ጋዳይ ቅ/ሚካኤልGaday S/t Mikhail

ጋዳይ  ቅ/ሚካኤልGaday S/t Mikhail የሀይማኖት ተቋም

እንኳን አደረሳችሁ ለቅዱስ ሚካኤል ወርሐዊ ባእል 252494944 አቢሲኒያ  ባንክ።Abebaw kasahun & Apraim Abebeይህ ቤተክርስቲያን እደምታዮት እድሣት ይፈልጋል  እና የበርከት...
21/03/2026

እንኳን አደረሳችሁ ለቅዱስ ሚካኤል ወርሐዊ ባእል 252494944 አቢሲኒያ ባንክ።
Abebaw kasahun & Apraim Abebe
ይህ ቤተክርስቲያን እደምታዮት እድሣት ይፈልጋል እና የበርከት ተሳታፊ እድትሆኑ በቅዱስ ሚካኤል ስም አንጠይቃለን🤲🤲🤲የሠራዊት ጌታ የልዑል እግዚአብሔር አገልጋይ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል 🙏

የስሙ ትርጓሜ “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ነው። ከእግዚአብሔር ዙፋን ትዕዛዝ ሲወጣ ኪሩቤልና ሱራፌል ለሚካኤል ያስተላልፋሉ፡፡ ሚካኤል ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ መላዕክትን ያዛቸዋል፤ ኪሩቤልና ሱራፌል መላዕክቱም ሁሉ አቤቱ የእጅህን ስራ አታጥፋ እያሉ ቀንና ማታ ይለምናሉ። ድርሳነ ሩፋኤል ላይ ተጽፎ እደምናገኘው 7 ሊቃነ መላዕክት ሲኖሩ አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ የመላዕክቱን ስም የመጨረሻውን ፊደል ስናይ ኤል ብሎ ይጨርሳል፡፡ ሚካ-ኤል ገብር-ኤል ኡራ-ኤል፤ ይህም “ስሜ በሱ ላይ ነውና” እንደሚል የእግዚአብሔር የምህረት ስም በክንፎቻቸው ስለተጻፈ መላዕክቱ ይጠብቁናል። አይሁድ ጌታን ሲሰቅሉት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በቁጣ ሰይፉን አወጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል ግን በአይሁድ ስራ አዝኖ፣ የፈጣሪን የትዕግስቱንና የፍቅሩን ብዛት እያደነቀ በአርምሞ አያቸው ይላል ድርሳኑ።

መላዕክቱ በክንፋቸው የእግዚአብሔር ስም ተጽፎበታል፡፡ “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለአንተ ያዛቸዋል፤ እግርህም በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቻቸው ያነሱሃል” ተብሎም በመዝሙር 90÷11 ተጽፋልና አህዛብን ጭምር ያለጊዜያቸው እንዳይሞቱ መላዕክት ይጠብቋቸዋል፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 33÷7 “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል” ይለናል፡፡ በትንቢተ ዳንኤል 10÷13 እና 10÷21 ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲናገር ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፣ በተዘጋ ጉድጓድ ሲያጽናናው ደግሞ “ከሚካኤል በቀር የሚያጽናናኝ የለም” አለ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜንኅዳር 25-የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርቆሬዎስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ‹‹መርቆሬዎስ›› ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም የኢየሱ...
03/12/2024

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ኅዳር 25-የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርቆሬዎስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ‹‹መርቆሬዎስ›› ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ወላጆቹ አስሊጥ ከምትባል ሀገር ቢሆኑም እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡ አያቱና አባቱ ሥራቸው አውሬ ማደን ስለነበር አንድ ቀን እንደልማዳቸው አውሬ ሲያድኑ ከገጸ ከለባት ወገን የሆኑ ሁለት ወንዶች አግኝተዋቸው የመርቆሬዎስን አያት በሉት፡፡

አባቱንም ሊበሉት ሲሉ የታዘዘ መልአክ ከለከላቸው፡፡ ዙሪያቸውንም በእሳት አጥሮ ከበባቸው፡፡ እነርሱም በተቸገሩ ጊዜ ለመርቆሬዎስ አባት ሰገዱለት፡፡ በዚያን ጊዜም እግዚአብሔር ፍጥረታቸውን ወደገራምነት ለወጠውና እንደበጎች የዋሆች ሆነው አብረውት ወደ መንደር ገቡ፡፡ ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርቆሬዎስ ተወለደና ስሙ ፒሉፓዴር ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸውም በእርሱ ዘንድ ብዙ ዘመናት ኖሩ፡፡ ከዚህም በኋላ ክርስቲያኖች ሆኑ፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም ወላጆች አስቀድመው አረማውያን ነበሩና የክርስትና ጥምቀትን በጸጋ ተቀበሉ፡፡ አባቱን ኖህ እናቱንም ታቦት ብለው ሰየሟቸው፡፡
ቀድሞ ፒሉፓዴር የነበረውም ስሙ ተለውጦ መርቆሬዎስ ተባለ፡፡ የውሻ መልክ ያላቸው ግን መልአኩ በተገለጠላቸው ጊዜ እንደነገራቸው ለቅዱስ መርቆሬዎስ አባት የሚታዘዙና የሚያገለግሉ ሆኑ፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባትና የውሻ መልክ ያላቸውን ዜናቸውን ሲሰማ ወታደሮቹን ልኮ በፊቱ አቆማቸው፡፡ እግዚአብሔርም የቀድሞ ፍጥረታቸውን መልሶላቸው አራዊት አደረጋቸውና ንጉሡን እጅግ አስፈሩት፡፡ ንጉሡም የቅዱስ መርቆሬዎስን አባት የአራዊት ተፈጥሮአቸውን ያርቅለት ዘንድ ለመነው፡፡ የቅዱስ መርቆሬዎስም አባት በለመነ ጊዜ ተፈጥሮአቸውን መልሶላቸው ገራሞች ሆኑ፡፡
ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ገዥና የሠራዊቱ አለቃ አድርጎ ሾመው፡፡ የውሻ ፊት ያላቸውም አብረው ያገለግሉት ስለነበር ሁሉም ይፈራው ነበር፡፡ ንጉሡም የመርቆሬዎስን አባት ወደ ጦርነት ከላከው በኋላ ሳይመለስ ስለቀረ ሚስቱን ሊያገባት አሰበ፡፡ የመርቆሬዎስ አባትም የመርዶሳውያን አገሮች ሁሉ ገዢ በነበረው ንጉሥ ተይዞ ቢማረክም ገዥው ክርስቲያን መሆኑን አይቶ አከበረው፡፡ ቆይቶም በሀገሩ ላይ ሾመው፡፡ ሚስቱም ጠፍታ ከሀገሯ ወጥታ ሄዳ ስለነበር ከባሏ ተገናኝተው በዚያው መኖር ጀመሩ፡፡ መርቆሬዎስም አባቱና እናቱ ከሞቱ በኋላ ንጉሡ በአባቱ ፈንታ በመርዶሳውያን አገር ላይ ሾመው፡፡

መርቆሬዎስ መኰንንነት በተሾመም ጊዜ ገጸ ከለባቱ አብሮት ነበር፡፡ ለመዋጋትም በወጣ ጊዜ የቀድሞው የአራዊት የሆነ ተፈጥሮውን እግዚአብሔር ይመልስለት ስለነበር ማንም አይቋቋመውም ነበር፡፡ ለቅዱስ መርቆሬዎስ ታላቅ የድል አድራጊነት ኃይል ተሰጠውና ዜናው በሁሉም ሀገሮች ተሰማ፡፡ በሮሜ ሀገር ጣዖትን የሚያመልከው ዳኬዎስ የተባለውም ንጉሥ የበርበር ሰዎች ጋር ጦርነት ሊገጥም በወጣ ጊዜ እጅግ ሲበዙበት ፈራ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በጦሩ መሀል የተሳለ ሰይፍ የያዘ የእግዚአብሔርን መልአክ ስላየ ንጉሡን እግዚአብሔር ያጠፋቸዋልና አትፍራ›› አለው፡፡ መልአኩም ሰይፉን ለቅዱስ መርቆሬዎስ ሰጠውና ‹‹ጦርነቱን ድል ባደረግህ ጊዜ እግዚአብሔርን አስበው›› አለው፡፡ ጦርነቱን ድል አድርጎ ሲጨርስም መልአኩ ድጋሚ ተገልጦለት ‹‹ለምን የፈጣሪህን ስም መጥራት እረሳህ?›› አለው፡፡ ከጦርነቱም በኋላ ንጉሥ ዳኬዎስ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረግ በዓልን አደረገ፡፡ ቅዱስ መርቆሬዎስም በዚያ ስላልተገኘ ለጣዖታቱ ዕጣን በማሳረጉ እንዳልተባበረ ንጉሡ ሲያውቅ መልእክተኞችን ልኮ አስመጣው፡፡ ንጉሡም ‹‹ከእኔ ጋር ለምን

[የቁስቋም ክብር በኢትዮጵያ ቀደምት ሊቃውንት]✍በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ❖♥ ከ3 ዓመት የስደት ውጣ ውረድ በኋላ የአምላክ እናት ልጇ አምላካችን ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜ...
15/11/2024

[የቁስቋም ክብር በኢትዮጵያ ቀደምት ሊቃውንት]
✍በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
❖♥ ከ3 ዓመት የስደት ውጣ ውረድ በኋላ የአምላክ እናት ልጇ አምላካችን ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜን አስከትላ ከመዐዲ ወደ ላዕላይ ግብጽ በጀልባ ደግሞ ከካይሮ በስተደቡብ 320 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በላዕላይ ግብጽ በምትገኘው ወደ ደብረ ቊስቋም ገብተው በመንገድ ጒዞ ካገኛቸው ድካም 6 ወር ከ10 ቀናት ዐርፈዋልና ኅዳር 6 በደመቀ መልኩ በዓሏ ይከበራል፡፡

❖ ♥በደብረ ቁስቋም ሳሉ ጨካኙ ሄሮድስ እንደሞተ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ "የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘኽ ወደ እስራኤል አገር ኺድ" ብሎታል (ማቴ 2፡19-20)።

❖ ♥ ይኽቺን ጌታ ከእናቱ ጋር ያረፈባትን የተቀደሰች ቦታን ጌታችን ባርኳት ወደ ናዝሬት ተመልሰዋል። ጌታችን ካረገ ከብዙ ዘመን በኋላ በኅዳር ስድስት ቀን “አስተጋብኦሙ እግዚእነ ለሐዋርያቲሁ ቅዱሳን ውስተ ዝንቱ ደብረ ቊስቋም ወቀደሰ ታቦተ ወቤተ ክርስቲያን ወሠርዐ ቊርባነ ወመጠዎሙ ሥጋሁ ቅዱሰ ወደሞ ክቡረ” ይላል (በዚኽ በደብረ ቊስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰበሰባቸው ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ሰጥቷቸዋል) ይላል፡፡

❖♥ በዚኽ ምክንያት ደብረ ቁስቋምን የእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በግብጽ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ይሏታል፤ የግብጽ ኦርቶዶክስ ምእመናን በእጅጉ የሚወዷት የቁስቋም ገዳም ስትኾን በ1993 ዓ.ም. ላይ እመቤታችን በገዳሙ ተገልጣ እንደነበር ይናገራሉ፤ በዚኽችም ገዳም 100 መነኮሳት ይገኙበታል፤ ከቦታዋ ክብር የተነሣ "ዳግሚት ቤተልሔም" ይሏታል፤ በገዳሙም በቅዱሳት መጻሕፍት የተመላ ታላቅ ቤተ መጻሕፍት አለ፨

❖♥ በጌታ በተባረከችው ይኽቺ ቦታ ላይ በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ ቅዱስ ጳኩሚስ ገዳምን የገደመ ሲኾን፤ የእስክንድርያ 23ኛ ፓትርያርክ ቴዎፍሎስ በታናሿ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ምትክ ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት ባሰበ ጊዜ እመቤታችን ተገልጻለት የልጇ የክርስቶስ ትሕትናው በገዳሙ እንዲታሰብበት ባለበት እንዲኾን ነግራዋለች።

❖♥ በርካቶች የኢትዮጵያ ሊቃውንት እመቤታችን ከልጇ ጋር ወደ ቊስቋም የመግባቷን ነገር የጻፉ ሲኾን ለምሳሌም አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በሰዓታት መጽሐፉ ላይ በስፋት ሲዘረዝረው፡-

♥ [“በሊዓ ሕፃናት ሶበ ኀለየ ሄሮድስ አርዌ ሰማይ
ምስለ ዮሴፍ አረጋይ
ነገደት ቊስቋመ ናዛዚተ ሐዘን በብካይ”]
(የሰማዩ አውሬ ሄሮድስ ሕፃናትን መብላት ባሰበ ጊዜ፤ ከሐዘንና ከልቅሶ የምታረጋጋ ማርያም ከአረጋዊዉ ዮሴፍ ጋራ ወደ ቊስቋም ኼደች (ተሰደደች))

❖♥ “አሥረጸት ማርያም አክናፈ ረድኤት አምሳለ ዖፍ ለዐሪገ ቊስቋም
ህየ ከመ ትትዐቀብ ዘመነ ወአዝማነ ወመንፈቀ ዘመን በከመ ይቤ መጽሐፍ”
(ማርያም ወደ ቊስቋም ተራራ ለመውጣት እንደ ዎፍ የረድኤት ክንፎችን አበቀለች በመጽሐፍ እንደተናገረ በዚያ በዘመንና በዘመናት በዘመን እኩሌታም ትጠበቅ ዘንድ)

❖ ♥ “ብጽዐን ለኪ ኦ ደብረ ቊስቋም
እምኲሎን አድያም እምናዝሬት እስከ ቤተልሔም
ዘተጸወነ ላዕሌኪ መድኀኔ ኲሉ ዓለም”
(ከናዝሬት እስከ ቤተ ልሔም ካሉ አውራጆች ኹሉ የዓለም ኹሉ መድኀኒት ወደ አንቺ የተጠጋ የቊስቋም ተራራ ሆይ ክብር ይገባሻል)

❖♥ “በቃለ ውዳሴ ጥዑም ይደሉ ሰላም
ለዕበይኪ ፍጹም አድባረ ቊስቋም
ማኅደረ ልዑል ዘአርያም”
(በአርያም ያለ የልዑል ማደሪያው የኾንሽ የቊስቋም ተራራ ሆይ ፍጹም ለሚኾን ክብርሽ በሚጣፍጥ የምስጋና ቃል ሰላምታ ማቅረብ ይገባል) በማለት ዘርዝሮ ጽፎ

.            ♥[   ]♥ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በቅዱስ ላል-ይበላ ዘመነ መንግስት ሲሆን፣ ኖሩበት ዘመን "562" ዓመት ነው! በግብፅ ገዳማት "300" ዓመት፣ በኢትዮጵያ ገዳማት "26...
14/11/2024

. ♥[ ]♥

ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በቅዱስ ላል-ይበላ ዘመነ መንግስት ሲሆን፣ ኖሩበት ዘመን "562" ዓመት ነው! በግብፅ ገዳማት "300" ዓመት፣ በኢትዮጵያ ገዳማት "262" ዓመታትን ኖረዋል! ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሀገራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡! አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡! ልጅ አጥተው 30 ዘመን ሲያዝኑ ሲማጸኑ ኖረዋል፡፡ በዚሁ እግዚአብሔር ልመናቸውን ሰምቶ ልጅ ሰጣቸው፣ ይህም ጻድቁ በመጋቢት 29 ተጸንሰው ታህሳስ 29 ተወለዱ፡፡ እርሳቸውም በተወለዱ ጊዜ አፈፍ ተነስተው “ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ ዘአውጻእከኒ እምጽ ልመት ውስተ ብረሃን” ብለው አመስግነዋል! ኋላም ምድራዊ መብል መጠጥ ሳይመገቡ ሳይጠጡ ለምስጋና ተግተው በመኖራቸው መላዕክትን መስለዋል።

ሦስት ዓመት ሲሆናቸው ቅዱስ ገብርኤል ከእመቤታችንና በገነት ካሉ ቅዱሳን ዘንድ አስባርኮ ገዳማውያን ካሉበት አበ ምኔት ወስዶ ከበሩ አኖራቸው! አባ ዘመደ ብርሃን አሳድጎ አስተምሮ ከመዓርገ ምንኩስና አድርሷቸዋል፡! በክህነትም ሀብተ ፈውስ ተሰቷቸዋል! ኋላ ግን ኤጲስ ቆጶሳቱ ካህናቱ ዝናቸውን ሰምተው እየመጡ የጸሎት ግብር የሚያስፈቷቸው ቢሆን ቅዱስ ገብርኤል በክንፉ ነጥቆ ከጌታ ፊት አቀረባቸው፡! በገድልህ በትሩፋትህ ከሞተ ነፍስ ከርደተ ገሃነም የሚድኑ ብዙ ነፍሳት አሉና ከሰው ተለይተህ ወደ ጫካ ግባ፣ ኑሮህም ከ60 አናብስተና ከ60 አናምርት ጋር ይሁን አላቸው! ጌታዬ ምን ተመግበው ይኖራሉ? ብለው ጌታን ጠየቁት፡፡ “ዘኬድከ ጸበለ-እገሪከ ይልህሱ ወበውእቱ ይጸግቡ…” የረገጥከውን ትቢያ ልሰው ያው ምግብ ሆኗቸው ይኖራሉ ብሏቸው ውሳጤ ገዳም ገብተው ከአናብስትና አናምርት ጋር ይኖሩ ጀመር።

በዚህ መልኩ መልአኩ 30 ዓመት ከቆዩ በኋላ ጌታ ባንድነት በሦስትነት ተገልጾ “ምን ላድርግልህ ትሻለህ?” አላቸው፡፡ መጀመሪያ ላሉበት መጸለይ ይገባልና የምድረ ጋቦታን ሰዎች ማርልኝ አሉት፡፡ 3000 ኃጥአንን ከሲኦል አውጥቶ ገነት አግብቶላቸዋል።

“ሑር ምድረ ኢትዮጵያ ወበህየኒ ሀላዉከ ነፍሳት ዘታወጽኦሙ – ወደ ኢትዮጵያ ሂድ” አላቸው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በሰረገላ ነፋስ ጭኖ ምድረ ከብድ አድርሷቸዋል፡፡ ዳግመኛም ወደ ዝቋላ ደብር ቅዱስ ወስዷቸው ከዚያ ሆነው በንጽሐ ልቦና የኢትዮጵያን ሕዝብ ሃጢአት አይተው ከባሕሩ በራሳቸው ቆመው ይጸልዩ ጀመር፡፡ አርባ ቀን ሲሆናቸው መልአኩ መጥቶ “ዘገብረ ተዝካረከ ወዘጸውዐ ስመከ እምሕር ለከ ብሎሀል” አላቸው፡፡ መላ ኢትዮጵያን ካልማረልኝ አልወጣም ብለው መቶ አመት ሲጸልዩ ኑረዋል፡፡ ከመቶ አመት በዃላ ጌታ “ተንስእ ወጻእ መሐርኩ ለከ ኩሎ ኢትዮጵያ ምሬለሃለሁ ውጣ” ብሏቸው ወጥተዋል።

ከዚህ በኋላ ምድረ ከብድ ወርደው ከምድር በላይ ከሰማይ በታች ሆነው ሰባት ዓመት እንደ ትኩል ዓምድ ሆነው ዓይናቸውን ሳይከድኑ ሰባት ዓመት ቆመው ጸልየዋል፡፡ ሰይጣንም በምቀኝነት ተነሳስቶ ቁራን መስሎ መጥቶ አይናቸውን አንቁሮ አሳወራቸው፡፡ ሁለት ሱባኤ ሲፈጽሙ ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል መጥተው እፍ ብሏቸው አድነዋቸዋል፡፡ ከዚያ ተነስተው ወደ ዝቋላ ሲሄዱ ሥላሴን በአምሳለ አረጋውያን ከጥላ ስር አርፈው አገኟቸው፡፡ በእግዚአብሔር ዙፋን ተማጽነናል አዝለህ አንድ አንድ ምዕራፍ ሸኘን አሏቸው፡፡ አዝለው ከሸኙአቸው በኋላ በአንድነት በሦስትነት ሆኖ ታያቸው ደንግጠው ወደቁ፡፡ አንስተው ዝቋላ ወርደህ ጠላቶችህን ተበቀላቸው አሏቸው፡፡ በዚያም በዝቋላ ብዙ ዘመናትን በተጋድሎ ኖረው፣ በበዓለ ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳወሎስ ሐምሌ "5" ቀን ከስጋ ድካም አርፈዋል።

22/04/2024

የማቴዎስ ወንጌል Matthew 5

ምዕራፍ፡5፤
1፤ሕዝቡንም፡አይቶ፡ወደ፡ተራራ፡ወጣ፤በተቀመጠም፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡ፤
2፤አፉንም፡ከፍቶ፡አስተማራቸው፡እንዲህም፡አለ።
3፤በመንፈስ፡ድኻዎች፡የኾኑ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መንግሥተ፡ሰማያት፡የእነርሱ፡ናትና።
4፤የሚያዝኑ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መጽናናትን፡ያገኛሉና።
5፤የዋሆች፡ብፁዓን፡ናቸው፥ምድርን፡ይወርሳሉና።
6፤ጽድቅን፡የሚራቡና፡የሚጠሙ፡ብፁዓን፡ናቸው፥ይጠግባሉና።
7፤የሚምሩ፡ብፁዓን፡ናቸው፥ይማራሉና።
8፤ልበ፡ንጹሖች፡ብፁዓን፡ናቸው፥እግዚአብሔርን፡ያዩታልና።
9፤የሚያስተራርቁ፡ብፁዓን፡ናቸው፥የእግዚአብሔር፡ልጆች፡ይባላሉና።
10፤ስለ፡ጽድቅ፡የሚሰደዱ፡ብፁዓን፡ናቸው፥መንግሥተ፡ሰማያት፡የእነርሱ፡ናትና።
11፤ሲነቅፏችኹና፡ሲያሳድዷችኹ፡በእኔም፡ምክንያት፡ክፉውን፡ዅሉ፡በውሸት፡ሲናገሩባችኹ፡ብፁዓን፡ናችኹ።
12፤ዋጋችኹ፡በሰማያት፡ታላቅ፡ነውና፥ደስ፡ይበላችኹ፥ሐሴትም፡አድርጉ፤ከእናንተ፡በፊት፡የነበሩትን፡
ነቢያትን፡እንዲሁ፡አሳደ፟ዋቸዋልና።
13፤እናንተ፡የምድር፡ጨው፡ናችኹ፤ጨው፡ዐልጫ፡ቢኾን፡ግን፡በምን፡ይጣፍጣል፧ወደ፡ውጭ፡ተጥሎ፡
በሰው፡ከመረገጥ፡በቀር፡ወደ፡ፊት፡ለምንም፡አይጠቅምም።
14፤እናንተ፡የዓለም፡ብርሃን፡ናችኹ።በተራራ፡ላይ፡ያለች፡ከተማ፡ልትሰወር፡አይቻላትም።
15፤መብራትንም፡አብርተው፡ከእንቅብ፡በታች፡አይደለም፡እንጂ፡በመቅረዙ፡ላይ፡ያኖሩታል፡በቤት፡ላሉት፡
ዅሉም፡ያበራል።
16፤መልካሙን፡ሥራችኹን፡አይተው፡በሰማያት፡ያለውን፡አባታችኹን፡እንዲያከብሩ፡ብርሃናችኹ፡እንዲሁ፡
በሰው፡ፊት፡ይብራ።
17፤እኔ፡ሕግንና፡ነቢያትን፡ለመሻር፡የመጣኹ፡አይምሰላችኹ፤ልፈጽም፡እንጂ፡ለመሻር፡አልመጣኹም።
18፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ሰማይና፡ምድር፡እስኪያልፍ፡ድረስ፥ከሕግ፡አንዲት፡የውጣ፡ወይም፡አንዲት፡
ነጥብ፡ከቶ፡አታልፍም፥ዅሉ፡እስኪፈጸም፡ድረስ።
19፤እንግዲህ፡ከነዚህ፡ከዅሉ፡ካነሱት፡ትእዛዛት፡አንዲቱን፡የሚሽር፡ለሰውም፡እንዲሁ፡የሚያስተምር፡ማንም፡
ሰው፡በመንግሥተ፡ሰማያት፡ከዅሉ፡ታናሽ፡ይባላል፤የሚያደርግ፡ግን፡የሚያስተምርም፡ማንም፡ቢኾን፡ርሱ፡
በመንግሥተ፡ሰማያት፡ታላቅ፡ይባላል።
20፤እላችዃለኹና፦ጽድቃችኹ፡ከጻፊዎችና፡ከፈሪሳውያን፡ጽድቅ፡ካልበለጠ፥ወደ፡መንግሥተ፡ሰማያት፡ከቶ፡
አትገቡም።
21፤ለቀደሙት፦አትግደል፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል፤የገደለም፡ዅሉ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል።
22፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥በወንድሙ፡ላይ፡የሚቈጣ፡ዅሉ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል፤ወንድሙንም፡ጨርቃም፡
የሚለው፡ዅሉ፡የሸንጎ፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል፤ደንቈሮ፡የሚለውም፡ዅሉ፡የገሃነመ፡እሳት፡ፍርድ፡ይገ፟ባ፟ዋል።
23፤እንግዲህ፡መባኽን፡በመሠዊያው፡ላይ፡ብታቀርብ፥በዚያም፡ወንድምኽ፡አንዳች፡ባንተ፡ላይ፡እንዳለው፡
ብታስብ፥
24፤በዚያ፡በመሠዊያው፡ፊት፡መባኽን፡ትተኽ፡ኺድ፥አስቀድመኽም፡ከወንድምኽ፡ጋራ፡ታረቅ፥በዃላም፡
መጥተኽ፡መባኽን፡አቅርብ።
25፤ዐብረኸው፡በመንገድ፡ሳለኽ፡ከባላጋራኽ፡ጋራ፡ፈጥነኽ፡ተስማማ፤ባላጋራ፡ለዳኛ፡እንዳይሰጥኽ፡ዳኛም፡
ለሎሌው፥ወደ፡ወህኒም፡ትጣላለኽ፤
26፤እውነት፡እልኻለኹ፥የመጨረሻዋን፡ሳንቲም፡እስክትከፍል፡ድረስ፡ከቶ፡ከዚያ፡አትወጣም።
27፤አታመንዝር፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል።
28፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥ወደ፡ሴት፡ያየ፡ዅሉ፡የተመኛትም፡ያን፡ጊዜ፡በልቡ፡ከርሷ፡ጋራ፡
አመንዝሯል።
29፤ቀኝ፡ዐይንኽም፡ብታሰናክልኽ፡አውጥተኽ፡ከአንተ፡ጣላት፤ሙሉ፡ሰውነትኽ፡በገሃነም፡ከሚጣል፡ይልቅ፡
ከአካላትኽ፡አንድ፡ቢጠፋ፡ይሻልኻልና።
30፤ቀኝ፡እጅኽም፡ብታሰናክልኽ፡ቈርጠኽ፡ከአንተ፡ጣላት፤ሙሉ፡ሰውነትኽ፡በገሃነም፡ከሚጣል፡ይልቅ፡
ከአካላትኽ፡አንድ፡ቢጠፋ፡ይሻላልና።
31፤ሚስቱን፡የሚፈታት፡ዅሉ፡የፍቿን፡ጽሕፈት፡ይስጣት፡ተባለ።
32፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥ያለዝሙት፡ምክንያት፡ሚስቱን፡የሚፈታ፡ዅሉ፡አመንዝራ፡
ያደርጋታል፥የተፈታችውንም፡የሚያገባ፡ዅሉ፡ያመነዝራል።
33፤ደግሞ፡ለቀደሙት፦በውሸት፡አትማል፥ነገር፡ግን፥መሐላዎችኽን፡ለጌታ፡ስጥ፡አንደ፡ተባለ፡
ሰምታችዃል።
34፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፦ከቶ፡አትማሉ፤በሰማይ፡አይኾንም፡የእግዚአብሔር፡ዙፋን፡ነውና፤
35፤በምድርም፡አይኾንም፡የእግሩ፡መረገጫ፡ናትና፤በኢየሩሳሌምም፡አይኾንም፡የታላቁ፡ንጉሥ፡ከተማ፡
ናትና፤
36፤በራስኽም፡አትማል፥አንዲቱን፡ጠጕር፡ነጭ፡ወይም፡ጥቍር፡ልታደርግ፡አትችልምና።
37፤ነገር፡ግን፥ቃላችኹ፡አዎን፡አዎን፡ወይም፡አይደለም፡አይደለም፡ይኹን፤ከነዚህም፡የወጣ፡ከክፉው፡
ነው።
38፤ዐይን፡ስለ፡ዐይን፡ጥርስም፡ስለ፡ጥርስ፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል።
39፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥ክፉውን፡አትቃወሙ፤ዳሩ፡ግን፡ቀኝ፡ጕንጭኽን፡በጥፊ፡ለሚመታኽ፡ዅሉ፡
ኹለተኛውን፡ደግሞ፡አዙርለት፤
40፤እንዲከስኽም፡እጀ፡ጠባብኽንም፡እንዲወስድ፡ለሚወድ፡መጐናጸፊያኽን፡ደግሞ፡ተውለት፤
41፤ማንም፡ሰው፡አንድ፡ምዕራፍ፡ትኼድ፡ዘንድ፡ቢያስገድድኽ፡ኹለተኛውን፡ከርሱ፡ጋራ፡ኺድ።
42፤ለሚለምንኽ፡ስጥ፥ከአንተም፡ይበደር፡ዘንድ፡ከሚወደ፟ው፡ፈቀቅ፡አትበል።
43፤ባልንጀራኽን፡ውደድ፡ጠላትኽንም፡ጥላ፡እንደ፡ተባለ፡ሰምታችዃል።
44-45፤እኔ፡ግን፡እላችዃለኹ፥በሰማያት፡ላለ፡አባታችኹ፡ልጆች፡ትኾኑ፡ዘንድ፡ጠላቶቻችኹን፡
ውደዱ፥የሚረግሟችኹንም፡መርቁ፥ለሚጠሏችኹም፡መልካም፡አድርጉ፥ስለሚያሳድዷችኹም፡ጸልዩ፤ርሱ፡
በክፉዎችና፡በበጎዎች፡ላይ፡ፀሓይን፡ያወጣልና፥በጻድቃንና፡በኀጢአተኛዎችም፡ላይ፡ዝናቡን፡ያዘንባልና።
46፤የሚወዷ፟ችኹን፡ብትወዱ፡ምን፡ዋጋ፡አላችኹ፧ቀራጮችስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡የለምን፧
47፤ወንድሞቻችኹንም፡ብቻ፡እጅ፡ብትነሡ፡ምን፡ብልጫ፡ታደርጋላችኹ፧አሕዛብስ፡ያንኑ፡ያደርጉ፡
የለምን፧
48፤እንግዲህ፡የሰማዩ፡አባታችኹ፡ፍጹም፡እንደ፡ኾነ፡እናንተ፡ፍጹማን፡ኹኑ።

16/03/2024
14/02/2024

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን

የካቲት 6-በዓለም ሁሉ በመመካከር በሚሰበሰብበት ቦታ ሁሉ ገድሏል እንዲነገር ጨካኝ ያዘዘላት፣ ገድልና ድርሳን ማንኛውንም ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የጻፈላት በዓል ሸዋ ቅድስት ማርያም እንደ ዕረፍተ ሥጋ ነው።

+ ቅድስት አትናስያና እስቱ ደናግል ልጆቻችሁ በአንድ ጊዜ በሰማዕትነት አረፉ።
ከእነርሱም ጋር የከበሩ ቅዱሳን ዮሐንስና አቡኪር በሰማትነት አርፈዋል።

+ የዓለም ሁሉ መምህር የሆነው አባ አቡሊዲስ በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ ሥጋው ከባሕርይ ሕይወቱ በቤተአምራት የወጣበት ዕለት ነው።

|
የስማቸው ኅሊና ትምህርት ‹‹የእግዚአብሔር ስጦታ››፣ ‹‹የእግዚአብሔር ሃይማኖት›› እና ‹‹የእግዚአብሔር ምስጋና›› የሚል ነው።
አቡ መረቅ ከታናሽነቱ ጀምሮ በገድል ተጠምዶ የሚኖር መነኮሰ።
የቀብር ዮሐንስ ግን በንጉሥ ውሥጥ ውስጥ የሚያገለግል ነው።
የነሱም ሀገራቸው እስክንድርያ ሲሆኑ የሚኖሩት ግን አን እንገናኛለን።
በዚያም እነዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት ደናግል ቴዎድራ፣ ቴዎፍና፣ ቴዎዶክስያ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ፊት ቆመው የጨረር ክብር መሰከሩ።
ንጉሡም ከወዴት በመከራቸው ጊዜ ከእስክንድርያ ሕመም ሲነገሩት ወደዚያ ወሰዱት ያሠቃዩአቸው።

እነዚህም ቅድመ ቅዱሳት ደናግል እስክንድርያ በደረሱ ጊዜ ዳግመኛ በመኮንኑ ፊት ቆመው የጨረር አምላክነት በመስቀል ላይ በጣም ማምለክን ረገሙ።
በዚ የተናደደው መኮንን ጽኑ ሥቃይን አሠቃያቸው።
በመጨረሻ ማሠቃየት በሠላቸው ጊዜ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ።
እናታቸው የቀበረች ቅድስት አትናስያም ደናግል ልጆቻችን በአንድ ወቅት በጨረር ስም ምስክር ሆነው በሰማዕትነት ከሞቱ ለሰማያዊው ሙሽራ ለክርስቶስ ሙሽሮች እንደሚሆኑ በመንገር ታጽናናቸው።
አቡ መረራም በከበረች ሃዋርያዊት በቅድስት ቴክላ ላይ የደረሰውን መከራና መመልከቻውን ክብር ይገልፃቸውና ያጽናኑ።

ሰማእቷ ትርዳን 💟💟💟💟💟💟
13/02/2024

ሰማእቷ ትርዳን 💟💟💟💟💟💟

Address

Amanu'el
W

Telephone

+251918206728

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጋዳይ ቅ/ሚካኤልGaday S/t Mikhail posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share