የአጋሮ ደ/ ፀ /ቅ/ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት:"Agaro st- George Sunday School"

  • Home
  • Ethiopia
  • Agaro
  • የአጋሮ ደ/ ፀ /ቅ/ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት:"Agaro st- George Sunday School"

የአጋሮ ደ/ ፀ /ቅ/ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት:"Agaro st- George Sunday School" ስለ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ስርአት፣ ትውፊት መማር ማስተማር ቤተክርስቲያንን በቅንነት እና በእውቀት ማገልገል

እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰባረ አፅም አመታዊ ክብረ በአል እና 100ኛ አመት የምስረታ በአል በሰላም አደረሰን።የሰማዕቱ ምልጃ እና በረከት በሁላችን ላይ ይደር።ለ125ኛ ውም ያድርሰን...
26/01/2026

እንኳን ለሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰባረ አፅም አመታዊ ክብረ በአል እና 100ኛ አመት የምስረታ በአል በሰላም አደረሰን።የሰማዕቱ ምልጃ እና በረከት በሁላችን ላይ ይደር።ለ125ኛ ውም ያድርሰን።

11/01/2026

ሲማሩ የት ነበርሽ?ከመባል፣ ከእኛ ወገን ነበሩ ከመባል ይሰውረን።

በሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል ዲያቆን ብሩክ ካሳቸው ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን እግዚአብሔር ነብስህን ከደጋጎች ቅዱሳን ጎን ያሳርፍ።ከህፃንነትህ ጀምሮ ያገለገልከው ሰማእት ...
13/09/2025

በሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል ዲያቆን ብሩክ ካሳቸው ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን እግዚአብሔር ነብስህን ከደጋጎች ቅዱሳን ጎን ያሳርፍ።
ከህፃንነትህ ጀምሮ ያገለገልከው ሰማእት ምልጃ አይለይህ አሜን!

ሁላችሁም ተጋብዛችሁዋል፡፡
18/08/2023

ሁላችሁም ተጋብዛችሁዋል፡፡

26/04/2023

+ የአንድ ሰው ውሎና አመሻሽ +
ይህ እስካሁን ምንጩን ያላገኘሁት አንድ ወንድሜ የላከልኝ በፈረንጅ አፍ የተጻፈ የቆየ የአንድ ሰው ገጠመኝ ነው :-
አንድ ወንድም ስልኩን ድምፅ አልባ ማድረግ ረስቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ስብከት ይማራል:: በዚህ መካከል ስልኩ ይጮኃል::
ሰባኪው ስብከቱን አቁሞ በዓይኖቹ ተቆጣው:: ከስብከቱ በኋላ ምእመናን ስብከቱን በመረበሹ ወቀሱት:: አንዳንዶቹም እያዩት ራሳቸውን በትዝብት ነቀነቁ:: ከሚስቱ ጋር ወደ ቤታቸው ሲሔዱም ሚስቱ ስለ ቸልተኝነቱ ምክር መሥጠትዋን ቀጠለች::
እፍረት መሸማቀቅና ውርደት ዘልቆ እንደተሰማው በፊቱ ላይ ይታይ ነበር:: ከዚያች ሰንበት በኋላ እግሩን ወደ ቤተ ክርስቲያን አንሥቶ አያውቅም::
ውስጡ የተረበሸው ይህ ሰው ያንኑ ምሽት ወደ መጠጥ ቤት አመራ:: አእምሮው እንደታወከ ነበር::
ቁጭ ባለበት ድንገት የሚጠጣበት ጠርሙስ ወድቆ ተሰበረና መጠጡም በዙሪያ ተረጨ:: ፍንጣሪው የነካቸው ሰዎች ወደ እሱ መጠጋት ጀመሩ:: ሊጮኹበትና በጥፊ ሊሉት እንደሆነ ታውቆት ቀድሞ ዓይኖቹን ጨፈነ::
ሰዎቹ ግን በተሰበረው ጠርሙስ ስብርባሪ ተጎድቶ እንደሆነ ተጨንቀው ጠየቁት::
አስተናጋጁ መጥቶ የፈሰሰበትን እንዲያደርቅ ማበሻ ሰጠው:: የጽዳት ሠራተኛዋ መሬቱን ወለወለች::
የቤቱ ባለቤት "አይዞህ ያጋጥማል? ዕቃ የማይሰብር ማን አለና?" አለችውና ሌላ መጠጥ አስመጣችለት::
ከዚያች ቀን ጀምሮ ከዚያ መጠጥ ቤት ቀርቶ አያውቅም::
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስልክን ክፍት ማድረግና ሥርዓተ አምልኮ መረበሽ መቅደስ ውስጥ ጫማ አድርጎ የመግባት ያህል ስኅተት ነው:: እንኩዋን ቤተ ክርስቲያን ኤምባሲ እንኩዋን ስልክህን ውጪ አስቀምጠህ ትገባለህ:: ሰውዬው ላጠፋው ጥፋት ግን በፍቅር የሚያናግረው ሰው በማጣቱ ከነ ስልኩ ሊጠፋ ወሰነ::
ቤተ ክርስቲያን የድኅነት ሥፍራ ናት:: መጠጥ ቤት ደግሞ የጥፋት ጎዳና ነው:: በዚህ ሰው ታሪክ ውስጥ ግን በድኅነት ሥፍራ ካሉ ሰዎች ይልቅ በጥፋት ሥፍራ ያሉ ሰዎች ለሰውዬው ስኅተት የተሻለ ፍቅር አሳዩ:: አንዳንዴ የአንዳንድ ምእመናን ጠባይ ነፍሳትን ወደ ሲኦል ይሰድዳል::
አንዳችን የአንዳችን ጠባቂ መሆን እንችላለን ዓለምን ለመፈወስ የሚቻለንን እናድርግ:: ነፍሳትን ከማዳን ነፍሳትን ማጥፋት በጣም ቀላል ነው::
መድኃኔዓለም ክርስቶስ የኃጢአተኞች ወዳጅ ነበረ:: እሱ የማንንም ቅስም በክፉ ቃል አልሰበረም:: እኛ ግን ሰው ላይ ስንጨክን መጠን የለንም:: በዚህ ምክንያት እንደ ኒቼ ያሉ ሰዎች "ብቸኛው ክርስቲያን መስቀል ላይ የሞተው ነው" ብለው እስኪዘብቱብን ደርሰዋል::
መጽሐፍ ግን ሰው ሲሳሳት ስናይ ምን ማድረግ እንዳለብን እንዲህ ሲል ይናገራል :-
"ወንድሞች ሆይ፥ ሰው በማናቸውም በደል ስንኳ ቢገኝ፥ መንፈሳውያን የሆናችሁ እናንተ እንደዚህ ያለውን ሰው በየውሃት መንፈስ አቅኑት" ገላ. 6:1
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ Henok Haile
ሐምሌ 26 2014 ዓ.ም.
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ይህ የዲያቆን ሄኖክ የፌስቡክ ገጽ አይደለም:: ትምህርቶቹን ለማካፈል ብቻ የተከፈተ ነው:: መልእክቶችና ጥያቄዎች ወደ እኛ አትላኩልን::
አላስፈላጊ ኮሜንቶችና ስድቦችን የሚለጥፍ ሰው ሲኖር ከገጹ በክብር እናሰናብታለን::
የዲያቆን ሄኖክ

ሁላችሁም ተጋብዛችሁዋል!
25/04/2023

ሁላችሁም ተጋብዛችሁዋል!

23/12/2022

በመንፈስ ቅዱስ ስትሞላ ማርያምን በታላቅ ድምጽ ታመሰግናለህ እንጂ እንደ ዘንዶ አታጓራም❗️
ሉቃ.፩፥፵፪

21/12/2020
ሰማእቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከክፉ ሁሉ ይሰዉረን ሀገራችንንም ሰላም ያድርግልን አሜን!🤲🤲🤲
02/12/2020

ሰማእቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከክፉ ሁሉ ይሰዉረን ሀገራችንንም ሰላም ያድርግልን አሜን!🤲🤲🤲

ስለዚህ ሰዉ አባቱን እና እናቱን ይተዋል፤ በሚስቱም ይጣበቃል፤ሁለቱም አንድ ስጋ ይሆናሉ፡፡ዘፍ 2፡24ዉድ ወንድማችን  እና የሰንበት ትምህርት ቤታችን እንቁ አርአያ መምህር አቤል እንኳን ለእ...
20/11/2020

ስለዚህ ሰዉ አባቱን እና እናቱን ይተዋል፤ በሚስቱም ይጣበቃል፤ሁለቱም አንድ ስጋ ይሆናሉ፡፡ዘፍ 2፡24
ዉድ ወንድማችን እና የሰንበት ትምህርት ቤታችን እንቁ አርአያ መምህር አቤል እንኳን ለእዚህ ክብር አበቃህ ትዳራችሁን እግዚአብሄር አምላክ ይባርክ፤ ድንግል ትቀድሰዉ፤ ሰማእቱ ከፊታችሁ ይቅደም አሜን፡፡

Address

Agaro

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአጋሮ ደ/ ፀ /ቅ/ ጊዮርጊስ ሰንበት ትምህርት ቤት:"Agaro st- George Sunday School" posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share