ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ነቅዐ ጽድቅ  የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ, Religious Center, Arba Minch, Arba Minch'.
(3)

"ነዋ ወንጌለ መንግሥት"

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/nekeatsidkmedia
▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1
▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/
▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha
▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

29/05/2026

ማህበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ውዳሴ ማርያም ከአማርኛ ወደ ጋሞኛ ቋንቋ ተርጉሞ ባስመረቀበት ወቅት የነበረው የእለቱ መርሃ-ግብር ላይ የአርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ፀሐፊ ቀሲስ መሰረት አሰፋ ንግግር ሲያደርጉ።

ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

27/05/2026

ማህበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ ከአማርኛ ወደ ጋሞኛ ቋንቋ ተርጉሞ ማስመረቁንና ለአካባቢው ምዕመናን ማበርከቱን አስመልክቶ ስለ መጽሐፉ አጠቃላይ ይዘት ፣ዓላማ በተመለከተ ከአዘጋጆች ጋር የተደገ ቆይታ።
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

27/05/2026

ማህበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ውዳሴ ማርያም ከአማርኛ ወደ ጋሞኛ ቋንቋ ተርጉሞ ባስመረቀበት ወቅት የነበረው የእለቱ መርሃ-ግብር ላይ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ የማጠቃለያ የምስጋና ንግግር ሲያደርጉ።
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የጋሞኛ ቋንቋ ትርጉም ውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ በደመቀ ሁኔታ ተመረቀ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ነቅዓ ጽድቅ ጋሞና አካባቢ...
24/05/2026

የጋሞኛ ቋንቋ ትርጉም ውዳሴ ማርያም የጸሎት መጽሐፍ በደመቀ ሁኔታ ተመረቀ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ነቅዓ ጽድቅ ጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሀገር ሽማግሌዎችና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ዛሬ ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።

የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ የተከናወነው በአርባምንጭ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ በሚገኘው በማህበረ ቅዱሳን የሥብከተ ወንጌል መሰብሰቢያ አዳራሽ ነው።

በዕለቱ የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ፣የአርባ ምንጭ ዙሪያና የጋጮ ባባ ወረዳዎች ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን አበባው ጌታሁን ፣ክቡር አቶ ሽመልስ ታደሰ የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፣ክቡር አቶ ደስታ ደምበላ የአርባ ምንጭ ከተማ ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ፣ የማህበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የተለያዩ አድባራትና አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ዘማሪያን ፣ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆች ማህበረ ምዕመናን በቦታው ተገኝተዋል።

በምረቃው መርሃ-ግብር ላይ እንደተገለጸው፣ ይህ በጋሞኛ ቋንቋ የተዘጋጀው ውዳሴ ማርያም ምዕመናን የፈጣሪያቸውንና የድንግል ማርያምን ምስጋና በገዛ ቋንቋቸው በመጸለይ መንፈሳዊ እርካታን እንዲያገኙና ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምታስተምረውን ስርአተ አምልኮ ይበልጥ ለመረዳት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

የሀገረ ስብከቱ ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ መጽሐፉ ተተርጉሞ ለምረቃ እንዲበቃ ከፍተኛ ጥረት ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን፣ ይህ ታሪካዊ ክንውን የቤተክርስቲያንን የወንጌል አገልግሎት ተደራሽነት ይበልጥ እንደሚያሰፋውና ለአካባቢው ማህበረሰብ ትልቅ መንፈሳዊ ስጦታ መሆኑን ገልጸዋል።

​በዚህ ታሪካዊ ሥራ ላይ ከፍተኛ ድርሻ ለነበራቸው ለአባቶችና ለባለሙያዎች (ለቀሲስ ኢ/ር ገዳሙ አድማሱ፣ ለዲያቆን ታደሰ ካንኮ፣ ለዲያቆን ተካልኝ በቀለ፣ ለዲያቆን አእላፍ አዳሙ እና ለአቶ ቃይዳ ቆና) በማኅበረ ቅዱሳን ስም የምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

በዕለቱ ከተሳታፊዎች የተሰበሰበው አስተያየት እንደሚያመላክተው፣ መጽሐፉ መመረቁ ትልቅ ደስታን የፈጠረ ከመሆኑም በላይ ወደፊትም ሌሎች ተመሳሳይ የትርጉም ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ መነሻ እንደሚሆን ተመልክቷል። ሥነ-ሥርዓቱ በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት፣ በምስጋና እና በጸሎት ተጠናቋል።

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች ያግኙን፤ ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/nekeatsidkmedia

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.co m/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/nekeatsidkemedia?igsh=MWsycDFxaW0yaWxyaQ==

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

23/05/2026

አርባ ምንጭ እድገት በር ደብረ አእላፍ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ፍልሰተ አጽም ዓመታዊ ክብረ በዓል መታሰቢያ ግንቦት ፲፪/፳፻፲፰ ዓ/ም
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በምዕራብ አባያ ወረዳ ቤተ ክህነት በብርብር ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ትምህርት ቤት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጎበኙ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፲፰...
23/05/2026

በምዕራብ አባያ ወረዳ ቤተ ክህነት በብርብር ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ትምህርት ቤት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ተጎበኙ
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ነቅዓ ጽድቅ ጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

በጋሞ እና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በምዕራብ አባያ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር ከሚገኙ መንፈሳዊና ማኅበራዊ የልማት ተቋማት መካከል አንዱ በሆነው በብርብር ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል መጀመሪያና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተከናወኑ የልማት ሥራዎች የመስክ ምልከታና ቅኝት ተካሄደባቸዋል።

በትምህርት ቤቱ የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የተከናወኑትን ዘርፈ-ብዙ የልማት ተግባራት ለመገምገምና ለማበረታታት በተደረገው በዚህ ጉብኝት ላይ ከሀገረ ስብከት የመጡ ከፍተኛ ልዑካን፣ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ ዋና ፀሐፊ ፣መጋቤ ሀብታት ቀሲስ ደጉ አልቤ የሒሳብና በጀት ክፍል ኃላፊ፣ የወረዳው ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መርጌታ ታምራት፣ የደብሩ ሰበካ ጉባዔ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት የምዕራብ አባያ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መርጌታ ታምራት እና የደብሩ ሰበካ ጉባዔ አባላት በትምህርት ቤቱ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የተሰሩ የልማት ሥራዎችን ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል። የጉብኝቱ ተሳታፊዎችም ትምህርት ቤቱ በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ የልማት አቅምና የውስጥ አደረጃጀት እጅግ የተሻለና አርአያነት ባለው የአፈፃጸም ደረጃ ላይ መድረሱን በተግባር ተመልክተዋል።

የልማት ሥራዎቹን የጎበኙት የጋሞ እና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሠናያት ያዕቆብ ደስታ እና የሀገረ ስብከቱ የሒሳብና በጀት ክፍል ኃላፊ መጋቤ ሀብታት ደጉ አልቤ፤ ትምህርት ቤቱ ማኅበረሰባዊ አገልግሎቱን ለማስፋፋትና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እስካሁን ያከናወናቸውን አስደናቂ ተግባራት በላቀ ሁኔታ አድንቀዋል።

ኃላፊዎቹ አክለውም፣ የተመዘገቡት ስኬቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉና ተቋሙ ይበልጥ እንዲዘምን ለቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸውና ሊሰሩ በሚገቡ ዋና ዋና ተግባራትና ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ዙሪያ ጠቃሚ ምክረ-ሀሳቦችንና መመሪያዎችን ሰጥተዋል።

ቤተ ክርስቲያን ከመንፈሳዊ ተልዕኮዋ ጎን ለጎን የምታከናውናቸው እንደነዚህ ያሉ የልማትና የትምህርት ሥራዎች ለአካባቢው ማኅበረሰብ ሁለንተናዊ ዕድገትና ለትውልድ ግንባታ ያላቸው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን የዕለቱ የጉብኝት ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

📷 የምዕራብ አባይ ወረዳ ቤተ ክህነት ሚዲያ ነው።

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች ያግኙን፤ ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/nekeatsidkmedia

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.co m/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/nekeatsidkemedia?igsh=MWsycDFxaW0yaWxyaQ==

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

ታላቅ መንፈሳዊ የምስራች! በጋሞኛ ቋንቋ ተተርጉሞ የተዘጋጀው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በአርባ ምንጭ ይካሄዳል።፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ግን...
23/05/2026

ታላቅ መንፈሳዊ የምስራች!

በጋሞኛ ቋንቋ ተተርጉሞ የተዘጋጀው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በአርባ ምንጭ ይካሄዳል።
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ነቅዓ ጽድቅ ጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

«ከእግዚአብሔርም ሕግ መጽሐፍ አነበቡ፥ ትርጓሜውንም እየሰጡ አስታወቁት፥ ሕዝቡም ንባቡን አስተዋለ።» ነህምያ ፰:፰

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን አገልግሎትን በቋንቋቸው ተደራሽ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ እና በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር በቅርቡ በአርባ ምንጭ ከተማ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

ይህንን ታላቅ መንፈሳዊ መርሃ-ግብር ያዘጋጀው በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ምዕመናን የእግዚአብሔርን ቃል እና የድንግል ማርያምን ምስጋና በቋንቋቸው በመማርና በመጸለይ መንፈሳዊ ሕይወታቸውን እንዲያሳድጉና ለነፍሳቸው ስንቅ እንዲሰበስቡ ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ መሆኑ ታውቋል።

በዕለቱ በሚካሄደው ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ በጋሞኛ ቋንቋ የተተረጎመው የ“ውዳሴ ማርያም” የጸሎት መጽሐፍ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት፣ ዕለቱን የጠበቀ መንፈሳዊ ስብከተ ወንጌል፣ በማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን የሚቀርቡ መንፈሳዊ መዝሙራት እና ሌሎች ልዩ ልዩ መንፈሳዊ መርሃ-ግብሮች ይካሄዳሉ።

በዚህ ታላቅ መርሃ-ግብር ላይ የሀገረ ስብከቱ ዋና ፀሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ፣ የሀገረ ስብከቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና መምህራነ ወንጌል፣ዘማሪያን፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶች በክብር ይገኛሉ።

ይህ ታሪካዊ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት የሚካሄድበት የፊታችን እሁድ ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በአርባ ምንጭ ደ/ኃ/ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በሚገኘው በማኅበረ ቅዱሳን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሲሆን አዘጋጁ ማኅበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል።

አዘጋጅ፦ ማህበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች ያግኙን፤ ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/nekeatsidkmedia

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.co m/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/nekeatsidkemedia?igsh=MWsycDFxaW0yaWxyaQ==

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

በማኅበረ ካህናትና በምእመናን ዘንድ ታላቅ አክብሮትና ምስጋና የተቸራቸው መልአከ ብስራት መኮንን እሸቱ የክብር አሸኛኘት ተደረገላቸው።፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ግንቦት ፲፬...
22/05/2026

በማኅበረ ካህናትና በምእመናን ዘንድ ታላቅ አክብሮትና ምስጋና የተቸራቸው መልአከ ብስራት መኮንን እሸቱ የክብር አሸኛኘት ተደረገላቸው።
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ግንቦት ፲፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ነቅዓ ጽድቅ ጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምንጭ

የቀድሞ የአርባ ምንጭ እድገት በር ደብረ አእላፍ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የነበሩት መልአከ ብስራት መኮንን እሸቱ ላበረከቱት ከፍተኛ መንፈሳዊና ልማታዊ አገልግሎት እውቅና የሰጠ ታላቅ የክብር አሸኛኘት መርሃ ግብር ተካሄደ።

መልአከ ብስራት መኮንን እሸቱ ደብሩን በበላይነት በአስተዳዳሪነት በመሩበት የሥራ ዘመናቸው፥ የቤተ ክርስቲያኗን መንፈሳዊ ተልዕኮ ከማስፋፋት ባለፈ በደብሩ ውስጥ በርካታ ዘላቂ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ፣ መዋቅራዊ አደረጃጀቶች እንዲጠናከሩና የአገልጋዮችና የምእመናን አንድነት እንዲጠበቅ በቁርጠኝነት መሥራታቸው በዕለቱ ተገልጿል።

ይህንን ታላቅና ፍሬያማ አገልግሎታቸውን ተከትሎም፥ በአሁኑ ሰዓት የጎፋና ባስኬቶ ሀገረ ስብከት ቁጥጥር ክፍል ኃላፊ በመሆን ወደ ተሻለና ከፍ ወዳለው የማዕረግ የሥራ ኃላፊነት መሸጋገራቸው ተገልጿል።

በታላቅ ድምቀት በተከናወነው በዚህ የሽኝት መርሃ ግብር ላይ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ከፍተኛ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች፣የየአድባራቱ አስተዳዳሪዎች፣ የደብረ አእላፍ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አዲሱ አስተዳዳሪ መልአከ መዊዕ አስተርዓየ አሻግሬ፣ የሰበካ ጉባኤ አባላትና የልማት ኮሚቴዎች፣ የደብሩ አገልጋይ ቀሳውስት፣ ዲያቆናትና መምህራነ ወንጌል እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ምእመናን ተገኝተዋል። በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የደብሩ የሰበካ ጉባኤ ለመልአከ ብስራት መኮንን እሸቱ ላበረከቱት ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ምስጋናውን በመግለጽ የክብር ስጦታ አበርክቶላቸዋል።

በሌላ በኩል መልአከ ብስራት መኮንን እሸቱን በመተካት መልአከ መዊዕ አስተርዓየ አሻግሬ የደብረ አእላፍ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አዲስ አስተዳዳሪ ሆነው በይፋ ሥራ መጀመራቸው ይታወሳል። አዲሱ አስተዳዳሪ በሽኝቱና በኃላፊነት ርክክቡ ሰዓት ባስተላለፉት መልዕክት፥ የተሰጣቸውን ታላቅ መንፈሳዊ አደራ የተቀበሉት በደስታ መሆኑን ገልጸው፥ የተጀመሩ መንፈሳዊና ልማታዊ ሥራዎችን ይበልጥ በተሻለ ሁኔታ ለማስቀጠልና ቤተ ክርስቲያኗን ወደ ላቀ ዕድገት ለማድረስ በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ ቃል ገብተዋል።

ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች ያግኙን፤ ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።

▶️ቴሌ ግራም
https://t.me/nekeatsidkmedia

▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.co m/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/nekeatsidkemedia?igsh=MWsycDFxaW0yaWxyaQ==

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

22/05/2026

በአርባ ምንጭ እድገት በር ደብረ አእላፍ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊው ፍልሰተ አጽማቸው ግንቦት ፲፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ሲከበር
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

እርገተ ክርስቶስነቅዐ ጽድቅ  የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ
21/05/2026

እርገተ ክርስቶስ
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

21/05/2026

መ/ር አባይነህ ጸጋዬ|የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ | በአርባ ምንጭ እድገት በር ደብረ አእላፍ አቡነ ተእለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ያስተማሩት ትምህርት ግንቦት ፲፪/፳፻፲፰ ዓ/ም
ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ

Address

Arba Minch
Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share