የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Abeba
  • የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት

የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት ይህ የደ/ኃ/ቅ/ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ለህዝበ ? The Sunday school is well known/famous/ 47 aged Sunday school that established by above mentioned actors.

Debere Hyle St.Raguel Church Sunday school was established in 1959 E.C by the will of Almighty GOD, that day's Administrator of the church& the honoring president of Sunday school Melake Hayl Aba Kifle Yohannes's series effort and with deep collaboration of the church's priests, Deacons and full interested about 40-50 village youngsters.

29/04/2026
24/04/2026

5 likes. "ወርሃዊ የቅድስት ኪዳነ ምሕረት ልዩ ጉባዔ ቀጥታ ሰርጭት ከመ/ደ/ኃ/ቅ/ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሚዲያ"

ዛሬ ምሽት 👇
24/04/2026

ዛሬ ምሽት 👇

የረቡዕ ጉባኤ ቀጥታ ስርጭት
22/04/2026

የረቡዕ ጉባኤ ቀጥታ ስርጭት

6 likes. "🔴ቀጥታ ሥርጭት🔴 ልዩ የረቡዕ ጉባኤ ከደ/ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤተክርስቲያን | አንቀጸ ብርሃን ሚዲያ"

ሳምንታዊው የረቡዕ ጉባኤ👇
22/04/2026

ሳምንታዊው የረቡዕ ጉባኤ👇

"ግልጽ ደብዳቤ ለአህመዲን ጀበል"  በቀሲስ ዶ/ር መንግሥቱ ጎበዜ
22/04/2026

"ግልጽ ደብዳቤ ለአህመዲን ጀበል" በቀሲስ ዶ/ር መንግሥቱ ጎበዜ

ግልጽ ደብዳቤ ለአህመዲን ጀበል _በጉልበትና በፈጠራ ድርሰት የታሪክ ባለቤት መሆን አይቻልም _በቀሲስ ዶ/ር መንግሥቱ ጎበዜ አንቀጸ ብርሃን ሚዲያ

ልዩ የትንሣኤ ጉባኤ በቅዱስ ራጉኤል ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች
17/04/2026

ልዩ የትንሣኤ ጉባኤ በቅዱስ ራጉኤል ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች

6 likes. "የቅዱስ ራጉኤል ግቢ ጉባኤ ልዩ የትንሣኤ ጉባኤ"

የሆሣዕና  እና የትንሣኤ በዓል የምስጋና መርሐግብር  ተካሄደየዘንድሮው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሆሣዕና በዓል አዘጋጅ  የመርካቶ ደ/ኃ/ቅ ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰ/ት ቤት እንደ...
16/04/2026

የሆሣዕና እና የትንሣኤ በዓል የምስጋና መርሐግብር ተካሄደ

የዘንድሮው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሆሣዕና በዓል አዘጋጅ የመርካቶ ደ/ኃ/ቅ ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰ/ት ቤት እንደነበር ይታወቃል ።

በመሆኑም በዚህ ታሪካዊ መርሐግብር በልዩ ልዩ አገልግሎት ለተሳተፉ አካላት ሰንበት ትምህርት ቤቱ እውቅና ሰጥቷል።

በተጨማሪም በበዓለ ትንሣኤ በበጎ አድራጎት እና በሌሎች አገልግሎቶች ሱታፌ ለነበራቸውም የእውቅናና የምስጋናው መርሐግብር ተካሂዷል።

አንቀጸ ብርሃን ሚዲያን በተለያዩ አማራጮች ይከተሉ
የዩቲዩብ ቻናል
https://www.youtube.com/

የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/Anqetseberhansundayschool

የፌስቡክ ፔጅ
http://www.facebook.com/sundayschoolofSR

የቲክቶክ ፔጅ
https://www.tiktok.com/

የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተ/ሃይማኖት ቤ/ክ በከባድ መሣሪያ ጉዳት ደረሰበትበሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በቆቦ ከተማ ቤተክህነት አስተዳደር የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲ...
16/04/2026

የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተ/ሃይማኖት ቤ/ክ በከባድ መሣሪያ ጉዳት ደረሰበት

በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በቆቦ ከተማ ቤተክህነት አስተዳደር የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአካባቢው በተከሰተ ጦርነት በከባድ መሣሪያ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል፡፡

ቤተክርስቲያኑ በከባድ መሣሪያ ጉዳት ሲደርስበት በአገልግሎት ላይ የነበሩ ካህናት በእግዚአብሔር ጥበቃ ጉዳት ባይደርስባቸውም የጣራ ቆርቆሮ፣ ኮርኒስና መስታዎት ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ መሆኑን፤ መገልገያ አልባሳትና መጻሕፍቱ ደግሞ በከፊል መጎዳታቸውን የወረዳ ቤተክህነቱ መረጃ ያመለክታል፡፡

ሰበካ ጉባኤው የሕንጻ ቤተክርስቲያኑን የጉዳት መጠን በባለሙያዎች ለማስጠናት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡

የቀመሌ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን በምእመናን ድካምና በከፍተኛ ወጭ በጥርብ ድንጋይ ተገንብቶ ሰኔ 6 ቀን 2013 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመርቆ እየተገለገሉበት የነበረ ሲሆን በደረሰው ጉዳት የደብሩ ሰበካ ጉባኤ አገልግሎቱን ለማስቀጠል መቸገሩን ገልጾ የፈረሰውን ለመጠገን በጎ አድራጊዎች ድጋፍ እንድያደርጉለት መንፈሳዊ ጥሪ አስተላልፏል፡፡

ከ2013-2014 ዓ.ም በተከሰተው ጦርነት በሀገረ ስብከቱ 182 አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ በሙሉና በከፊል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ተጠግነውና በአዲስ መልክ ተገንብተው አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ቢኖሩም በርካታ አብያተ ክርስቲያናት አሁንም በግንባታ ላይ ይገኛሉ፡፡‎

ዘገባው ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ነው።

"፤ እርስዋም መልካም ነገር የሞላባት ምጽዋትም የምታደርግ ነበረች" ሐሥ 9፥36የጌታችንን የትንሣኤ በዓል ምክንያት በማድረግ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤታችን በአጥቢያው ለሚገኙ ነዳያ...
16/04/2026

"፤ እርስዋም መልካም ነገር የሞላባት ምጽዋትም የምታደርግ ነበረች" ሐሥ 9፥36

የጌታችንን የትንሣኤ በዓል ምክንያት በማድረግ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤታችን በአጥቢያው ለሚገኙ ነዳያን የምሳ ምግባ መርሐግብር አካሂዳለች።

በየአመቱ የጌታን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ በአንቀጸ ብርሃን ሰ/ት/ቤት በጎ አድራጎት ክፍል አስተባባሪነት የሚካሄደው የአቅመ ደካሞች ድጋፍና ምገባ ዘንድሮም ተደራሽነቱን በማስፋት ተከናውኗል።

በዚህም ዛሬ ሚያዝያ 08/2018 በአዳም ሐሙስ ዕለት መታሰቢያ በዓል ለበርካታ ወገኖች ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ የምሳ ምገባ መርሐግብር ተካሂዷል።

በተመሳሳይ በበዓሉ ዋዜማ አቅመ በአጥቢያችን ለሚገኙ አቅመ ደካማ ወገኖችም የበዓል መዋያ ገንዘብ፣ ዶሮ፣ እንቁላል እና ዘይት ድጋፉ ተደርጓል።

በመሆኑም ሰንበት ትምህርት ቤታችን በተለያዩ ዘርፎች የምታከናውነውን የበገ አድራጎት ተግባራት ለማገዝ የምትፈልጉ ወገኖች በአሐዱ ባንክ በንግድ ባንክ - 1000755994522 መኮንን ደሳለኝ እና ወይም ትብለጥ ዓለማየሁ በሚል ድጋፍ መላክ ይችላሉ።

ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ!

Address

Merkato
Addis Abeba
1000/51419

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ክ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት:

Share