳይቋረጥ ቀጥሏል። ከዚህም ባሻገር ለከተማዋ ወጣቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የድርሻችንን ተወጥተናል።
3. በጤና ዘርፍ፦
ከኢትዮጵያ ደም ባንክ ወላይታ ዲስትሪክት ጋር በመተባበር፣ በከተማዋ ታሪክ ከፍተኛ ቁጥር ያለው (ሪከርድ) የደም ልገሳ መርሐ ግብር በቤተ ክርስቲያኒቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዲከናወን አድርገናል። የቤተክርስቲያን መሪዎች እና ምዕመናኑም ያለ ምንም ማቅማማት ደም ልገሳ ተተግብሮአል። ቤተክርስቲያናችን አንዳንድ ጽንፊ የረገጡ ሰዎች በክፋት ተነሳስተው ስሟን በከንቱ የሚያጠፏት ዓይነት አይደለችም። ለዚህ ጉዳይ የከተማው ማሕበረሰብ በሙሉ ምስክር ናቸው።
4. በስፖርት ዘርፍ፦
የመጀመሪያውን የሴቶች የእግር ኳስ ቡድን በማቋቋም በከተማ ደረጃ ሴቶችን በማበረታታት ረገድ ቀዳሚዎች ነን። ከእነዚህም ተጫዋቾች መካከል አንዳንዶቹ አሁን ላይ ለወላይታ ዲቻ ዋና ቡድን እየተጫወቱ ይገኛሉ።
5. በአስቸጋሪ ወቅቶች (ለምሳሌ ያክል ኮቪድ-19)፦
በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ለኅብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠርና የጥንቃቄ መልእክቶችን በማድረስ ረገድ የአረካ ከተማ ቁጥር 1 ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ግንባር ቀደም ነበረች።
6. በከተማ ጽዳትና ውበት፦
የተለያዩ መርሐ ግብሮችን ምክንያት በማድረግ የከተማዋን ጽዳትና ውበት በመጠበቅ ረገድ ከፍተኛ ተሳትፎ ስናደርግ ቆይተናል።
በእነዚህ ሁሉ አኩሪ ሥራዎች ምክንያት የከተማዋ የትምህርት ቢሮ እንዲሁም የወጣቶችና ስፖርት መምሪያ በክልል ደረጃ በተደጋጋሚ የአንደኝነት ሽልማትን ለመቀበል በቅተዋል። ይህ ግልጽ የሆነ እውነት ነው! ለዚህ ጉዳይ ታሪክ ራሱ ምስክር ነው።
በቀን 18-08-2018 ዓ.ም. መልዕክቱ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ እንድትተባበሩ እናሳስባለን።

25/04/2026
 ቤተክርስቲያኗ የተመሰረተችው በ1961 ዓ.ም ሲሆን፣ አጀማመሯም በጥቂት አማኞች አማካኝነት በየቤቱ በሚደረግ የጸሎትና የአምልኮ ሥነ-ሥርዓት ነበር። የአማኞች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ቋሚ የ...
25/04/2026


ቤተክርስቲያኗ የተመሰረተችው በ1961 ዓ.ም ሲሆን፣ አጀማመሯም በጥቂት አማኞች አማካኝነት በየቤቱ በሚደረግ የጸሎትና የአምልኮ ሥነ-ሥርዓት ነበር።
የአማኞች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ ቋሚ የመሰብሰቢያ ቦታ አስፈላጊ ሆነ። በዚህም መሠረት ኮሚቴ ተዋቅሮ ለከተማው መስተዳድር የቦታ ጥያቄ አቀረበ። መጀመሪያ ላይ መስተዳድሩ "ቦታ የለንም" በሚል ጥያቄውን ውድቅ ቢያደርገውም፣ አማኞቹ ግን በጸሎትና በጥረት በመቀጠላቸው በመጨረሻም አሁን ያለችበት ቦታ ተሰጣቸው።
ቤተክርስቲያኗ ያረፈችበት ቦታ ቀደም ሲል የቆሻሻ መጣያ ተብሎ የሚጠራ ሥፍራ ነበር። ዛሬ ግን ያ የተናቀ ስፍራ በእግዚአብሔር ረድኤት ተለውጦ ለከተማዋ ውበትና ለነዋሪዎቿ የመንፈሳዊ ዕረፍት ምንጭ የሆነ ታላቅ የአምልኮ ስፍራ ለመሆን በቅቷል።
ሰሞኑን ከአረካ ከተማ አስተዳደር በአረካ ከተማ ቁ-1 ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ላይ
ስለሚደርሰውና እየደረሰ ላለው በደል አስመልክቶ

👉 ወቅታዊ የአቋም መግለጫ ነጥቦች

ቤተክርስቲያኗ በሰሞኑ ሁኔታ ላይ ያላትን አቋም በሚከተሉት አምስት ነጥቦች ገልጻለች፡-
ሀ/ የጸሎት ጥሪ፦ በመላው ዓለምና በኢትዮጵያ የሚገኙ ምዕመናን ሁሉ ስለ ቤተክርስቲያኗ በጸሎት እንዲተጉ ጥሪ ቀርቧል።
ለ/ የስም ማጥፋት ዘመቻ ይቁም፦ በቤተክርስቲያኗና በመሪዎቿ ላይ የተጀመረው የማጥቃትና ስም የማጥፋት ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም ትጠይቃለች።
ሐ/ የልማት ስራ እንቅፋት ይወገድ፦ ቤተክርስቲያኗ የገዛ ይዞታዋን እንዳታለማ የተከለከለችበትንና በልማት ስራዋ ላይ የተጻፈውን የማገጃ ደብዳቤ አጥብቃ ትቃወማለች፤ የተጀመረው ሁከትም እንዲቆም ትጠይቃለች።
መ/ የሕልውና ጥበቃ፦ የቤተክርስቲያንን ሕልውና አደጋ ላይ የሚጥሉና ስሟን የሚያጠለሹ ማናቸውም የዘመቻ ተግባራት እንዲቆሙ አጥብቃ ታሳስባለች።
ሠ/ የመንግስት ጣልቃ ገብነት፦ የከተማው አስተዳደር በቤተክርስቲያኗና በመሪዎቿ ላይ እያደረሰ ያለውን ኢ-ሕገመንግስታዊ እርምጃና ዛቻ ቤተክርስቲያኗ አጥብቃ ትቃወማለች።
እኛ እንደ ቤተ ክርስቲያን ሁሌም ሰላምን፣ ፍቅርን እና አንድነትን በማስፋፋት ለማህበረሰብ ጥቅም መሥራታችንን እንቀጥላለን። በዚህም ጉዳይ ፍትሃዊ እና ሕጋዊ መፍትሔ እንዲሰጥ በክብር እንጠይቃለን። በቀን 17-08-2018 ዓ.ም. መልዕክቱ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ እንድትተባበሩ እናሳስባለን።
ቤተክርስቲያን በተለያዩ ዘርፎች የሰራችውን እና እየሰራች ያለችውን ተግባራት አያይዘን እናቀርባለን።

A Brief History and Current Status of Kale Hiwot Church, Areka City No. 1
The church was founded in 1961, and its beginning was a prayer and worship service held in each home by a few believers.
As the number of believers increased, a permanent meeting place became necessary. Accordingly, a committee was formed and submitted a request for a site to the city government. Although the government initially rejected the request, saying, "We do not have a place," the believers continued to pray and strive, and finally were given the current site.
The site where the church stands was previously known as a garbage dump. Today, however, that neglected site has been transformed by God's grace into a great place of worship that is a source of beauty for the city and a source of spiritual rest for its residents.
Recently, the Areka City Administration issued a statement regarding the abuse that has been and is being committed against the Qala Hiwot Church in Areka City No. 1

👉 Current Position Statement Points

The Church has expressed its position on the current situation in the following five points:-
A/ Call for Prayer: All believers throughout the world and in Ethiopia are called to pray for the Church.
B/ Stop the Defamation Campaign: It calls for the immediate cessation of the campaign of attacks and defamation against the Church and its leaders.
C/ Remove obstacles to development work: The Church strongly opposes the letter of prohibition that has been written on its development work and prohibits it from developing its own property; it also calls for the cessation of the violence that has begun.
D/ Protect the Existence: It strongly urges that any campaign activities that threaten the existence of the Church and tarnish its reputation be stopped.
E/ Government Intervention: The Church strongly opposes the unconstitutional actions and threats being taken by the city administration against the Church and its leaders.
We, as a church, will always continue to work for the benefit of the community by promoting peace, love and unity. We respectfully request that a fair and legal solution be provided to this matter. On 17-08-2018 E.C. We urge you to cooperate by sharing the message so that it reaches many.

19/04/2026

የአረካ ከተማ ቁጥር 1 ቃለ ህይወት በ ኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን በወላይታ ዞን ካሉ አንጋፋና ጥንካሬያቸው ከሚመሰከርላቸው አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዷ ናት። ቤተክርስቲያኗ ከመንፈሳዊ አገልግሎቷ ጎን ለጎን፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ተምሳሌታዊ ተግባራትን ስታከናውን ቆይታለች።
ቤተክርስቲያኗ እስካሁን ያከናወነቻቸው ዋና ዋና ተግባራት፦
በጤና ዘርፍ፦ የማህበረሰቡን ጤና ለመጠበቅ የግልና የአካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን በተለያዩ መንገዶች ስትሰራ ቆይታለች።
በትምህርት ዘርፍ፦ ጥራቱን የጠበቀ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመክፈት፣ በክልል ደረጃ በ8ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና አንደኛ በመውጣት ተሸላሚና ሞዴል መሆን ችላለች።
በከተማ ልማት፦ የተለያዩ የንግድ ሱቆችን በመገንባትና የንግድ እንቅስቃሴዎችን በማስፋፋት ለከተማዋ ዕድገት የራሷን ድርሻ እያበረከተች ትገኛለች።
የወቅቱ ጥሪና የልማት ዕቅድ፦
በአሁኑ ወቅት ቤተክርስቲያኗ በመንግስት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት፣ በነባር ይዞታዋ ላይ የኮሪደር ልማት ሥራ ለመስራት በዝግጅት ላይ ትገኛለች። የቤተክርስቲያኒቷ ዋና ሰብሳቢ አቶ ነጋው ሳሙኤል ፕሮጀክቱን ለማስጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸው፣ በመላው ዓለም የሚገኙ የቤተክርስቲያን ልጆችንና ደጋግ ኢትዮጵያውያንን ጥሪ አቅርበዋል።
የሥራው ባለቤት እግዚአብሔር ነውና፣ ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከግብ እንዲደርስ ሁላችሁም በጸሎት፣ በሃሳብና በገንዘብ ከጎናችን እንድትቆሙ በእግዚአብሔር ፍቅር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ድጋፍ ለማድረግ፦
በገንዘብ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000039060845
ብርሃን ባንክ (Berhan Bank)፦ 1601540014654
በሙያና በምክር፦
በከተማ ፕላን፣ በግንባታ፣ በዲዛይንና በልማት አስተዳደር ዘርፍ ያላችሁን ልምድና ዕውቀት በማካፈል ፕሮጀክቱን መደገፍ ትችላላችሁ።
ለተጨማሪ መረጃ፦
አቶ ነጋው ሳሙኤል (ዋና ሰብሳቢ)፦ +251910439136
መጋቢ በረከት ጎአ (ዋና መጋቢ)፦ +251968751344
እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይባርካችሁ!
መልዕክቱ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ እንድትተባበሩ እናሳስባለን።

በአረካ ከተማ በቤተክርስቲያን ይዞታ ዙሪያ እየተከሰተ ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ የቀረበው አቤቱታ በግልጽ እና በዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦ጉዳዩ፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የታሰሩ የቤተክርስቲያን...
18/04/2026

በአረካ ከተማ በቤተክርስቲያን ይዞታ ዙሪያ እየተከሰተ ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ የቀረበው አቤቱታ በግልጽ እና በዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ጉዳዩ፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የታሰሩ የቤተክርስቲያን መሪዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እና ለይዞታ ጥያቄው ተገቢው ምላሽ እንዲሰጥ ስለመጠየቅ

ቤተክርስቲያኒቱ ካላት ነባር ይዞታ ጋር በተያያዘ፣ ከዞኑ መንግሥት በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ጉዳዩ በውይይት እንዲፈታ እስከ ላይኛው የመንግሥት መዋቅር ድረስ የመብት ጥያቄዋን በሰላማዊ መንገድ እያቀረበች ትገኛለች።

ይሁን እንጂ፣ ይህ ሕጋዊ ሂደት እየተከናወነ ባለበት ሁኔታ፣ የከተማው አስተዳደር ዛሬ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም (እንደ ወቅቱ አቆጣጠር) ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የቤተክርስቲያኒቱን መሪዎች ያለምንም ጥያቄና በግፍ በአረካ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አስሮ አቆይቷቸዋል።

ይህ በቤተክርስቲያን መሪዎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ኢ-ፍትሐዊ እስር በአስቸኳይ እንዲቆም፣ የታሰሩትም እንዲፈቱ እና ለቀረበው የይዞታ ጥያቄ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ፈጣንና ፍትሐዊ ምላሽ እንዲሰጥ አጥብቀን እንጠይቃለን።

16/04/2026

ይሄን የቤተክርስቲያንን ሥራና አገልግሎትን በምትችሉት ነገር ሁሉ ለመደገፍ እጃችሁ አይላላ። የሥራው ባለቤት እግዚአብሔር ነውና ሁላችሁም በጸሎት፥ ሐሳብ በመስጠት እና በገንዘብ በጎናችን እንድትቆሙ በእግዚአብሔር ፍቅር እናሳስባለን።
1. በገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ የምትፈልጉ፦
በቤተክርስቲያኑ የተዘጋጀ የባንክ ሂሳብ [1000039060845 CBE,1601540014654 BERHAN BANK ] ገቢ በማድረግ፣ ለፕሮጀክቱ ቀጣይነት አስተዋፅኦ ማበርከት ትችላላችሁ።
2. በሙያና በምክር፦
በከተማ ፕላን፣ በግንባታ፣ በዲዛይን እና በልማት አስተዳደር ዘርፍ ያላችሁን ልምድና እውቀት በማካፈል ፕሮጀክቱን ማጠናከር ትችላላችሁ። [የኢሜይል አድራሻ ወይም ስልክ ቁጥር 0910439136 አቶ ነጋዉ ሳሙኤል(ዋ/ሰብሳቢ )
0968751344 በረከት ጎአ ዋ/መጋቢ ]
በነገር ሁሉ እግዚአብሔር ይባርካችሁ።

Yeshua በሚል ርዕስ በባለራእይ ድራማና ሥነ ፅሑፍ ቡድን የተዘጋጀውን አስተማሪ የሆነውን ፕሮግራም ከታች ባስቀመጥነው በቤተክርስቲያናችን TikTok Account በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፈው...
12/04/2026

Yeshua በሚል ርዕስ በባለራእይ ድራማና ሥነ ፅሑፍ ቡድን የተዘጋጀውን አስተማሪ የሆነውን ፕሮግራም ከታች ባስቀመጥነው በቤተክርስቲያናችን TikTok Account በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፈውን ገብተው በመከታተል እንድትባረኩበት እናሳስባለን።

.number1.kale 1067 Followers, 0 Following, 2145 Likes - Watch awesome short videos created by Areka No-1 KHC Officially

ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርሰቶስ ሞትና ትንሳኤ መታሰቢያ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ! ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።      ...
12/04/2026

ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርሰቶስ ሞትና ትንሳኤ መታሰቢያ በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ!

ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።
(የሉቃስ ወንጌል 24:5)
" እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና.. ይህን ኢየሱስን እግዚአብሔር አስነሣው ለዚህም ነገር እኛ ሁላችን ምስክሮች ነን፤ስለዚህ በእግዚአብሔር ቀኝ ከፍ ከፍ ብሎና የመንፈስ ቅዱስን የተስፋ ቃል ከአብ ተቀብሎ ይህን እናንተ አሁን የምታዩትንና የምትሰሙትን አፈሰሰው።"
(የሐዋርያት ሥራ 2:24፣32-33)
የአረካ ከተማ ቁ፩ (እናት)ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን

Address

Wolayta
Areka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Areka No.1 kale hiwot church youth officially posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share