ተስፋ የበጎ-አድራጎት ክበብ

ተስፋ የበጎ-አድራጎት ክበብ ኦርቶዶሳዊ ለሆኑ እና ከኢ-አማንያን ለሚነሱ ጥያቄዎች እንዲሁም ኦርቶዶክሳዊዉን ት/ት ከ መጽሃፍ ቅዱስ እና ከ አባቶች አስተምህሮ ተመዠኖ ይመለሳል

24/07/2018
08/12/2017

Deacon Henok Haile
አንዱ ወደ አንድ አባት ቀረብ ብሎ "ድንግል ማርያም እኮ
እንደ እኛ ሰው ናት" አላቸው። እርሳቸውም "ልክ ነህ
እርስዋ በተፈጥሮዋ ሰው ናት ፣ አንተ ግን ሰው ነህ?"
አሉት።
ነገሩ ስድብ ይመስላል ፣ አስተውሎ ላየው ግን ሰው ነኝ
ለማለትም መሥፈርት እንዳለው ያስታውሳል። "ኤልያስ
እንደ እኛ ሰው ነበረ" ነገር ግን ዝናምን በጸሎቱ ያቆመ
መሆኑን ስንሰማ ሰው ነን ለማለት እንፈራለን። ንጉሥ
ዳዊት ለልጁ ሰሎሞን "ሰው ሁን" ያለው ሰው መሆን
ማለት እንደ ሰው ክብርን አውቆ መኖር ስለሆነ ነው።
ክቡር ሆኖ ሳለ ካላወቀና በኃጢአቱ ከጸና እንደሚጠፉ
እንስሳት ይመስላል።
ሰው ለመሆን ብዙ መሥፈርቶች በመጽሐፍ ቅዱስ
ተቀምጠዋል ፣ የድንግል ማርያምን እናትነት መቀበልም
ሰው የመሆን ምልክት ነው።
"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል" ተብሎ እንደተጻፈ "ጽዮን
እናታችን" ማለት ያልቻለ ምኑ ሰው ይባላል?
"የእግዚአብሔር ከተማ ጽዮን ሆይ ይሉሻል የናቁሽ ወደ
እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ" ተብሎ ለዳዊት ከተማ
ተነግሮላት ነበር። ስንት ኃጢአተኛ ሲራኮትባት ለሚውልባት
ለዳዊት ከተማ የሚሰገድ ከሆነ ለንጽሕቲቱ ከተማው
ለድንግል ማርያም አይሰገድም እንዴት ይባላል? ነቢዩ
ከጽዮን ጫማ በታች ይሰግዳሉ ብሎ ለዳዊት ከተማ
ከተናገረ ከድንግሊቱ ጫማ በታች እንዴት ይሰገድ ይሆን?
በእርግጥ የናቅዋት ሁሉ ወደ ጫማዋ ሊሰግዱ ይሆን?
በፍጹም አይሆንም! የድንግልን ጫማዋንማ ለእኛ
ለምናከብራትም ማን ባደለን? እኛ አክሱም ጽዮን ቁስቋም
ግሸን በረከቷን ሽተን እየተጓዝን የናቋት እንዴት ጫማዋን
ያገኛሉ?
አባ ጊዮርጊስ "ገሊላዊትዋ ድንግል ጫማን እሸከም ዘንድ
፣ ጥላዋ ያረፈበትን እስም ዘንድ ማን ባደለኝ?" ይል
የለምን? ከእግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ ማለት ይዋረዳሉ ነው
እንጂ ይህ ክብር ለናቋት የሚገባ አይደለም።
"ጽዮንን ክበቧት በዙሪያዋም ተመላለሱ" (መዝ 48:12)
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
[email protected]
ኅዳር 21 2009
ሊባኖስ ፣ ጢሮስና ሲዶና

08/12/2017

Mathematicians say LIFE is like a line segment drawn from point B to point D.
What is point B to point D?
It's from point of Birth(B) to point of Death(D).
So life starts from the moment we are Born(B) until the day we Die(D).
But in the middle of B(Birth) and D(Death) is a mysterious C.
What is C then?It is CHRIST.
If we put Christ in the middle of our life(Birth--->Christ--->Death) our life will not end at D but extend to E.
What is E? It's Eternal Life.
So all those who put Christ in the middle of their life have Eternal life after Death
But those who do not put Christ in the middle of their lives don't have Eternal life after Death but they have F(Fire).
Therefore the mathematical Equation or Definition of Life For Christians is
B + C + D = E
Birth+Christ+Death= Eternal Life
And the mathematical Equation or Definition Of Life For Unbelievers:
(B - C ) + D = F
Birth - Christ + Death = Fire
Any one that avoids C must surely lose E
For scriptural references, please check the following
1John 5:11-13 Acts 4:12 John 5:34 Rom 10:1 John 3:16 & 17 Rev 20:11-15
There's always blessing in sharing.... so share with others. He that wins a soul is wise!!!

+++ Taabotaaf Iyyesuus Kiristoos+++{ታቦትና ኢየሱስ ክርስቶስ የሚለውን ጽሑፍ ዲያቆን ዳኜዘርፉ እንደሚከተለው ወደ ኦሮሚፋ ተርጉሞታል::}Manni Kiristaanaa Ort...
19/08/2017

+++ Taabotaaf Iyyesuus Kiristoos+++
{ታቦትና ኢየሱስ ክርስቶስ የሚለውን ጽሑፍ ዲያቆን ዳኜ
ዘርፉ እንደሚከተለው ወደ ኦሮሚፋ ተርጉሞታል::}
Manni Kiristaanaa Ortodoks Tawaahidoo
Itoophiyaa Taabotarratti kan barreessite
maali? Jedhamtanii yoo gaafatamtan deebiin
keessan maal laata? ‹Abboommii kurnantu
irratti barreeffame › yoo jettan deebiin
keessan sirrii miti. Deebii sirrii deebisuu
keenyaan dura waa’ee Taabotaa waan
muraasa haa ilaallu. Yeroo hedduu Waa’ee
barbaachisummaa Taabotaa ibsoota
kennaman irratti bakka guddaa kan qabatan
caqasa Waayee Taabota Kakuu Moofaa kan
dubbatan sababa ta’eef Gaaffileen waayee
Taabotaa akka addaan hin citne kan taasise
fakkata. Kanaaf barreeffama gabaabaa
kanaan kallattiin waayee Taabota kakuu
haaraa haa ilaallu.«
Taabotni Kakuu Haaraa keessatti maaliif
barbaachisa? Gaaffii jedhu deebisuuf guyyaa
dhumaa kamisa galgala gooftaan keenya
icciitii Qurbaanaa itti barsiise haa yaadannu.
Gooftaan keenya bakka duuka buutotni walitti
qabamanitti «Daabbee olkaasee eebbise
cabsees kenneef hoodha nyaadha kun foon
kooti jedheen, Xoofoos olkaasee galateeffate
kanas dhugaa kun sababa cubbuu namoota
baay’ee kan dhangala’u dhiiga koo kakuu
haaraa ti» (Maat.26:26). Gooftaan keenya
dursee «Foon kook an nyaate dhiiga koos
kan dhuge jireenya barabaraa qaba» jechuun
barumsa hundeesse Icciitii Qurbaanaa
dalagaan duuka keebutotatti bifa kanaan
barsiise.(Yoh.6:56) duuka buutotnis erga
Gooftaan keenya olba’ee booda wangeela
lallabaa «Biddeena cabsaa jabaataa turan»
Duuk.2:42 Qulqulluun phaawuloosis ‹Gooftaa
irraa kanan fudhe anis dabarsee isiniif
kenneera› jechuun fooniif dhiiga Gooftaa
akkamitti fudhachuu akka qabnu ‹Otoo hin
ta’iniif kan fudhate idaa fooniif dhiiga
gooftaa› akka irra jiru barsiisuun sirna
Qurbaanaa ka’eera.
Haa qalbeeffannu! fooniif dhiigni gooftaa
kennamuusaa kiristaanni amanu tokko
kabajamaan fooniif dhiiga gooftaa kana akka
maaddii yookaan nyaata gad bu’aa tokkootti
minjaala kamirrattuu dhiyaachuu danda’a
jedhanii yaaduun guddaa ulfaata. Kanaaf
manni kiristaanaa barri wareegamtootaa
darbee hanga bara baqa dhaabdetti yeroo
yerootti fooya’aa kan dhufe seera mana
Qulqullummaa Aarsaa kakuu haaraa
kabajaan aarsuuf ijoollota isheef kennuu
dandesseetti. Aarsaa Hoolaafi re’ee yommuu
arsamaa ture bara kakuu moofaallee
qofaasaatti Teessoon Aarsaa guddaan
qophaa’ee Tsseeoo kanattis namni kan ol itti
hin seenne Dunkaana walga’iinsaa keessatti
kabajaan taa’ee ture. Dukaanattii keessatti
kan tajaajilan Aarooniif Ijoolleensaa Uffata
addaa uffachuun dhiiga hoolichaa gaanfaa
Teessoo Arsaa/mesewiya/ dibuun sirnasaa
raawwachaa turan. Aarsaa dhiiga Hoolaa fi
Re’eef Ulfinni fi kabajni hangi kun yoo
kennameef akka Hoolaa sababa Cubbuu
keenyaa kan kenname ofiisaas Aarsaa hoolaa
jaalatamaa taasisee of dhiyeesse hoolaan
waaqayyoo, akka hangafa lubummaa isaatti
harkasaa fannoorratti diriirsee kan aarfameef
fooniif dhiiga isaas hoodha nyaadhaa jedhee
kan nuuf kenne fooniif dhiigni Gooftaa keenya
Iyyesuus Kiristoos aarsaa ta’ee yoo dhiyaatu
kan irratti dheeyeefamu hagam haa
kabajamuree?
Manni kiristaanaa ortodoks Tawaahidoo
Itoophiyaa fooniif dhiigaaf ‹Teessoo Aarsaa >
kan jettu Taabotni bocaan, tajaajilaan,
kabajaanis Bara Ooriitii Waaqayyo Museef
Taabota kenneef wajjin tokko miti. Taabotni
Duraanii luboota afuriin kan baatamu
keessasaattis Tsillaatiin kan keessa taa’u
yoo ta’u, Taabotni kan ammaa garuu Boca
tsillaatii kan qabu tsillee/gabatee/ dha.
Manni kristaanaa taabota kakuu haaraa
maqaa sadiin waamti-
1. Taabota kakuu/waadaa/,
2. Tsillaatii fi
3. Teessoo Aarsaa/መሠዊያ/ jechuun.
Taabota kakuu kan jedhamu Waaqayyo
Israa’eloota wajjin kakuu duraan galeef osoo
hin taane ‹‹Foon koo kan nyaate dhiiga koos
kan dhuge jireenya baraa baraa qaba›
jedhamee isa kennameefi ‹sababa Cubuu
Namoota hedduuf kan dhangala’u Dhiigni koo
kakuu haaraa kana dha› jedhee Gooftaan
keenya kan kenne kan kakuu haaraa ti. (Maat
26:26-30) Kanaaf Taabota kakuu kan
jedhamu Fooniif dhiiga gooftaan kan
kenname kan kakuu haaraa ti.Taabota
jedhamuun isaammoo waaqayyo Araaraan
kan irra bulu, Fooniif dhiiga isaan immoo
qaamaan kan itti mul’atu Teessoo ufinaa
waan ta’eefi dha.
Tsillatii/Gabatee/ kan jedhamu Abboommiin
kurnan irratti waan barreeffameef miti.
Raawwataa seerota hundaa kan ta’e
Fayyisaan addunyaa kirisroos ‹Aalfaa fi
Oomeegaa› kan jedhu maqaansaa
kabajamaan Taboticharratti waan
barreeffameefi. (Sirna mana kiristaanaa/
hangafa lubootaa Kinfe Gebri’el Altayyee/,
Seenaa mana kiristaanaa/ Abbaa
Gorgooriyoos hagafa phaaphaasii shawaa/).
Namootni tokko tokko ‹‹Taabotni mana
kiristaanaa Itoophiyaa kan Ooriitii waliin wal
hin fakkatu!›› jedhanii akka mormii guddaa
yoo kaasan baay’ee ajaa’iba. Altokko “Kan
Ooriitii duuka buuti’’ si’a tokkommoo
‘’maaliif Akka ooriitii hin taane’’ jedhanii
mormuun bitaa galchuu dha.Kan Ooriitii kan
inni hin fakkaanne amma kan jirru kakuu
haaraa keessa fi tajaajilli taabotaas adda
waan ta’eefi dha. Taabotni kakuu haaraa
tabotaa tokkoon duraaniirra kan baay’ates
hundumaaf qaqqabuu kan qabu fooniif dhiigni
gooftaa kan itti qoqqoodamu Teessoo Aarsaa
waan ta’eefi. Dukkanni qorichaa kan baay’atu
Namootni qoricha barbaadan waan
baay’ataniif mitiiree? Taabitni kan baay’ates
Aarsaan aarsamu sababa cubbuu hunda
keenyaa kan dhangala’aee fi cubbuu
hundarraa kan qulqulleessu isa malees
jireenya hin qabdan kan jedhamne Fooniif I
dhiigni gooftaa cuubbuun kan dhukkubsataniif
waan nu barbaachisuu fi dha.
Abban gorgooriyoos akkas jechuun ibsu
‹‹Tsillaatiin ooriitii Waaqayyo duumessa
uffateemuseefi Aarooniin kan dubbate
israa’eloota qofaaf Araaraan teessoo itti
mul’ate dha. Kun garuu (kan kakuu haaraa)
Fooniif dhiigni gooftaa kan itti qoqqoodamu
foon kook an nyaate dhiiga koos kan dhuge
jireenya baraa baraa qaba foon koo nyaadhaa
dhiiga koos dhugaa jechuun kanneen amanan
kan itti waamu Teessoo aarsaa araaraa ti.
Kabajniifi sagadnis kan taasifamuuf kanaafi.
›› (Seenaa mana kiristaanaa itoophiyaa
fuula109). Kan baay’ee nama dinqisiisu biroo
Abbaan Gorgooriyoos Sirna Taabotaan
Giriikota Indimisiyoonota wajjin akka wal
fakkaannu tuquun yoo barreessan
Giriikotnimmoo waa’ee Andimiisiyoonotaa
yoo ibsan Taabota Itoophiyaa waliin kan wal
fakkatu jedhanii barreessuu isaani ti.
Sirna Mana kiristaanaa Itoophiyatti taabotota
hundarratti kan barreeffamu ‹‹Aalfaa fi
Oomeegaa›› kan jedhu maqaa fayyisaa
Addunyaa Kiristtosiiti. Maqaa isaa waliin
tabotoota hundarratti caqasa ‹‹ከመ ለስሙ
ለኢየሱስ ክርስቶስ ይስግድ ኲሉ ብርክ ዘበሰማያት
ወዘበምድር›› ‹‹kunis samii fi lafa lafaa gadi kan
jiran hundumtuu maqaa iyyesuusiif haa
jilbeenffatan›› kan jedhu dha. (Fil 2፡10)
Taabota fuuldurattis namni jilbeenfatu maaliif
akka sagadu taboticharratti kan barreeffame
jechi kun ni ibsa. Sababni isaa ‹‹humni jilbi
hundi Iyyesuusiif akka jilbeenfatu›› kan ta’uu
fi dha. Foonsaa akka kutamu dhiigni isaas
akka dhangala’u namni amanu hunduu
Aarsaa kana fuulduruatti sodaan kiristoosiif
sagada. « Fooniif dhiiga isaas yaaddannoo
qofaa dha» namni jedhu garuu Aarsaa kana
fuulduratti akka sagaduu fi Aarsaa kanas
akka kabaju hin eegnu. Maqaa Iyyesuus
Kiristoos Taabota isheerratti barreessitee
kabaja kan kennituuf Ijoollee mana
kiristaanaa kakuu haaraa waan taaneef
waaqayoon ni galateeffanna.
Maqaan Taabota biroo Taabota Aarsaa kan
jedhu yoo ta’u waa’ee meeshaa aarsaa
kanaa qulqulluun phaawuloos «Aarsaa qabna
Dunkaanattii keessatti kan tajaajilanis
isarraanyaachuuf mirga hin qaban» jechuun
waa’ee Teessoo Aarsaa kakuu haaraa nutti
hima. (Ibr.13:10) Teessoon Aarsaa kun
dunkaana Ooriitii kan tajaajilan ijoolleen
Aaroon isarraa nyaachuuf mirga kan hin
qabne Nuti kiristaanota qofaaf fooniif dhiiga
gooftaa Teessoo Aarsaa kanarra jiru akka
nyaannuuf kan nuuf kenname Taabota Aarsaa
((Christian Alter) dha.
Waa’ee Tajaajila Taabotaa kakuu haaraa
keessaa yommuu dubbannu namootni tokko
tokko gaaffii isaan kaasan keessaa « Taabota
kan qabdu mana kiristaanaa Itoophiyaa qofaa
dha» jechuun gargar baasuuf carraaqqii
taasifamu dha. Keessumattuu «Gibxiin/
Misirri/ Taabota hin qaban» kan jedhu yeroo
baay’ee kan dhaga’amuu dha. Dubbii
kanarratti nuti deebii kennuurra deebii
Gibtsoota mataa isaanii yoo keenye caala ifa
ta’a. Gibtsootni mana kiristaanaa Taabota
Itoophiyaa wajjin meeshaa qulqulluu lama
qabdi. Tokkoffaan tsillatii/Alter board/ yoo
ta’u lammaffaan taabota/Ark/ dha. Lubni
Taadiroos Maalatii kan jedhaman barreessaa
beekamaan mana kiristaanichaa ‹‹Church
The House of God›› kitaabasaa jedhamurratti
waa’ee haala hojii gabatee Aarsaa (Alter
Board) yommuu dubbatan ‹‹Tsillaatiin Aarsaa
kun fannoo tokko yookaan baay’ee irratti
kaafama, Aalfaa fi Oomeegaa jedhamees
irratti barreeffama, sana booda Faar.86:1
irratti Hundeen ishee Tabboota eebbifamoo
dha jechi jedhu irratti barreeffama. Erga
jedhaniin booda waa’ee hojii isaa yommuu
dubbatan ‹‹manni kiristaanaa Gibtsii
Teessoon Aarsaa meeshaan inni itti
hojjatamu seerri kaa’ame hin jiru, hanga
jaarraa 4ffaa tti muka qofarraa hojetamaa
ture dhagaa gati jabeessa/ዕብነ በረድ/ fi
dhagaa irraas hojjatamuu danda’a››. erga
kana jedhanii booda waa’ee Taabota Aarsaa
mana kiristaanaa Itoophiyaa yoo dubbatan «
muka irraa kan hojjatamu taabotni aarsaa
mana kiristaanaa itoophiyaa keessatti
tajaajila keenuun akka itti fufetti jira» jechuun
guduunfu.
Kun waa’ee Teessoo Aarsaa/መሠዊያ/ malee
waa’ee taabotaa hin dubbatu waa’ee
taabotaaa Barreessaan kun mana
kiristaanaattii wwebsaayitii oofiiseelaawwii
irratti kan armaan gadii barreessaniiru.
‹‹In the middle of the Alter, there is a wooden
box, called in Coptic 'pi totc' which means 'a
seat' or 'a throne', and is used as a Chalice-
Stand. Usually it is cubicle in shape, about
thirty centimetres high and twenty-five
centimetres wide, the top is closed with high
flaps. The beautiful carving is inlaid with
ebony and ivory and is decorated with four
small icons. It can be only the Lord in the
last supper, St Mary, Archangel Michael, St.
Mark and then the patron Saints.
It is called 'the Throne' for it represents the
presence of the Crucified Lord. Its name also
corresponds to the 'Ark of the Old
Testament', for it contained the Tablets of
Law written with the finger of God to declare
God's covenant with man. The new Ark now
contains the true Blood of Christ, as the New
covenant, that fulfils the Law and the
prophets.››
Teessoo Aarsaa giduutti saanduqa mukaatu
jira Kun koptic/Gibtsiitti Tiitoot jedhamuun
beekama hiikni isaas Barcuma/‹መንበር›
yookaan Teessoo ulfinaa jedhama. Xoofoon/
ጽዋ/ kan dhaabbatus achirra dha. Bocni
isaas kan naanna’e yoo ta’u saantimeetira
13/25 dha. Irra keessi isaa carqiidhaan
kafanama. Halluu gurraachaaf adiin kan
bareedee yoo ta’u suuraa afur naannoo
isaarra taasifama. Suuraawwan kunneenis;
Gooftaa keenya guyyaa kamisaa galgala
duuka buutota isaa waliin, kan Giiftii keenya
drbee Maariyaamii, kan Qulqulluu mikaa’elii
fi suuraa Qulqulluu yaadannoon taasifamuuf
ti.
‹Teessoo› jedhamee kan waamamu Gooftaan
Fannifame akka irra bulu yaaduudhaani.
Maqaan kunis kan kakuu moofaa waliin kan
wal fakkaatu dha. Taabotni sun kakuu
Waaqayyo Uumata isaa waliin seene kan itti
barreeffame tsillaatii seeraa ti. Taabotni
haaraan amma jiru garuu dhiiga kiristoos isa
dugaa kan qabe yoo ta’u kiristoosis seeraaf
raajota raawwatee kakuu haaraa kan nuuf
kennee dha) http://www.stmarkdc.org/
coptic-sanctuary ibsi kun Abbaan
Gorgooriyoos waa’ee taabota mana
kiristaanaa keenya ibsa isaan kennan irraa
tasa gargar hin ba’u. kana akka
fakkeenyaatti kaafne malee tabotichi
naanna’uu dhiisuu fi sirna isaan gargari
malee mana kiristaanaa itiyoophiyaatti
Fooniif dhiiga gooftaatiif teessoo aarsaati
jettee kan kabajju taabotaa wajjin kabajaanf
tajaajilaan qixa kan ta’an dibata meerooniin
kan kabajamaniifi Teessoorra kan taa’an
meeshaalee qulqullaa’oon mana kiristaanota
hunda jira.
Jabana kanatti dhugummaa dhiigaaf fooniitti
kanneen hin amanne waliin waa’ee
barbaachisummaa Teessoo Aarsaa mormuun
yeroo baay’een yoo barbadaa’u mul’ata.
Maqaan Iyesuus kiristoos kan itti barreefame
taabotaan ‹Xaa’ota› kan jedhan
‹kiristaanota› ilaalaa ajaa’ibsiifanna. xaa’otni
‹‹Humni/Jilbi hundi maqaa Iyyesuus
kiristoosiif haa jilbeenfatu›› jedhamee itti
barreeffame akkamitti jiraachuu danda’a?
‹‹Aalfaa fi oomeegaa›› xaa’oti jedhu jira?
Taabotni Wangeelli irra kan kaa’amu, dibata
meerooniin kan ulfaateef kabajame, fooniif
dhiigni gooftaa kan irratti qoqqoodamu
akkamitti Xaa’otii jedhamee waamama?
Waaqni Abbaan tokkichi qulqulluu dha
waaqni ilmaa tokkichi qulqulluu dha waaqni
afuura qulqulluu tokkichis qulqulluu dha
jechuun maqaan Sillaasee ittiwaamamee
sirna qulquleessaa kan irratti geggeeffamuun
waaqeffanaa Ormaati jedhaniiija jabaachuun
akkam nama naasisaree? Namni tokko tokko
taabotni hatamee gurgurame oduuwwan
jedhan yommuu afarsamanitti taabotni huna
hin qabu jechuu yaalu. Mqaan kiristoos kan
irratti abrreeffame Taabota dhiisnaan
Kiristoos mataan isaa qarshii soddomatti
gurguramee jira mitii? Liixoosxiraa hanga
qaraani’oo itti tufamaa, reebamaa, lafarra
harkifamaa fannifamee jira mitiree? Kanaaf
Galatniif ulfinni isaaf haa ta’uutii human
dhabeeti jechuu dandeenyaaree? Taaboticha
mul’isne agarsiisna jechuun kan dubbatan
mana kiristaanaa gad kan godhan itti
fakkaatee, mana kiristaanaa taabotichaan
waaqayyon kan waaqeffattu taabota
waaqeffattu jechuun waan isheen hin jenne
jetteetti jechuun kan dirqisiisuu yaalan
yommuu agarru gaddaan laphee keenya
cabsuu malee maal jenna? Manni kiristaanaa
taabota kan uwwistu kabaja Fooniif dhiigni
gooftaatiif malee kan isheen itti leeyyaatu
jiraatee miti. Yoo mul’ates maqaa fayyisaa
addunyaa Iyyesuus kiristoos, maqaa
qulqullootaa malee wanti biraa hin jiru.
Manni kiristaanaa Gooftaan ishee qullaa isaa
fannoorra yommuu oolu kan itti hin leeyyofne
maqaan isaa kan itti barreeffame taabotatti
hin leeyyoftu!
Barreessaan:- Dn Heenook Hayilee
Kan hiike :- Dn Daanyee Zarfuu

30/07/2017

"ጥቅስ ብቻ ስጠኝ" ፍጥጫ!!!!!!!
በኦርቶዶክስ ተዋህዶ አላፍርም የሚል!!
#ፕሮቴስታንቱ-- ቆይ ግን ታቦት ምንድን ነው? ጥቅስ ብቻ ስጠኝ ለእያንዳንዱ
መልስህ?
#ኦርቶዶክሱ-- ታቦት ማለት ቤተ ሀደረ ከሚለው ከግዕዝ ቃል የወጣ ሲሆን
"ማደሪያ" ማለት ነው። የምን ማደሪያ? ካልከኝ የቃሉ ማደሪያ ኦ.ዘፀ 25፥22
#ፕሮቴስታንቱ--እና ድሮ ለቃሉ ማደሪያ ነበር፥ አሁን በአዲስ ኪዳን ለምን አስፈለገ?
#ኦርቶዶክሱ-- በአዲስ ኪዳን የጌታችን ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ይፈተትበታል (በዮሐ.ወ 6፥54) የምታገኘው ይህ ሥጋውና ደሙ የምከብርበት ዙፋን ነው።
#ፕሮቴስታንቱ - ታቦት ጣኦት ነው እግዚአብሔር ከእኔ በቀር የተቀረፀ ምስል ለራስህ አታድርግ አላለም ወይ?
#ኦርቶዶክሱ - ታቦት ጣኦት ነው ካልክ ታቦትን ቀርፆ ለሙሴ የሰጠው
እግዚአብሔር ነውኮ ኦ.ዘፀ 32፥16 እና እግዚአብሔር ከእኔ በቀር ሌላ
የተቀረፀ ምስል ለራስህ አታድርግ እያለ ለምን ቀርፆ ሰጠዉ?
#ፕሮቴስታንቱ -- ለሙሴ የሰጠው ታቦት ወድቆ ተሰብሯል።
#ኦርቶዶክሱ -- አወ እውነት ነው ነገር ግን እግዚአብሔር እንደገና ሙሴ
እንዲቀርፅ አዞታል። ኦ.ዘፀ 34፥1
#ፕሮቴስታንቱ -- እሽ ይሁንና ሙሴ የቀረፀው ሁለት ብቻ ነው ይህ ሁሉ ከየት
መጣ??
#ኦርቶዶክሱ -- ከሙሴ ቀጥሎ ያሉት ቅዱሳን አባቶች እንዲቀርፁ ስልጣን
ተሰጣቸው ኦ.ዘፀ 31፥1-6 እንዲሁም ባሰልኤም ታቦትን ቀርጿል ኤ.ዘፀ
37፥1።
#ፕሮቴስታንቱ -- እሽ ይሁንና ለምን በቅዱሳን ስም ይቀረፃል?
ኦርቶዶክሱ -- የመታሰብያ ስም እስከተሰጣቸው ድረስ ት.ኢሳ 56፥4
ይቀረፅላቸዋል ነገር ግን በታቦቱ ላይ የሚከብረው የጌታችን ሥጋውና ደሙ
ነው።
#ፕሮቴስታንቱ -- እኔ አሁንም ያልገባኝ ታድያ ለምን በየሀገሩ በየአህጉሩ ታቦት በዛ
ከቅዱሳኑ ቁጥርምኮ ይበዛል?
#ኦርቶዶክሱ -- መልስ ሳልሰጥህ በፊት ጥያቄ አለኝ? መጽሐፍ ቅዱስ ሲታተም
1 ነበር አይደል? ታድያ አሁን በእያንዳንዳችን እጅ ላይ የሚገኘው ከየት መቶ
ነው?
#ፕሮቴስታንቱ -- ያው ተባዝቶ ስለታተመ ነዋ፡፡
#ኦርቶዶክሱ -- ታቦቱም እንዲሁ ለአገልግሎት እንዲመች በየስፍራው አለ! ይህ
ለምን ይሆናል ካልከኝ ት.ሚልክ 1፥11 ተመልከት። ደግሞም በአዲስ ኪዳን
እግዚአብሔር ለሰዎች ቅርብ አምላክ ነውና ነው ት.ኤር 23፥23።
#ፕሮቴስታንቱ -- ለምን በታቦቱ ላይ የቅዱሳን ስም ይፃፋል?
#ኦርቶዶክሱ -- በታቦቱ ላይ ብቻ አይደለም በሰማይ ቤትም ተፅፎላቸዋል፥ ሉቃስ
10፥20።
#ፕሮቴስታንቱ -- ታቦት በአዲስ ኪዳንኮ ተሽሯል አያስፈልግም
#ኦርቶዶክሱ-- ማነው የሻረው? ጌታ በማቴ 5፥17 ላይ ምን ነበር ያለው? ህግንና
ነብያትን ልሽር አልመጣሁም ልፈፅማቸው ነው እንጅ አላለም ወይ?
#ጴንጠው - እናንተ ኦርቶዶክሶች ብቻ አከረራችሁት እንጅ ታቦት የሚባል ነገር
መኖር የለበትም።
#ኦርቶዶክሱ-- አይደለም በምድር ላይ አይደለም በኦርቶዶክሶች መቅደስ
ውስጥ በሰማይምኮ አለ ታቦት። ነገ እዛ ስትሄድም ይጠብቅሃል ራእይ 11፥19
ይህንንም ሲያመለክት ነው ቅዱስ ጳውሎስ ሀገራችን በሰማይ ነው እያለ 2ኛ
ቆሮ 5፥1-5 የተናገረው።
#ፕሮቴስታንቱ -- እሽ ሁሉም እንዳለ ሆኖ ለምንድን ነው እሽ ታቦት ሲሰረቅ ዝም
የሚለው ሃይል የለውምኮ ሌባ ሰረቀው ምናምን ሲባል እሰማለው የሰረቀው
ሌባም ሲሸጠው ታቦቱ ታምራትን እንኳን አያደርግም።
#ኦርቶዶክሱ -- ገና አሁን ምርጥ ጥያቄ ጠየከኝ!! ለመሆኑ ታቦት ይበልጣል
ወይስ ኢየሱስ ክርስቶስ ይበልጣል?? ታቦት ማለት የቃሉ ማደሪያ ነው፤
ኢየሱስ ክርስቶስ ደሞ እራሱ የታቦቱ ባለቤት ነው። እስቲ ንገረኝ?
#ፕሮቴስታንቱ -- መብለጡንማ ኢየሱስ ነው

27/07/2017

+++ ክንፍ ከሌላቸው መላእክት ጋር የተደረገ ቆይታ +++

በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ቆይታዬ እጅግ ከማልረሳቸው ውብ ጊዜዎች መካከል አንዱ ከሕጻናት ጋር ያሳለፍኩት ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሕጻን ቅንና ንጹሕ መሆኑ በሚያደርገው ሥራ ይታወቃል›› ብሎ ጠቢቡ ሰሎሞን የመሰከረላቸው ሕጻናት በየዋህነታቸው ፣ በማያልቁ ጥያቄዎቻቸውና ፍቅርን በተሞላ ወዳጅነታቸው ‹ምነው ሕጻን ሆኖ መቅረት ቢቻል› ያስብላሉ፡፡ (ምሳ.20፡11) ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹ልጆችህ የአንተ እንዲሆኑ ከፈለግህ ለእግዚአብሔር ሥጣቸው› በማለት እንደተናገረ ልጆቻችንን የእኛ ለማድረግ ስንል ልንወስነው የሚገባን ውሳኔ በእግዚአብሔር ቤት እንዲያድጉ ማድረግ ነው፡፡ ሕጻናት እግዚአብሔርን በመፍራት ካደጉ እንደ ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ ለወላጆቻቸው የሚጸልዩና ከራሳቸው አልፈው እናት አባታቸውን ከክህደት የሚያድኑ ይሆናሉ፡፡

አንዳንድ ወላጆች እነርሱ ወደ ቤተ ክርስቲያን እየሔዱ ፣ እየጾሙ እየጸለዩ ልጆቻቸውን ግን ከቤት የሚያስቀሩ ‹እኔ ከጾምኩልህ ከጾምኩልሽ ይበቃል› የሚሉ አሉ፡፡ እግዚአብሔር ግን ወላጆችንም ብቻ ሳይሆን ልጆችንም ይፈልጋል፡፡ ‹አህያይቱን ከውርንጫይቱ ጋር አምጡልኝ ፤ ማንም አንዳች ቢላችሁ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉ› ብሎ የለምን? አህያና ውርንጭላስ እናትና ልጅ አይደሉም? ስለዚህ ወላጆች ልጆቻቸው ለጌታ እንደሚያስፈልጉት ማወቅ አለባቸው፡፡

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ለሕጻናት ያላት ፍቅር ሕጻናትን ገና በልጅነታቸው ከማጥመቅ ይጀምራል፡፡ ምንም እንኳን ለመጠመቅ ማመን የሚያስፈልግ ቢሆንም ሕጻናትን ግን ‹ተዉአቸው ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው› ያለውን ይዛ ሕጻናትን በጥምቀት ትቀበላቸዋለች፡፡ ለዚህም ምክንያቷ ቅዱስ ጴጥሮስ ‹ተጠመቁ ፤ የመንፈስ ቅዱስን ሥጦታ ትቀበላላችሁ› ብሎ ለሦስት ሺህ ሰው ባስተማረበት ጊዜ ‹የተስፋው ቃል ለእናንተና ለልጆቻችሁ ጌታ አምላካችንም ወደ እርሱ ለሚጠራቸው በሩቅ ላሉት ሁሉ ነውና› ብሎ እንደተናገረው በጥምቀት የሚገኘው የመንግሥተ ሰማያት ተስፋ ‹ለልጆችም› ስለሆነ ነው፡፡ (ሐዋ. 2፡38-39)

አንዳንድ ሰዎች ሕጻናትን ‹ሳያውቁ አይጠመቁም› ብለው ይከለክላሉ ፤ ‹ልጄ አድጎ እስኪገባው ድረስ አይጠመቅም› የሚሉም አሉ፡፡ ስለ ምሳሌው ይቅርታና በዚህ አስተሳሰብ ከሔድን የአእምሮ ሕመም ያለበት ሰውስ መረዳት ስለማይችል አይጠመቅም ማለት ነው? ይህ ደግሞ ‹የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው› ላለው ርኅሩኅ ጌታ የማያውቁትን ባለማወቃቸው ይፈርድባቸዋል እንደማለት ነው፡፡ የሚገርመው ጥምቀት ሲሆን ‹ልጄ አውቆ ካልሆነ አይጠመቅም› የሚሉ ሰዎች ምግብን ፣ ልብስን ፣ ክትባትን ‹ልጄ አድጎ አውቆ ይብላ ፣ ይልበስ ፣ ይከተብ› አይሉም፡፡ ለልጃቸው ይበጃል ያሉትን በራሳቸው ውሳኔ ያደርጉለታል፡፡ የጥምቀት ዋጋው ደግሞ ከምግብ፣ ከልብስና ከክትባት በላይ ነው፡፡ እንዲሁም አንድ ልጅ ወላጆቹ ንብረታቸውን ትተው በሕጻንነቱ በሞት ቢለዩት የወላጆቹ ሀብት እንዳያመልጠው በሞግዚትም ቢሆን የወራሽነት መብቱ ይረጋገጣል፡፡ ሰማያዊ ርስት መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ ሲሆን ግን ቆይ ሲገባው ሊሉ ይሞክራሉ፡፡ ያም ሆነ ይህ ሐዋርያት በተደጋጋሚ ‹ከነቤተሰብ› ያጠምቁ እንደነበር ቤተ ክርስቲያናችን ሕጻናትን እንደ ሐዋርያት ከቤተሰብ ሳትነጥል በማጥመቅ ትቀበላቸዋለች፡፡

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ከዚህ ባሻገር በሕጻን አንደበት በአግባቡ ሲዜም በሚማርከው ዜማዋ ፣ ደማቅ በሆነው ሥርዓተ አምልኮዋ ፣ በአልባሳትዋ ፣ በዝማሬ ሥርዓትዋ ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ክስተቶችን ከመተረክ አልፋ በተግባር በምትፈጽምባቸው ደማቅ የአደባባይ በዓላትዋ ፣ ቤተ መቅደሱን በሞሉት የቅዱሳት ሥዕላት ሀብቷ ለዚህ ዓለም ገና አዲስ እንግዳ የሆኑ ሕጻናትን ልብ ከማንም በላይ ልትማርክ የምትችል ያደርጋታል፡፡ ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ልጅን ወስዶ መሥጠትና ጾምና ጸሎትን ፣ በሌሊት ተነሥቶ ማስቀደስን ፣ በካህናት ምክር መመራትን ፣ ፍቅረ ቤተ ክርስቲያንን አውቆ እንዲያድግ ማድረግ ወላጆች ለልጃቸው የሚያበረክቱት የመጨረሻ ሥጦታ ሲሆን ልጅም ካደገ በኋላ ወላጆቹን እያመሰገነ እንዲኖር የሚያደርግ ነው፡፡

የቅዱሳንን ሕይወት በቤተ ክርስቲያን ሲማር ፣ በመጻሕፍት ሲያነብና በመንፈሳዊ ፊልም ሲመለከት ያደገ ሕጻን ቅዱሳኑንን እንደ አርኣያ አድርጎ ስለሚያስብ በሕይወቱ ላይ በጎ ተጽዕኖ አርፎበት ያድጋል፡፡ በአንድ ወቅት በአንድ መንፈሳዊ መጽሔት ላይ (St. John ወይም Mighty Arrow ይመስለኛል፡፡) የአንድ ሕጻን ልጅ ፎቶ ተመልክቼ ነበር፡፡ ሕጻኑ በሚማርበት ትምህርት ቤት ሕጻናቱ ‹ጀግናዬ› (My Hero) የሚሉትን ሰው ዓይነት ልብስ ለብሰው እንዲመጡ ታዝዘው ነበር፡፡ አብዛኛዎቹ የክፍል ጓደኞቹ በፊልሞች ላይ የተመለከቷቸውን እንደ ስፓይደር ማን ፣ አይረን ማን ወዘተ ገጸ ባሕርያት ልብስ ለብሰው ሲመጡ ከኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ውስጥ ያደገው ሕጻን ግን የሚወደውንና ሥዕሉን ዘወትር የሚያየውን የክርስቶስ ምስክር የሕጻኑን ቅዱስ ሚናስን ዓይነት ልብስ ለብሶ ‹የእኔ ጀግና (My Super Hero) ቅዱስ ሚናስ ነው› ብሎ የሚናስን ታሪክ ለክፍል ጓደኞቹ ተረከላቸው፡፡ ልክ ነው ቅዱስ ጳውሎስ ‹እንደ ደመና የከበቡን ምስክሮች› ያላቸው ቅዱሳን የእኛ ጀግኖቻችን ናቸው፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ ሕጻናትን በማስተማር በኩል የአብነት ትምህርት ቤቶች የመጀመሪያውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ ትናንት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለመማር ከወላጆቻቸው በሕጻንነት ተነጥለው ያደጉ ሕጻናት የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያናችን አባቶች ናቸው፡፡ የቅዱስ ያሬድን ዜማ ፣ ቅኔና የቅዱሳት መጻሕፍትን ትምህርት ለመማር ከቤት ወጥተው አውሬ በልቷቸው ፣ ወራጅ ውኃ ወስዷቸው ፣ በረሃብ ተሰቃይተው በልጅነታቸው የሞቱ ብዙ ሕጻናትም በቤተ ክርስቲያን ታሪክ አሉ፡፡ ለዚህም ነው ሊቃውንት ‹በሔሮድስ ምክንያት ከሞቱት ሕጻናት በቅዱስ ያሬድ ምክንያት የሞቱት ሕጻናት ይበልጣሉ› ሲሉ የምንሰማው፡፡ ከአብነት ትምህርት ቤት በኋላ ደግሞ የሕጻናትን ጉዳይ ተረክቦ ከዳር እያደረሰ ያለው የቤተ ክርስቲያናችን ወሳኝ ተቋም ደግሞ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው፡፡ እንደሌሎች አብያተ ክርስቲያናት በሊቀ ጳጳስ ደረጃ ተቋቁሞለት የራሱ ማተሚያ ቤትና የፊልም ኢንዱስትሪ ተዘጋጅቶለት የሚሠራበትን ቀን ደግሞ በተስፋ እንጠብቃለን፡፡
ባለንበት ዘመን ዓለም ካለችበት የተበላሸ ሁኔታ አንጻር ልጆችን በሃይማኖት መንገድ ማሳደግ ለወላጆች እጅግ ፈተና የሆነበት ዘመን ነው፡፡ ስለዚህ ትናንት ከተሔደበት መንገድ በተሻለ ዘመኑን በዋጀ መንገድ ሕጻናትን መያዝ እንደሚገባ፡፡ በየትኛው ሀገርና በየትኛውም የኢኮኖሚ ደረጃ ቢኖሩ ሁሉም ሕጻናት አንድ ናቸው፡፡ በጥያቄዎች የተሞሉ ፣ ብሩሕ አእምሮ ያላቸው ፣ ያዩትን ከመናገር ወደ ኋላ የማይሉ ፣ የማያስመስሉ እኛ ካላሳየናቸው የማይዋሹ ንጹሐን ፍጥረታት ናቸው፡፡ ያለንበት ዘመን ከትናንቱ ፈጽሞ የተለየ ስለሆነ የልጆችን ጥያቄ እንደትናንቱ ‹ዞር በል ከፊቴ! ውሪ ሁላ!› ብሎ መገላገል አይቻልም፡፡

ለልጆች ጆሮ ሠጥተን ከሰማናቸው ለእኛ የሚተርፍ ቁምነገርም ከጣፋጭ አንደበታቸው ይሰማል፡፡ ፓትርያርክ ታዋድሮስ በአንድ ትምህርት ላይ ስለ አንዲት ሕጻን ብሩሕ አእምሮ ሲናገሩ ያሉት እዚህ ላይ ትዝ አለኝ፡፡ ሕጻናት ለወደፊቱ በትምህርታቸው ትልቅ ደረጃ ሲደርሱ ለዓለም ምን አዲስ ግኝት መፈልሰፍ እንደሚፈልጉ ተጠየቁ፡፡ አንዷ ሕጻን ተነሥታ ‹‹እኔ አድጌ ሳይንቲስት ስሆን መፍጠር የምፈልገው ሕልምን ቀርጾ የሚያስቀምጥ (Record የሚያደርግ) ትራስ ነው›› አለች፡፡ ይደንቃል ፤ ሕጻናት ሁልጊዜም የአዲስ ነገር ምንጮች ናቸው ፤ መቼም ትራሱ በሰው ኅሊና ከታሰበ መፈጠሩ አይቀርም፡፡
ይህንን መግቢያው የበዛ ጽሑፍ ድንገት ለመጻፍም የተነሣሁት በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ወቅት ያጋጠሙኝን ጥቂት የሕጻናት ጥያቄዎች ላካፍላችሁ ነው፡፡ ወላጆች የልጆቻቸውን የጥያቄ ዝናም መግታት የሚችሉት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲልኳቸው መሆኑን በማመን ወደ እኛ የሚልኳቸው ሕጻናት የሚጠይቁት ጥያቄ ተጠያቂውን የሚያስደነግጥ የሚያስደንቅ መሆኑ የተለመደ ነው፡፡ ሀገር ቤት ያሉት ሕጻናት በሰንበት ትምህርት ቤት እስካሳደግናቸው ድረስ በብዙ መልኩ ጥያቄዎቻቸው ተመልሰውላቸው ያድጋሉ፡፡ ከሀገር ውጪ በሰው ሀገር ቋንቋ አፋቸውን የሚፈቱ ሕጻናት ግን ስለ ሃይማኖታቸው ለማወቅ ያለባቸው ፈተና ሊታሰብብበት የሚገባ ከባድ ነገር ነው፡፡

መጀመሪያ በኅሊናዬ የመጣችው ሕጻን የዐሥራ ሁለት ዓመቷ ናኦሚ ናት፡፡ የዛሬ ሦስት ዓመት ገደማ ነበር እናቷን በጥያቄ አስጨንቃ የኖረችዋን ሕጻን ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘኋት፡፡ ጥያቄዋ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ነበር፡፡ ‹‹ጌታን ያጠመቀው መጥምቁ ዮሐንስ እንደሆነ አውቃለሁ ፤ መጥምቁ ዮሐንስን ማን አጠመቀው?›› የሚል ነበር፡፡
ደነገጥሁ! እስቲ ይኼን አሁን ማን ያስበዋል!? ደግነቱ አትዋረድ ሲለኝ ካሳደጉን አባት ከየኔታ ዘመንፈስ ሥር ቁጭ ብለን አሁንም ምስክር ሊሆኑ የሚችሉ ወንድሞቼ ጋር ስንማር ከእኛ ጀርባ ሲቀጽሉ የነበሩ ወንድሞች ደጋግመው ሲጮኋት ጆሮአችን ጥልቅ ያለች አንዲት ዜማ ትዝ አለችኝ፡፡ ‹አጥመቀ ወተጠመቀ ለሊከ!› (አጠመቅህ አንተም ተጠመቅህ!) ማለት ነው፡፡ ይህንን የቅዱስ ያሬድ ቃል ይዤ ‹ዮሐንስ ባጠመቀ ጊዜ ተጠምቋል› የሚል መልስ ለልጅቷ ሠጠኋት፡፡

በኋላ በጉዳዩ ላይ ሳነብና እነ የኔታ ምሥጢረን እነሊቀ ሊቃውንት ዕዝራንም ስጠያይቅ ሰፋ ያለ መልስ አገኘሁ፡፡ ቅዱስ ያሬድ ከዚህ በተጨማሪም ስለ ዮሐንስ ‹‹እምድኅረ አጥመቀ ለሊሁ ተጠምቀ›› (ካጠመቀ በኋላ ራሱም ተጠመቀ) ብሏል፡፡ ይሁንና የዮሐንስ መጠመቅ የበረከት ጥምቀት እንጂ የልጅነት ጥምቀት ገና በዚያ ጊዜ እንዳልተሠጠም ጨምረው ነገሩኝ፡፡ እንደዚያ ከሆነ ደግሞ ጌታችን ሁሉን ባዳነበት በዕለተ አርብ የተሠጠው ልጅነት ተካፋይ ሆኗል ማለት ነው፡፡ (ወመጠውኩዎሙ ዕዴየ ዘየማን ወኮነቶሙ ጥምቀተ እንዲል)

በሌላ ጊዜ ደግሞ አንዱ ሕጻን ‹በኖኅ ዘመን በጥፋት ውኃ ጊዜ እንስሳት ሁሉ ወደ መርከብ ሲገቡ ዓሣ ገብቶ ነበር ወይ?› አለኝ፡፡ ‹ገብቷል› ብለው እንዴት ውኃ በሌለበት ቆየ ሊለኝ ነው ፤ አልገባም ካልኩት ደግሞ ‹የንፍር ውኃ› ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ስለዚህ ቀጠሮ ሠጠሁ፡፡ በአጭሩ የዓሣ ዝርያ ወደ መርከቡ አልገባም፡፡ በጎርፍና በንፍር ውኃ ምክንያት ዓሣዎቹ ሊሞቱ ቢችሉም እንኳን እንቁላላቸው በዚያ ሁኔታ ሊቆይ እንደሚችል ሳይንሱም የሚደግፈው እውነታ ነው፡፡ ሌላዋ ሕጻን ደግሞ ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ብዙ ጥያቄዎች ጠይቀው ከተማሩ በኋላ ‹ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚሳሉት ቅዱሳት ሥዕላት ሲሣሉ ለምን ፈገግ ብለው አይሳሉም› ብላ ጠየቀች፡፡ ለጊዜው የሠጠኋት መልስ ‹‹በሥዕላት ፊት ጸሎት የሚያደርገው ሰው በኀዘን ወይም በመንፈሳዊ ስሜት ሆኖ በሚጸልይበት ጊዜ ሥዕላቱ በፈገግታ ወይም በመኮሳተር ቢሳሉ ጸሎቱን ሊያውኩ ስለሚችሉ ከስሜት ነጻ (Neutral) ሆነው ይሣላሉ›› የሚል ነበር፡፡ ጉዳዩ ግን ብዙ የተጻፈበት ርዕሰ ጉዳይ ነው፡፡

በደቡብ አፍሪካ ራስተንበርግ ከተማ ያገኘኋት ሕጻን ሳሮን ደግሞ ‹ኢትዮጵያ በጣም መጥፎ ሀገር ናት እኔ ኢትዮጵያ መኖር አልፈልግም!› አለችኝ፡፡ ፊቴ ተለዋወጠ ፤ በአርበኝነት ስሜት ለመከላከል ተነሣሁ፡፡ ‹እንዴት እንዲህ ትያለሽ?› አልኳት ቁጣዬን ዋጥ አድርጌ፡፡ ምንም ሳትረበሽ ቀጠለች ‹‹ከፈለግህ Google አድርግ ፤ ሕጻናትና ሴቶች በብዛት የሚደፈሩትና የሚጠለፉት በኢትዮጵያ ነው፡፡›› አለች በእርግጠኝነት፡፡ እኔ ግን እርስዋ ያለችውን ትቼ ኢትዮጵያን ለመከላከል ሞከርሁ፡፡ ‹‹ደቡብ አፍሪካ ቁጭ ብለሽ ኢትዮጵያን ትናገሪያታለሽ እንዴ? እንደ ደቡብ አፍሪካ ደግሞ ወንጀል ያበት ሀገር አለ እንዴ?›› አልኳት የሀገሬን ስም ለማስከበር እየተፍጨረጨርሁ፡፡ ሳሮን ግን አልተሸነፈችም ‹‹ልክ ነህ! ግን እኮ ደቡብ አፍሪካ ስሟ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ አንድም ጊዜ አልተጻፈም፡፡ ኢትዮጵያ ግን ብዙ ጊዜ ተጽፋለች!›› አለችኝ፡፡ ለዚህ ራስ የሚመታ ንግግር ከዝምታ በቀር ምን ልመልስ እችላለሁ?

ሕጻናቱ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት ብዙ ውብ ጥያቄዎች ያነሣሉ፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን የሚደረገው እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ታስቦበት የተደረገ ተምሳሌታዊ ትርጉም ያለው መሆኑ ደግሞ የሚያኮራ ነው፡፡ ሕጻናቱ በሃይማኖታቸውና በቤተ ክርስቲያናቸው እንዲኮሩ የሚያደርግ ነው፡፡ አንዳንድ ወላጆች ልጆቻቸውን የጠቀሙ እየመሰላቸው ልጆቻቸው እንዳይጾሙ ፣ ቅዳሴ ከረፈደ እንዲሔዱ ፣ ክርስትና ሲነሡ በፔርሙዝ በመጣ ሙቅ ውኃ እንዲጠመቁ ፣ በልተው እንዲቆርቡ ወዘተርፈ ሲያደርጉ አልፎ አልፎ ይታያል፡፡ ይህንን የወላጆች ቅጥ ያጣ አካሔድ ቆጣ ብሎ ማስቆም ከአባቶች የሚጠበቅ ቢሆንም በተለይ ከሀገር ውጪ ወላጆች ‹ብርዱን› ሲፈሩ ካህናቱ ‹ቦርዱን› እየፈሩ ሥርዓት ሲጣስ ዝም ብለው ለመመልከት ሲገደዱ ይታያል፡፡

ሥፍራውን መናገር ባያስፈልግም በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት እንዳይሔዱ ሆነው ያደጉ ሕጻናት የጾምን ፣ የጸሎትን ፣ የቅዳሴን ወዘተ ጥቅምና ትርጉምና ምንነት በአንድ ጃማይካዊ የኦርቶዶክስ ቄስ አማካይነት በቋንቋቸው ተምረው ሲገነዘቡ መረን የለቀቋቸውን ወላጆቻቸውንና በዚህ የተስማሙትን አገልጋዮች ጭምር ‹እንደዚህ እንደሆነ እስከዛሬ ለምን አልነገራችሁንም?› ብለው በጥያቄ አፋጥጠዋል፡፡ በሌላ ቦታ ደግሞ ሴት ልጅ በወር አበባ ጊዜ ወደ ቤተ መቅደስ የማትገባው ስለረከሰች ሳይሆን ‹በሐዲስ ኪዳን ቤተ መቅደስ ሊፈስስ የሚገባው ደም የመድኃኔዓለም ክርስቶስ ደም ብቻ መሆኑንና የፍጡራን ደም ሊፈስስበት ስለማይገባ ወንድም ሆነ ሴት ደም በሚፈስሰው ሰዓት ወደ ቤተ መቅደስ እንደማይገባ›› ሲማሩ ‹ምን ችግር አለው?› ሲሏቸው የኖሩ ሰዎች ላይ ወቀሳን አዝንመዋል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ለሕጻናት የሚሠጠው ቦታ ‹የነገ ተረካቢዎች› ብሎ ማሞገስ ከሆነ ፣ ለሴቶች በቤተ ክርስቲያን የሚሠጠው ድርሻ ‹እልልታ› ብቻ ከሆነ የምንኮራባት ቤተ ክርስቲያናችን ዘመኑን ለመዋጀት ትቸገራለች፡፡ በትምህርት ቤታቸው ቴአትርና ሙዚቃ ተለማምደው የሚያቀርቡ ሕጻናት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአግባቡ መዘመር እንኳን አለመቻላቸው ለጉዳዩ ትኩረት እንዳልተሠጠው የሚያሳይ ነው።

ስለዚህ ትናንት ከምንሠራው የተሻለ ሠርተን በልጅነታቸው በዘፈን ፈንታ የቤተ ክርስቲያንን ውብ ዜማን ፣ በልቶ ስብሐት ማለትን ፣ ጸሎት ማድረስን ፣ ቅዱሳት መጻሕፍት ማንበብንና በማለዳ ተግቶ ማስቀደስን ለልጆቻችን ካበረከትን እንደ ቅዱስ ቂርቆስ የእናታቸውን ቀሚስ ይዘው ‹ጌታ ሆይ እርሻውን አቃጥለህ ፍሬውን ብትባርክ ምን ይጠቅማል? ዛፉን አቃጥለህ ቅርንጫፉን ብትባርክ ምን ጥቅም አለበት? እባክህን የእናቴን ልብ አበርታ› ብለው የሚጸልዩ ቅዱሳንን እናፈራለን!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሐምሌ 19 2009 ዓ.ም.
ቩርዝቡርግ ፤ ጀርመን

31/03/2017

+++ የኒቆዲሞስ ክርስትና +++

ኒቆዲሞስ የሚለው ስም በዮሐንስ ወንጌል ብቻ ከተጻፉ ስሞች መካከል አንዱ ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ የዚህን ሰው ስም ባነሣበት ሥፍራ ሁሉ ‹አስቀድሞ በሌሊት የመጣው› የምትል ቅጽል ያስቀድማል፡፡ ይህ ሰው የአይሁድ አለቃ ነው፡፡ በሀብቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያለ ባለጸጋ ፣ በሹመቱ የአይሁድ ሸንጎ /synagogue/ አባል ፣ በትምህርቱ ደግሞ ጌታችን ራሱ እንደመሰከረለት ‹የእስራኤል መምህር› የሆነና አዋቂ ነው፡፡ የአይሁድ አለቃ ፣ የእስራኤል መምህር ኒቆዲሞስ ጌታችን ራሱ ለብቻቸው በቃል ምልልስ እያናገረ ጥያቄያቸውን እየመለሰ ካስተማራቸው ጥቂት ዕድለኛ ሰዎች አንዱም ነው፡፡ ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅነት ያገኘንበትን ምሥጢረ ጥምቀት በጥልቀት እና በዝርዝር የተማረው የመጀመሪያው ሰውም ኒቆዲሞስ ነው፡፡ መጥምቁ ዮሐንስ ጌታችን ጥምቀትን በተግባር ሲመሠርት የዓይን ምስክር እንደነበረ ሁሉ ጥምቀት በትምህርት ስትመሠረት ደግሞ የዓይን ምስክሩ ኒቆዲሞስ ነው፡፡

በትምህርቱ መካከልም ባቀረበው ጥያቄ ‹ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ ስለ መወለድ› ጌታችን በምሳሌ አድርጎ ያስተማረው ሲሆን አላምን ብሎ ‹እንዴት ሊሆን ይችላል?› ብሎ ሲከራከር ደግሞ ገሥጾታል፡፡ ዛሬም ድረስ ኒቆዲሞስ መልስ ከተሠጣቸው በኋላ የሚነታረኩ ተከራካሪዎች ምሳሌ ሆኖ በሊቃውንት ይጠቀሳል፡፡ እመቤታችን ድንግል ማርያምን የቅዱስ ገብርኤልን ብሥራት በሙሉ ልብ በመቀበሏ በምናመሰግናት ጊዜም ‹እንደ ዘካርያስ ሳትጠራጠሪ እንደ ኒቆዲሞስ ሳትከራከሪ ቃሉን የተቀበልሽ› እያልን መሆኑ ይህን እውነታ ያጎላዋል፡፡

ኒቆዲሞስ ወደ ክርስትና ከመጣበት መንገድ ጀምረን በዮሐንስ ወንጌል ስንከተለው ቀስ በቀስ እያደገ የመጣ የመንፈሳዊነት ደረጃን እናገኛለን፡፡ የኒቆዲሞስ ክርስትና እንደ ወጣኒ (ጀማሪ) እንደ ማዕከላዊና እንደ ፍጹም በሦስት ደረጃዎች ላይ የሚታይ ሕይወት ሆኖ በዮሐንስ ወንጌል ላይ ተመዝግቦ ይገኛል፡፡ እንደሚከተለው እንመልከተው፡፡

ወጣኒው (ጀማሪው) ኒቆዲሞስ

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፋሲካ በዓል በኢየሩሳሌም ሳለ ያደረገውን ተአምር ተመልክተው ብዙ ሰዎች በስሙ አምነው ነበር፡፡ ያ ወቅት ጌታችን በቃና ዘገሊላ ሠርግ ቤት ውኃን ወይን ያደረገበትና ፣ በቤተ መቅደስ ይሸጡ ይለውጡ የነበሩትን ገሥጾ ያስወጣበት ነበር፡፡ ይህንን ምልክት ተከትለው ካመኑበት ብዙ ሰዎች አንዱ ታዲያ ኒቆዲሞስ ነበር፡፡ ይህ ሰው በጌታችን ቢያምንም ባመነበት ወቅት እምነቱን በልቡ ብቻ ይዞ አቆይቶ ነበር፡፡ ከዚያም በአሳቻ ሰዓት በማታ ወደ ጌታችን መጣና ‹መምህር ሆይ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን› አለው፡፡ ኒቆዲሞስ ጌታችንን እግዚአብሔር በረድኤቱ ተአምራትን እንዲያደርጉ ከሚያስችላቸው ጻድቃን እና ነቢያት ለይቶ አላየውም ነበር፡፡ ንግግሩም ከእርሱ ጋር ምልክቱን አይተው አምነው ከነበሩት ሰዎች ቁጥር መሆኑን በሚያሳይ መንገድ ‹እናውቃለን› የሚል የብዙዎች ወኪልነት ንግግር ነበር፡፡ ከዚህ በኋላ ነበር እንግዲህ አምላካችን በዝርዝር ያስተማረው፡፡

ኒቆዲሞስን እንዲህ በሌሊት ያስመጣው ምንድር ነበር? ክርስቶስን በቀን በአደባባይ ሊያናግረው አይችልም ነበር? እሱ እንደሆነ በሔደበት መንገድ የሚለቀቅለት የአይሁድ አለቃ ነውና ጌታችንን ለማግኘት ሰዎች አገዱኝ ሊል አይችልም፡፡ ይህ እንግዲህ የኒቆዲሞስ የመጀመሪያው የክርስትና ደረጃ ነበር፡፡ እሱ አምላካችንን ስላደረገው ተአምር ሊያደንቀው ፈልጓል ‹እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው› ብሎ አመስግኖታል ፤ ሊከተለው ግን አልፈለገም፡፡ ሌላው ቀርቶ ከጌታችን ጋር ሆኖ ሰዎች እንዲያዩት አልፈለገም፡፡ የጌታ ተከታይ ፣ ደቀመዝሙር ሆኖ መታሰብ አልፈለገም ፣ ጉዳዩ ክብሩን የሚነካበት መሰለው፡፡ የተማረ ነውና ‹ገና ይማራል እንዴ› ብለው እንዳይንቁት ለክብሩ ሳሳ ፣ በዚያ ላይ ደግሞ ጌታችን በአይሁድ ሹማምንት ዓይን የተናቀ ነበር፡፡ እርሱ ‹ግንበኞች እንደናቁት ድንጋይ› ነበር፡፡ ‹‹የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።›› ይላል ነቢዩ፡፡ /ኢሳ. ፶፫፥፫/ ታዲያ የእርሱ ደቀ መዝሙር ሆኖ መታየት በዚያን ወቅት የሚያስከብር ነገር አልነበረም፡፡ ስለዚህ ፈራ ተባ እያለ በጨለማ መጣ፡፡

ወደ ክርስቲያናዊ ሕይወት የሚመጣ ሰው አንዱ ፈተናው ይኼ ነው፡፡ ክርስትናችን በሰዎች ፊት የታወቀ እንዲሆን ፈቃደኞች የማንሆን ብዙዎች ነን፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሰው ተብሎ ላለመታየት የሚሸሹ ብዙዎች ናቸው፡፡ ማዕተብ ማድረግ ፣ በቤተ ክርስቲያን አጠገብ ሲያልፉ መሳለም ፣ በአበው ትውፊት ጽዋዕ መጠጣት ወዘተ ማድረግ የሚከብዳቸው የሚጨነቁና የሚያፍሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ በሚሠሩበት መሥሪያ ቤት አካባቢ ስለ ሃይማኖታቸው ባይታወቅ የሚመርጡ፣ ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔዳቸው ባይሰማ ደስ የሚላቸው ኒቆዲሞሶች ብዙኃን ናቸው፡፡

የኒቆዲሞስ ችግር በክርስትናው ማፈሩ ብቻ አልነበረም፡፡ ክርስትና የሚያመጣበትን መዘዝ መፍራቱም ጭምር ነው፡፡ አይሁድ ‹‹እርሱ ክርስቶስ ነው ብሎ የሚመሰክር ቢኖር ከምኩራብ ይውጣ›› የሚል ስምምነት ላይ ደርሰው ነበር፡፡ (ዮሐ. ፱፥፳፪) በዚህ ሕግ ምክንያት በጌታችን አምነው እንኳን ስለ እርሱ ለመመስከር የሚፈሩ ብዙዎች ነበሩ፡፡ ‹‹ከዚህም ጋር ከአለቆች ደግሞ ብዙዎች በእርሱ አመኑ፤ ነገር ግን ከምኵራብ እንዳያስወጡአቸው በፈሪሳውያን ምክንያት አልመሰከሩለትም፤ ከእግዚአብሔር ክብር ይልቅ የሰውን ክብር ወደዋልና።›› (ዮሐ. ፲፪፥፵፪)

ኒቆዲሞስ ወደ ጌታ መጥቶ መማሩ እንዲታወቅ ያልፈለገውም ለዚህ ነበር፡፡ ለክርስትናው ምንም ዓይነት ዋጋ ለመክፈል ፈቃደኛ አልነበረም፡፡ ለማድነቅ እንጂ መከራን ለመቀበል አልተዘጋጀም፡፡ ይህ ዓይነቱ ችግር ሌላው የክርስቲያናዊ ሕይወት ፈተና ነው፡፡ ሐዋርያው የክርስትናችንን ዓላማ ሲገልጥ ‹‹ስለ እርሱ ደግሞ መከራን ልትቀበሉ እንጂ በእርሱ ልታምኑ ብቻ አይደለም፡፡›› ብሏል፡፡ (ፊል. ፩፥፳፱) ብዙዎቻችን ክርስትናችንን እንፈልገዋለን ፤ ሆኖም በክርስትናችን ምክንያት ቅንጣት መከራ እንኳን እንዲነካን አንፈልግም፡፡ በእግዚአብሔር በማመን ውስጥ ፈተናም አለ፡፡ ራሳችንን በእውነት ክርስቲያን ነኝ ብለን ለመጠየቅ ብንፈልግ አብረን መጠየቅ ያለብን በእውነት መከራ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ወይ ማለት ጋር ነው፡፡ በእግዚአብሔር በማመናችን ምክንያት ምን የከፈልነው ዋጋ አለ? ለእርሱ ብለን የተውነው ነገር ምንድን ነው? ለእሱስ ብለን ያጣነው ነገር ይኖር ይሆን? ምንም ነገር ከሌለ ክርስትናችን ገና ያልጠነከረ ነው ማለት ነው፡፡

ማዕከላዊው ኒቆዲሞስ

ፈሪሳዊያንና የካህናት አለቆች ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዘውት እንዲመጡ ሎሌዎች ላኩአቸው፡፡ እነዚህ ሎሌዎች ጌታችንን ይዘው እንዲመጡ ቢላኩም በጌታችን ጣዕመ ትምህርት ተደንቀው ተመስጠው ሲማሩ ውለው ባዶ እጃቸውን ተመለሱ፡፡ አይሁድ ‹ያላመጣችሁት ስለ ምንድን ነው?›› ብለው ቢጠይቋቸው ‹‹እንደዚህ ሰው ከቶ ማንም ተናግሮ አያውቅም›› ብለው መለሱ፡፡ ይህን ጊዜ አይሁድ ተቆጥተው ሎሌዎቹን ‹‹እናንተ ደግሞ ሳታችሁ? ከአለቆች ወይም ከፈሪሳውያን መካከል በእርሱ ያመነ ሰው የለም፡፡ ሕዝቡም ያመነበት ሕግ የማያውቅ ርጉም ስለሆነ ነው›› ብለው ገሠጹአቸው፡፡ እናንተ ያመናችሁት ባለማወቃችሁ ነው ፤ ከእኛ ከአዋቂዎቹ ማን በእሱ አመነ? ብለው ሊያሸማቅቋቸው ሞከሩ፡፡

ይህን ሁሉ ሲሆን የማታው ተማሪ የአይሁድ መምህር ኒቆዲሞስ እዚያ ቆሞ ነበር፡፡ ከአለቆች መካከል በጌታ ያመነ የለም ሲባል እየሰማ ነው፡፡ አሁን ክርስትናው ልትፈተን ነው፡፡ ደፍሮ እኔ አምኜአለሁ ብሎ መናገር ባይችልም ፈራ ተባ እያለ እንዲህ አለ ‹‹ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላቸው።›› እነሱ በተናገሩት ብቻ ለምን ትፈርዳላችሁ? እሱን ሳትሰሙ መፍረድ ተገቢ ነው ወይ? ማለቱ ነበር፡፡ አይሁድ እንደ ሎሌዎቹ ሁሉ ኒቆዲሞስን ማቃለል እንዳይችሉ የተከበረ መምህር ሆነባቸው፡፡ ስለዚህ ‹‹አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ነቢይ ከገሊላ እንዳይነሣ መርምርና እይ አሉት። እያንዳንዱም ወደ ቤቱ ሄደ።›› ጌታችን ከገሊላ ናዝሬት መምጣቱን በመጥቀስ መሲህ ከገሊላ አይነሣም ብለው ሊያስተባብሉ ሞከሩ፡፡ ይህ ግራ መጋባት በሐዋርያው ናትናኤልም የታየ ነበር እርሱ ‹‹ከናዝሬት መልካም ነገር ይወጣልን?›› ብሎ የጠየቀው መሲሁ ከይሁዳ ቤተ ልሔም እንደሚነሣ የተነገረውን ትንቢት በማየት ነበር፡፡ ጌታችን የተወለደው ከቤተ ልሔም ነው ያደገው ግን በገሊላ ናዝሬት በመሆኑ ነው ይኼ ሁሉ ውዥንብር፡፡ ኒቆዲሞስ ክርስትናውን በሌሊት ፈርቶ ጀመረ፡፡ አሁን ሙሉ በሙሉ ክርስቲያን ነኝ ብሎ መመስከርና መግለጥ ባይችልም ቢያንስ አይሁድ ከአለቆች ማን በእርሱ አመነ? ብለው ሲዘብቱ ቢያንስ ድምፁን ለማሰማት ሞከረ፡፡ በጥያቄ አስጨንቆም በዚያች ዕለት ስብሰባውን በተነው፡፡

ፍጹማዊው ኒቆዲሞስ

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል መከራ ዓለምን የማዳን ሥራውን ፈጸመ፡፡ በዚህ የመከራ ወቅት በዋለበት የዋሉ ባደረበት ያደሩ ደቀ መዛሙርቱ ከዮሐንስ በቀር በፍርሃት ተበተኑ፡፡ ነፍሱን ከሥጋው ተለይቶ ከመስቀሉ ሲወርድም አንድም ሐዋርያ አብሮት አልነበረም፡፡ በዚህ ወቅት ኒቆዲሞስ እንደ ቀድሞው ሌሊት እስኪሆን አልጠበቀም፡፡ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ ከአርማትያው ዮሴፍ ጋር ሆነው የጌታችንን ሥጋ ወሰዱ፡፡ እንደ አይሁድ የአገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት፡፡ ሲገንዙት እያለቀሱ ነበር ‹‹ሞትከኑ መንሥኤሆሙ ለሙታን ፤ ደከምከኑ መጽንኤሆሙ ለድኩማን›› ‹‹ሙታንን የምታስነሣ ሆይ ሞትክን? ደካሞችን የምታጸናቸው ሆይ ደከምክን?›› እያሉ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ጌታችን በመለኮቱ ሕያው እንደመሆኑ አነጋገራቸው፡፡ በነገራቸው መሠረት ‹‹ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት…›› የሚለውን በኪዳን ወቅት የምናደርሰውን ዓለም አቀፋዊ ጸሎት እያደረሱ ገነዙት፡፡

ኒቆዲሞስ ሲፈራ ፣ ቀስ እያለ ሲናገር የነበረውን ክርስትናውን በአደባባይ ገለጠ፡፡ ‹‹ልቡ ለጻድቀ ውኩል ከመ አንበሳ›› ‹‹ጻድቅ ግን እንደ አንበሳ ሳይፈራ ይኖራል ›› እንዲል ጠቢቡ በጌታ የደረሰ መከራ ቢደርስብኝ ሳይል ሥጋውን ተሸክሞ ገነዘ፡፡ ከምኩራብ ያስወጡኛል ብሎ የፈራው ኒቆዲሞስ ቤተ ክርስቲያን እንዳለች ስለተረዳ በድፍረት ክርስትናውን መሰከረ፡፡ ከሦስቱ የኒቆዲሞስ ክርስትና ደረጃዎች እኛ በየትኛው ላይ ነን? ስለ ሃይማኖታችንስ በየትኛው ደረጃ እንመሰክራለን፡፡ በጨለማ ነው? ፈራ ተባ እያልን ነው ? ወይንስ ያለ ፍርሃት?

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 2006 ዓ ም
[email protected]

Address

Ambo

Telephone

+251925692398

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ተስፋ የበጎ-አድራጎት ክበብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ተስፋ የበጎ-አድራጎት ክበብ:

Share