24/08/2026
በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ። 2ኛ ዜና 7:14
በአርቤጎና ያዬ ከተማ የአብያተ ክርስቲያናት ህብረት አስተባባሪነት በከተማዋ እምብርት በሚገኘው አደባባይ ታላቅ የጋራ የጸሎት፣ የንስሐና የምልጃ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።
የከተማዋ አብያተ ክርስቲያናትና ምእመናን በአንድነት ወደ አደባባይ በመውጣት፣ በፈጣሪ ፊት በመንበርከክና ንስሐ በመግባት ምድራቸው እንዲፈወስ ፀልየዋል።
- በመሃል አደባባይ በአፈር ላይ ተንበርክከው፣ በእግዚአብሔር ፊት በእንባና በምሬት አልቅሰዋል። ስለራሳቸው፣ ስለከተማቸው እንዲሁም ስለአባቶች በደል ንስሐ በመግባት የእግዚአብሔርን ምህረት ጠይቀዋል።
- ለበርካታ ባለስልጣናትና ለሚመለከታቸው አካላት የመንገድ ችግራቸውን አብራርተውና አመልክተው ምንም ዓይነት ዘላቂ መፍትሔ ማግኘት አልቻሉም። በመሆኑም ሕዝቡ መፍትሔውን ከሰዎች ሳይሆን ከሰማዩ አባት በመጠበቅ በለቅሶ ወደ አምላኩ ፀልዩአል።
- የዚህን መንገድ ሥራ የሚያስተጓጉል፣ የሚያዘገይና እንቅፋት የሆነ ማንኛውም ሰው ሰራሽም ሆነ መንፈሳዊ ከልካይ ኃይል በፈጣሪ እጅ እንዲወገድና መንገዱ እንዲከፈት በጽኑ ተጸልያል።
የያዬ ከተማ ሕዝብ በእንባና በጸሎት የዘራነዉን የፈውስና የልማት ፍሬ አምላክ በጊዜው እንደሚምመልስልን ሙሉ እምነት አለን!