ዜና ሥላሴ በአርባ ምንጭ የደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሚዲያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • ዜና ሥላሴ በአርባ ምንጭ የደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሚዲያ

ዜና ሥላሴ በአርባ ምንጭ የደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ   ክርስቲያን ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ዜና ሥላሴ በአርባ ምንጭ የደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሚዲያ, Religious organisation, South, Arba Minch'.

01/06/2026
የጋሞኛ ቋንቋ ትርጉም ውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ በደመቀ ሁኔታ ተመረቀግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ ...
26/05/2026

የጋሞኛ ቋንቋ ትርጉም ውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ በደመቀ ሁኔታ ተመረቀ

ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም

በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሀገር ሽማግሌዎችና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ዛሬ ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።

የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የተከናወነው በአርባምንጭ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ በሚገኘው በማህበረ ቅዱሳን የሥብከተ ወንጌል መሰብሰቢያ አዳራሽ ነው።

በዕለቱ የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ፣የአርባ ምንጭ ዙሪያና የጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን አበባው ጌታሁን ፣ክቡር አቶ ሽመልስ ታደሰ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፣ክቡር አቶ ደስታ ደምበላ የአርባ ምንጭ ከተማ ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ፣ የማህበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የተለያዩ አድባራትና አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማሪያን ፣ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆች ማህበረ ምዕመናን በቦታው ተገኝተዋል።

በምረቃው መርሃ-ግብር ላይ እንደተገለጸው፣ ይህ በጋሞኛ ቋንቋ የተዘጋጀው ውዳሴ ማርያም ምዕመናን የፈጣሪያቸውንና የድንግል ማርያምን ምስጋና በገዛ ቋንቋቸው በመጸለይ መንፈሳዊ እርካታን እንዲያገኙና ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምታስተምረውን ስርአተ አምልኮ ይበልጥ ለመረዳት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

የሀገረ ስብከቱ ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ መጽሐፉ ተተርጉሞ ለምረቃ እንዲበቃ ከፍተኛ ጥረት ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን፣ ይህ ታሪካዊ ክንውን የቤተክርስቲያንን የወንጌል አገልግሎት ተደራሽነት ይበልጥ እንደሚያሰፋውና ለአካባቢው ማህበረሰብ ትልቅ መንፈሳዊ ስጦታ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ታሪካዊ ሥራ ላይ ከፍተኛ ድርሻ ለነበራቸው ለአባቶችና ለባለሙያዎች (ለቀሲስ ኢ/ር ገዳሙ አድማሱ፣ ለዲያቆን ታደሰ ካንኮ፣ ለዲያቆን ተካልኝ በቀለ፣ ለዲያቆን አእላፍ አዳሙ እና ለአቶ ቃይዳ ቆና) በማኅበረ ቅዱሳን ስም የምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

በዕለቱ ከተሳታፊዎች የተሰበሰበው አስተያየት እንደሚያመላክተው፣ መጽሐፉ መመረቁ ትልቅ ደስታን የፈጠረ ከመሆኑም በላይ ወደፊትም ሌሎች ተመሳሳይ የትርጉም ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መነሻ እንደሚሆን ተመልክቷል። ሥነ-ሥርዓቱ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት፣ በምስጋና እና በጸሎት ተጠናቋል።

ምንጭ፦ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ዜና ሥላሴ በአርባ ምንጭ የደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሚዲያ

💥💥የአማኑኤል ቤተ ክርስቲያን የምህላ መረሐ ግብር 💥💥                        📸ዜና ሥላሴ ሚድያ📸በአርባ ምንጭ በሻራ ደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ አጥቢያ የሆነው አማኑኤል ...
24/05/2026

💥💥የአማኑኤል ቤተ ክርስቲያን የምህላ መረሐ ግብር 💥💥
📸ዜና ሥላሴ ሚድያ📸
በአርባ ምንጭ በሻራ ደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ አጥቢያ የሆነው አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን በ15/09/2018 ዓ.ም የምህላ አገልግሎት በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

“መረሐ ግብር ላይ የቤተ ክርስቲያኑ አገልጋዮችና ምዕመናን በብዛት ተገኝተው በጸሎት፣ በመዝሙር እና በመንፈሳዊ ትምህርት ተሳትፈዋል። ፕሮግራሙ የአንድነት፣ የፍቅር እና የመንፈሳዊ መታደስ መልዕክት አስተላልፏል።

⏰በቀጣይ 28/09/2018 ዓ.ም ተመሳሳይ መንፈሳዊ መረሐ ግበ‍እር እንደሚካሄዱ ገልጸዋል።

21/05/2026

ዜና ሥላሴ ሚድያ

 #በአርባ ምንጭ ሻራ ደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት "መርጌታ መዝገቡ ጌታሁን “የሊቀ አዕላፍ”የማዕረግ ስም ተሰጣቸው። #በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በ...
10/05/2026

#በአርባ ምንጭ ሻራ ደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት "መርጌታ መዝገቡ ጌታሁን “የሊቀ አዕላፍ”የማዕረግ ስም ተሰጣቸው።

#በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በአርባ ምንጭ ከተማ ሻራ ደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በመርጌትነት ሲያገለግሉ የቆዩት መርጌታ መዝገቡ ጌታሁን ፣ እስከ ዛሬ ድረስ ላበረከቱት ላቅ ያለ መንፈሳዊና ማህበራዊ አገልግሎት “የሊቀ አዕላፍ” የማዕረግ ስም ተሰጣቸው።

ይህ የማዕረግ ስም የተሰጣቸው የጋሞና አካባቢው ጎፋና ባስኬቶ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በብፁዕ አቡነ ኤልያስ አማካኝነት ሲሆን፣ አዲሱ የማዕረግ ስማቸውም "ሊቀ አዕላፍ መርጌታ መምህር መዝገቡ ጌታሁን" ተብሎ በይፋ ተነግሯል።

ሊቀ አዕላፍ መርጌታ መምህር መዝገቡ ጌታሁን በአርባ ምንጭ ከተማ በአቋቋም መምህርነትና በመርጌታነት ለ፳፫ (23) ዓመታት በታማኝነት ያገለገሉ ሲሆን፣ በዚህ ቆይታቸውም በርካታ ቀሳውስትና ዲያቆናትን በማፍራት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተተኪ መምህራንን ሲያፈሩ ቆይተዋል።

ከመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ባሻገር፣ በመንግስት የጤና ተቋም ውስጥ በጤና ባለሙያነት በመሰማራት ሕዝብንና መንግስትን በቅንነት እያገለገሉ የሚገኙ ታታሪ አገልጋይ መሆናቸው ይታወቃል።

"በሁለት በኩል የተሳሉ" በሚል የተገለጹት መምህሩ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ለሕዝብ አገልግሎት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ መቆማቸው ለዚህ ማዕረግ እንዳበቃቸው ተጠቁሟል። የማዕረግ አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ዛሬ ግንቦት ፪ ቀን ፳፻፲፰ (2 ቀን 2018)ዓ.ም በደብሩ በተከናወነው የክብር ሥነ-ሥርዓት ላይ፦የሀገረ ስብከቱ የትምህርት ክፍል እና የካህናት አስተዳደር ክፍል ኃላፊ መልአከ ልዑል ቃለ ጽድቅ አበጀ እና የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሰብሀት ቀለመ ወርቅ በላይ፣ የሰበካ ጉባኤ አባላት እና በርካታ ማህበረ ምዕመናን በተገኙበት አዲሱ የማዕረግ ስማቸው ይፋ ሆኗል።

Address

South
Arba Minch'
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዜና ሥላሴ በአርባ ምንጭ የደብረ ልዑል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share