ከገድላት አንደበት-ke gedilat andebet

ከገድላት አንደበት-ke gedilat andebet ከኢ/ኦ/ተዋሕዶ ቤ/ክ ገድላት ላይ የተገኙ የቅዱሳን አባቶቻችን እና የቅዱሳት እናቶቻችን ገድላቸው በየቀኑ ይነገርበታል!

‹‹...በቀናች ሃይማኖት ሆኖ ስሟን መጥራት ወድቆ የሚፍገመገመውን ያነሣል፣ ኀጥኡንም ጻድቅ ያደርጋልና፡፡ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምት...
22/08/2026

‹‹...በቀናች ሃይማኖት ሆኖ ስሟን መጥራት ወድቆ የሚፍገመገመውን ያነሣል፣ ኀጥኡንም ጻድቅ ያደርጋልና፡፡ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን የክብርት እመቤታችንን ስም የሚጠራ አንደበት ምንኛ የተባረከ ነው፡፡ እንደምን ያመልጥ! እንደምንስ ከመከራ ሁሉ ይድን ዘንድ ምንኛ ዕድለኛ ይሆን! እንደምን ከፍ ከፍ ይል! ይህ ስም ከሁሉ ይልቅ እንደምን የተከበረ ነው፡፡ በቃልኪዳን ውኃ ያነጻን ዘንድ ጻድቃንም ለመሆን ወደ እርሷ ለሚገቡ ኀጥአን አማላጅ ይሆን ይሆን ዘንድ በቃልኪዳን ቀለም በመንግሥተ ሰማያት በር የተጻፈ ነውና፡፡

አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የክብርት እመቤታችን ቃልኪዳን የተጀመረ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካረገ በኋላ አይደለም፡፡ አዳም ከገነት ከወጣና ከከብሩም ከተለየ ጀምሮ ነው እንጂ፡፡ ፈጽሞ ባለቀሰ ጊዜ ጌታችን አለኝታ ባለው ቃልኪዳን ‹ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ተሰቅዬ ሙቼ አድንሃለሁ› ብሎታልና፡፡ እመቤታችንን የዓለሙ ሁሉ መድኀኒት አድርጎ እንደፈጠራት ልብ አድርጋችሁ እነሆ ዕወቁ፡፡

ሁለተኛም ከሁሉ ይልቅ ከቸር ፈጣሪያችን በተሰጧት ኪዳናት ሁሉ ለእስራኤል ደኅንነት ትሆን ዘንድ ለሙሴ የተሰጠው ሕጉ የተጻፈበት ጽላት ያለበት መጠጊያ ብሎ ስም እንዳወጣለት ዕወቁ፡፡ የተወደዳችሁ የክርስቶስ ወገኖች ሆይ! አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የክብርት እመቤታችን ስም አጠራር የማዳኑን ኃይል እንነግራችሁ ዘንድ ስሙ፡፡

አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ለነቢያት፣ ለሐዋርያት፣ ለጻድቃንና ለሰማዕታትም ሁሉ እመቤታቸው ናት-የእርሷ ቃልኪዳን ፍጻሜያቸው ነውና፡፡ በእርሷ ሥጋ መስቀልን አሳስቦ ከመናገሩ የተነሣ ምንም ለእነዚህ ክቡራን ሁሉ ቃልኪዳን ቢሰጣቸው የቃልኪዳን መመኪያ አክሊል እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ ይህን ቃልኪዳን በመስማት አምነው አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች የክብርት እመቤታችንን ስም በመጥራት የዳኑትን ስንቱን እንነግራችኋለን፡፡ የተአምራቷ ኃይል ከሰማይ ከዋክብት ከባሕር አሸዋ እጅግ የበዛ ነውና፡፡ ልመናዋ ክብሯ ለዘለዓለሙ በዕውነት በሁላችን በተዋሕዶ ልጆች ላይ አድሮብን ይኑር››

"የገነት ዛፍ ማርያም ሆይ፤ ልጅሽ በክንዱ ዐቅፎ በአፉ እየሳመ በቀኙ ሊያሳርፍሽ ባሳረገሽ ጊዜ፤ አንቺን ለመቀበል ክንፍ ለክንፍ እየተጋጩ እልፍ አእላፋት መላእክት ወረዱ፡፡ መላእክት በየነገድ በየነገድ ኾነው በመባርቅት ክንፎች እንደ ጋሻ ጋርደው ከኤዶም ገነት በተቀበሉሽ ጊዜ የሚያስደንቅ ክብር ለተገለጸባት ለክብርት ዕርገትሽ ሰላምታ ይገባል!!!

እንኳን ለእመቤታችን የዕርገት በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!

‹‹ጽድቅ ያለ ጭንቅ መከራ አትገኝም››በዚኽች ዕለት በዓመታዊ የዕረፍታቸው በዓል ስታስበው የሚውሉት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ፊሊጶስ ዘደብረ ቢዘን ወደ ዋልድባ ሔደው ከአቡነ ሳሙኤል ጋር በመገናኘት...
11/08/2026

‹‹ጽድቅ ያለ ጭንቅ መከራ አትገኝም››
በዚኽች ዕለት በዓመታዊ የዕረፍታቸው በዓል ስታስበው የሚውሉት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ፊሊጶስ ዘደብረ ቢዘን ወደ ዋልድባ ሔደው ከአቡነ ሳሙኤል ጋር በመገናኘት የጽድቅን ነገር ተነጋገሩ፡፡ በዚያም ተቀምጠው በሰንበት ቀን ከቅጠልና ዕንጨት ፍሬዎች በቀር እህል ሳይቀምሱ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾሙ፡፡ ሲጸልዩ በልቅሶና በኀዘን ስለሆነ ከልቅሷቸው ብዛት የተነሣ ዐይኖቻቸው ደፈረሱ፣ ሲሰግዱም በአራቱም አቅጣጫ አንድ አንድ ሺህ ይሰግዳሉ፡፡ ከታላቅ ተጋድሏቸውም ብዛት የተነሣ የሰውነታቸው ቆዳ ከአጥንታቸው ጋር ተጣበቀ-በረኀብና በጥም ሥጋቸው አልቋልና፡፡ እንዲህ ባለ ታላቅ ተጋድሎ በዋልድባ ከአቡነ ሳሙኤል ጋር ከተቀመጡ በኋላ ወደ ሌላ በረሓ ወጥተው ሔዱ፡፡

በመንገድም ሳሉ ደክመው ሲወድቁ ይጠብቃቸው የነበረው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦ ‹‹…ጽድቅ ያለ ጭንቅ መከራ አትገኝምና በርታ›› ብሎ አበረታቸውና ሁልጊዜም ከእርሳቸው እንደማይለይ ነገራቸው፡፡ በመንገድም እየተጓዙ ሳሉ አራዊት እየመጡ ሰገዱላቸው፡፡ አንዲት ዋሻን አግኝተው በውስጧ በኣታቸውን ሊያበጁ ሲሉ ስለደከሙ መቆፈር ቢሳናቸው አንበሳ መጥቶ በቁመታቸው ልክ ጉድጓድ ቆፈረላቸውና መርቀው ሸኙት፡፡ አቡነ ፊሊጶስም በዚያች ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ሥጋቸውን ዘመሚቶች በልተው እስኪጨርሱት ድረስ ቆመው 40 ቀንና 40 ሌሊት ጸለዩ፡፡ የ40 ቀኑንም ሱባኤያቸውን በጨረሱ ጊዜ መልአኩ ተገልጦ ‹‹…ጽድቅ የሚገኘው ከመከራ በኋላ ነውና አሁን ግን ይበቃሃል ና ውጣ›› ብሎ በእጆቹ ስቦ ከጉድጓዱ አውጥቶ ሰውነታቸውን በክቡራን እጆቹ ዳስሶ ቊስላቸውን አዳነላቸው፣ ሥጋቸውም እንደታናሽ ልጅ ሥጋ ሆነ፡፡

ዳግመኛም አባታችን ፊሊጶስ ወደ ሌላ በረሓ ገብተው ሰውነታቸውን በሰሌን ቅጠል እየገረፉ፣ በእሾህ ጨፈቃ (ክምር) ላይም እስከ ሦስት ቀን ተኝተው እየቆዩ ሰውነታቸውን ድጋሚ ይጎዱ ጀመር፡፡ ከመከራውም ብዛት የተነሣ ነፍሳቸው ልትወጣ በደረሰች ጊዜ ጌታችን ከነቢያት ማኅበር፣ ከመላእክት ማኅበርና ከመነኰሳት ማኅበር ጋር ተገልጦ በቃሉ አረጋግቶ ቊስላቸውን ፈውሶ ሰውነታቸውን አደሰላቸውና ‹‹…በዚህ ዓለም የደከመ ሰው ለዘለዓለሙ ይድናል›› ብሎ በከንፈሮቹም ሳማቸውና ቃልኪዳን ከገባላቸው በኋላ በታላቅ ክብርና ምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡

አቡነ ፊሊጶስ ዳግመኛ ወደ ሌላ በረሓ ገብተው በኣት አበጅተው መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰጣቸው እሾሃማ ብረቶች ሰውነታቸውን እየጎዱ ከብረት የተሠራ የእሾህ ጫማም እየተጫሙ ደማቸው እየፈሰሰ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስኪወድቅ ድረስ እስከ 30 ዓመታቸው ድረስ በእንዲህ ያለ ታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችንም ዳግመኛ በዚህ በረሓ ውስጥ ሳሉ ተገልጦ ሰውነታቸውን ዳስሶ ከፈወሳቸው በኋላ ‹‹ለብዙዎች አባት ትሆናለህ፣ በትምህርትህ ብዙዎች ይድናሉ›› በማለት ከዚህ ቦታ ወጥተው መነኰሳትን ሰብስበው እንዲያስተምሩ አዘዛቸው፡፡ ከዚህም ቦታ ወጥተው ጺዳርዋ ወደሚባል በረሓ ውስጥ ወደሚገኝ ገዳም ሲጓዙ ሥሉስ ቅዱስ በሦስት ሰዎች አምሳል ተገለጡላቸውና ፊት ለፊት አነጋገሯቸው፤ መንገዱንም እየመሩ ወስደው ጎዳህ ከተባለው ቦታ አድርሰዋቸው ተሠወሩ፡፡

ዳግመኛም አባታችን ፊሊጶስ እሳት ከሰማይ አውርደው የሐይቅን ባሕር ካነደዷት በኋላ
ሌላ ታላቅ ተኣምርን ማድረግ በወደዱ ጊዜ ከመነኰሳት ልጆቻቸው ውስጥ አንዱን ሉቃስ የተባለውን ጠርተው ወደሌላ ሀገር ሔዶ መልእክት እንዲነግር አዘዙት፣ ሉቃስም ‹‹አባቴ ሆይ! ታንኳ ማን ይሰጠኛል?›› ሲላቸው ሰማዕቱ አቡነ ፊሊጶስም ‹‹ጫማህን አድርግና በባሕሯ ላይ ተራመድ፣ አትፍራ መስቀልህን በላይዋ ላይ አመልክት፣ እርሷም እንደ ደረቅ ምድር ትሸከምሃለች፣ ከእርሷም ወጥተህ በመንገድ ላይ አንበሳ ታገኛለህ እርሱም ይረዳሃል›› አሉት፡፡ ልጃቸው ሉቃስም በቃላቸው ታምኖ ሔደና ጫማውን አድርጎ ጫማዎቹ ሳይርሱ እንደ ደረቅ ምድር ባሕሯን እየጠቀጠቀ ሲሔድ ይህንንም የተመለከቱ ሁሉ እጅግ አደነቁ፡፡ የሀገሩ ሰዎችም ‹‹የደብረ ቢዘኑ መምህር ሰማዕቱ አቡነ ፊሊጶስ የሚያስደንቅ ተኣምር አድርጎ ባሕሯን አቃጠላት፣ ዳግመኛም ተማሪዎቹን በጫማ ባሕርን እየጠቀጠቁ በባሕር ላይ እንዲሔዱ ያዛል›› ብለው ለንጉሡ ለዐፄ ዳዊት መልእክት ላኩ፡፡

ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም መልእክተኛ በመላክ ‹‹…አባቴ ሆይ! እርስዎ እውነተኛ ሰው እንደሆኑ እኔ ዐውቄያለሁና በእውነት የደብረ ቢዘን መምህር አባቴ ፊሊጶስ ሆይ! ሰማዕት ነዎትና ዜና ገድልዎም ግሩም ነው እኔም በጸሎትዎ ተማጽኛለሁና መጥተው ልጆቼን መንግሥቴን ይባርኩልኝ›› ብሎ መልእክት ላከላቸው፡፡ አባታችንም ‹‹…አንተስ በመጀመሪያ ትምህርቴን አልወደድክም ነበር ነገር ግን ከሚስትህ ከእግዚእ ክብራና ከአንተ የሚወለድ የተመረጠና የተባረከ ልጅ አለ፤ እርሱም የመንግሥትህ ወራሽ ነው፣ በእርሱ ዘር መንግሥትህ ትጸናለች፣ ከእርሱም በፊት ከእርሱም በኋላ ሃይማኖቱ የቀና እንደ እርሱ ያለ የለም፤ እርሱ ሥርዓቴን ይወዳል፣ ገዳሜንም ያከብራል፣ ልጆቼንም ይወዳል›› ብለው ስለ ልጁ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ትንቢትን ነገሩት፡፡ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም ይህንን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው፡፡

ዳግመኛም ንጉሡ ወደ እርሱ መጥተው ብዙ ወርቅንና ብርን ሀገሮችንም የፈለጉትንም ነገር እንዲወስዱ መልእክት ላከባቸው፡፡ ንግሥቲቱ እግዚእ ክብራም ‹‹ሰማዕቱ አባቴ ፊሊጶስ ሆይ! በጸሎትህ ተማጽኛለሁ፣ ስለዚያ ስላልከው ልጅም አጥቤ እጠጣው ዘንድ የእግርህን ትቢያ እንድትሰጠኝ በአምላክህ በእግዚአብሔር አምልሃለሁ…›› ብላ መልእክት ላከችላቸው፡፡ አባታችንም ‹‹ልጅ በምትወልጂ ጊዜ ስሙን ዘርዐ ያዕቆብ ብለሽ ጥሪው›› አሏት፡፡ ለንጉሥ ዳዊትም ‹‹እኔ ብርህንና ወርቅህን አልፈልግም፣ እኔ ገዳማዊ መነኵሴ ነኝና ሀገሮችህንም አልሻም፣ ጸሎት ግን አባቶች ሐዋርያት እንዳዘዙኝ ለአንተ እጸልይልሃለሁ፣ ንጉሥ ሆይ! በሃይማኖትህ የቀናህ ሁን፣ እግዚአብሔርም ከአንተ ጋር ይሁን›› አሉት፡፡ ከዚኽም በኋላ ዘርዐ ያዕቆብ ተወለደና በሰማዕቱ በአቡነ ፊሊጶስ በእግሩ እጣቢ ጸበል እንደተወለደ እናቱ ነገረችው፡፡ አቡነ ፊሊጶስ እንደነገሯትና በእርሷ ላይ የሆነውን ሁሉ ለልጇ ዘርዐ ያዕቆብ ነገረችው፡፡ እርሱም የደብረ ቢዘን ገዳም መነኰሳትን የሚወዳቸው ሆነ፡፡

ዛሬ ላይ የመናፍቃንን ሀሳብ የሚያራምዱ በቤታችን ያሉ አንዳንድ ርዝራዥ ሰዎች ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብን ይቃወማሉ። አለማወቅ በድንግዝግዝ ጨለማ ውስጥ እንደሚጓዝ ነው፤ ግን ደግሞ የማያውቁት ነገር እንደ ዕውቀት ቆጥሮ መናገር ራሱን የቻለ ድንቁርና ነውና ቤተክርስቲያናችንን እና ሀገራችንን በትክክል ዕንወቅ፣ ትክክለኛው ዕውቀት እርሱ ብቻ ነው። ሌላው ሁሉም ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው "የውሸት ዕውቀትና ከንቱ መለፍለፍ ነው።"

ፎቶው አቡነ ፊሊጶስ የመሠረቱት ሰሜናዊ ቀይ ባሕር የሚገኘው "ደብረ ቢዘን አቡነ ፊሊጶስ አንድነት ገዳም" ነው። ጻድቁ ከጽኑ ተጋድሎአቸው በኃላ በዛሬዋ ዕለት በዕረፍታቸው ጊዜ ነሐሴ 5 ቀን ጌታችን ተገልጦላቸው እንዲህ አላቸው፡- "... ወዳጄ የከበርክ ፊሊጶስ ሆይ! በሰማይና በምድር ያሉትን ምሥጢራት ኹሉ የሰማንያ አንዱንም የቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢራት ገልጨልሃለሁ፡፡ እኔ በቸርነቴ ገለጽኩልህ እንጂ አንተ በምልክት ከመምህር የተማርክ አይደለህምና ስምህ 'ፋድል ፊሊጶስ' ይሁን" አላቸው፡፡ "ፋድል" ማለት ያልተማረ (ፊደል ያልቆጠረ) ማለት ነው፡፡
(ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ፊሊጶስ ዘደብረ ቢዘን አንዳዴ ባሕር)

የደብረ ቢዘኑ አቡነ ፊሊጶስ እጅግ ብዙ መነኮሳትን በቆብ ስለወለዱ ልክ እንደነ አቡነ ተክለሃይማኖት እና እንደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ "ወላዴ አእላፍ" ተብለዋል፡፡ የከበሩ የአቡነ ፊሊጶስና የልጆቻቸው ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

በሱባዔ፣ በምሕላ፣ በምጽዋት፣ በጸሎት፣ በስግደት በመትጋት መዋዕለ ጾሙን በየገዳማቱ ካሉት አባቶቻችንና እናቶቻችን ጋር እንተባበር ዘንድ የፈቀደልን የጊዜ ባለቤት ልዑል እግዚአብሔር ይክበር ይ...
07/08/2026

በሱባዔ፣ በምሕላ፣ በምጽዋት፣ በጸሎት፣ በስግደት በመትጋት መዋዕለ ጾሙን በየገዳማቱ ካሉት አባቶቻችንና እናቶቻችን ጋር እንተባበር ዘንድ የፈቀደልን የጊዜ ባለቤት ልዑል እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን!!!

የአምላክ እናት ክብርት እመቤታችን ዕርገቷን ለማየት ታብቃን! የቤተ ክርስቲያናችንን እና የሀገራችንንም ትንሣኤ ታሳየን።
መልካም ሱባኤ!!!

አቡነ ተክለ ሃይማኖትና የቆብ ልጃቸው አቡነ ዮሐንስ አብረው በጎንድ በታላቅ ተጋድሎ ይኖሩ ነበርና በአንደኛው ዕለት ወጥ እየሠሩ ሣለ ወጡ ሊገነፍል ሲል አቡነ ተክለ ሃይማኖት ማማሰያ ሊያመጡ ...
05/08/2026

አቡነ ተክለ ሃይማኖትና የቆብ ልጃቸው አቡነ ዮሐንስ አብረው በጎንድ በታላቅ ተጋድሎ ይኖሩ ነበርና በአንደኛው ዕለት ወጥ እየሠሩ ሣለ ወጡ ሊገነፍል ሲል አቡነ ተክለ ሃይማኖት ማማሰያ ሊያመጡ ይሔዳሉ፡፡ እርሳቸውም ማማሱውን ይዘው ሲመለሱ አቡነ ዮሐንስ ግን እሳቱም ወጡም ሳያቃጥላቸው በእጃቸው እያማሰሉት ነበር፡፡ ከዚኽም በኋላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ‹‹ይኽ ቦታ ከእኔ ይልቅ ለአንተ የተገባ ነው›› ብለው ተሰናብተወቸው ከጎንድ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሔዱ፡፡

አቡነ ዮሐንስም ጉንድ ተክለ ሃይማኖት ገዳምን በአባታቸው በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ስም ሰይመውት ገዳሙን አቅንተው በቦታው ላይ በታላቅ ተጋድሎ ኖሩ፡፡ ገዳሙም ዛሬ ‹‹ጉንድ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም›› ተብሎ ይጠራል፡፡ አቡነ ዮሐንስ ዘጠገሮ ጨረቃንና ፀሐይን በእጃቸው እየያዙ ይጸልዩ የነበሩ በመንዝ በይፋት ያሉ ክርስቲያኖች ብርዱን ውርጩን በስማቸው የሚገዝቱባቸው ታላቅ የበረከት አባት ናቸው፡፡

በኢየሩሳሌም ለ50 ዓመት፣ በሀገራችን ኢትዮጵያ ለ450 ዓመታት ኑረዋል፡፡ ዕጨጌ ዮሐንስ በአንድ በዓት ተወስነው የሚቆዩት ለ50 ዓመት ነበር፡፡ በሀገራችን 5 የተለያዩ በዓቶች ነበሯቸው፡፡ በደብረ ሊባኖስ፣በጠገሮ፣ በአዘሎ፣ በፍርኩታና በሌሎቹም ታላላቅ ቦታቦዎች ላይ በእያንዳንዱ ገዳም ሃምሳ ሃምሳ ዓመት በጸሎት ኖረው በአጠቃላይ በ500 ዓመታቸው ነው በዛሬዋ ዕለት ያረፉት፡፡ ዐፅማቸው መንዝ ከአርባ ሐራ መድኃኔዓለም አጠገብ ፍርኩታ ኪዳነ ምሕረት ገዳም ውስጥ ይገኛል፡፡ አቡነ ዮሐንስ ዘጠገሮ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

+ + +

በውስጥ መስመር የምትልኳቸውን መልእክቶች ከመብዛታቸው የተነሣ ኹሉንም ከፍቼ ማንበብ እስከማልችልበት ድረስ ተቸግሬአለሁ። ስትደውሉም ስትጽፉም ላልመለስኩላችሁ ኹሉ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ!!!

ይመስለኛል የዐውደ ርእይው የመጨረሻ ዕለት "የተለየ ችግር ያጋጠማችሁ እኅት ወንድሞች ካላችሁ በውስጥ መስመር ማስታወሻ አስቀምጡኝ በምትፈልጉት መልኩ እረዳችኋለሁ" በማለቴን ተከትሎ በጣም ብዙዎቻችሁ ስልክ በመደወል መልእክት በመጻፍ "...ደመወዝ የሚገባልን በ30 ነው፤ ከሐምሌ 26 በፊት ምንም ማድረግ ስለማንችል እባክህ የፓኬጅ ዕድሉ አይለፈን፤ የኾነ መፍትሔ ካለህ...." ብላችሁኛል።

ስለዚኽ እኔም እሑድ ሌሊቱን ከኅሊናዬም ተማክሬ የእናንተንም ኀሳብ አክብሬ ይኽን ወሰንኩ፦ ፓኬጁን ጨምሮ ዐውደ ርእዩ ላይ የነበረውን እጅግ ታላቅ ቅናሽ እንደዛው እንዳለ እስከ ነሐሴ 1 ቀን ድረስ አራዝሜላችኋለሁ። ወደ ቢሮ እየሔዳችሁ ዐውደ ርእይ ላይ በነበረው ዋጋ መውሰድ ትችላላችሁ። ፓኬጁም እንደዛው እንደነበረው ነው። ከነሐሴ 2 በኋላ ግን ኹሉም ዋጋ ወደነበረበት ይመለሳል። በተለይ መልክዐ ጉባኤው አጠቃላይ የታተመው እያለቀ ስለኾነ ይኽ ወርቃማ ዕድል አይለፋችሁ በእውነቱ! ለወዳጅ ዘመዶቻችሁም አሳውቁ።

አድራሻ፦ ከፒያሳ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተሻግሮ ወደ ሽሮሜዳ (ፈረንሳይ) (6 ኪሎ) ታክሲ መያዣ ከፍ ብሎ ውቤ በረሓ አፓርትመንት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. S8

ለተጨማሪ መረጃ፦
0912063211/0925119240

በውስጥ መስመር የምትልኳቸውን መልእክቶች ከመብዛታቸው የተነሣ ኹሉንም ከፍቼ ማንበብ እስከማልችልበት ድረስ ተቸግሬአለሁ። ስትደውሉም ስትጽፉም ላልመለስኩላችሁ ኹሉ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ!!!...
03/08/2026

በውስጥ መስመር የምትልኳቸውን መልእክቶች ከመብዛታቸው የተነሣ ኹሉንም ከፍቼ ማንበብ እስከማልችልበት ድረስ ተቸግሬአለሁ። ስትደውሉም ስትጽፉም ላልመለስኩላችሁ ኹሉ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ!!!

ይመስለኛል የዐውደ ርእይው የመጨረሻ ዕለት "የተለየ ችግር ያጋጠማችሁ እኅት ወንድሞች ካላችሁ በውስጥ መስመር ማስታወሻ አስቀምጡኝ በምትፈልጉት መልኩ እረዳችኋለሁ" በማለቴን ተከትሎ በጣም ብዙዎቻችሁ ስልክ በመደወል መልእክት በመጻፍ "...ደመወዝ የሚገባልን በ30 ነው፤ ከሐምሌ 26 በፊት ምንም ማድረግ ስለማንችል እባክህ የፓኬጅ ዕድሉ አይለፈን፤ የኾነ መፍትሔ ካለህ...." ብላችሁኛል።

ስለዚኽ እኔም እሑድ ሌሊቱን ከኅሊናዬም ተማክሬ የእናንተንም ኀሳብ አክብሬ ይኽን ወሰንኩ፦ ፓኬጁን ጨምሮ ዐውደ ርእዩ ላይ የነበረውን እጅግ ታላቅ ቅናሽ እንደዛው እንዳለ እስከ ነሐሴ 1 ቀን ድረስ አራዝሜላችኋለሁ። ወደ ቢሮ እየሔዳችሁ ዐውደ ርእይ ላይ በነበረው ዋጋ መውሰድ ትችላላችሁ። ፓኬጁም እንደዛው እንደነበረው ነው። ከነሐሴ 2 በኋላ ግን ኹሉም ዋጋ ወደነበረበት ይመለሳል። በተለይ መልክዐ ጉባኤው አጠቃላይ የታተመው እያለቀ ስለኾነ ይኽ ወርቃማ ዕድል አይለፋችሁ በእውነቱ! ለወዳጅ ዘመዶቻችሁም አሳውቁ።

አድራሻ፦ ከፒያሳ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተሻግሮ ወደ ሽሮሜዳ (ፈረንሳይ) (6 ኪሎ) ታክሲ መያዣ ከፍ ብሎ ውቤ በረሓ አፓርትመንት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. S8

ለተጨማሪ መረጃ፦
0912063211/0925119240

ደብረ መድኃኒት አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አንድነት ገዳም! በዚኽች ዕለት ሐምሌ 26 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ስታስበው የሚውሉት ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ያደረጉት ታላቅ ተአምር ይኽ...
02/08/2026

ደብረ መድኃኒት አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን አንድነት ገዳም!
በዚኽች ዕለት ሐምሌ 26 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓላቸው ስታስበው የሚውሉት ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ያደረጉት ታላቅ ተአምር ይኽ ነው፦ ‹‹ምንም ሳያስታጉል በየቀኑ ዕጣን የሚያሳርግ ወደ እግዚአብሔር መጸለይን የሚያበዛ ለአቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ቤተ ክርስቲያን የሚላላክ አንድ መነኩሴ ነበር፡፡ ከዕለታትም በአንዲት ቀን እንቅልፍ መጥቶበት ተኝቶ ሳለ በዚያች ዕለት ሕልመ ሌሊት አገኘው፡፡ ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ሕልመ ሌሊት እንዳገኘው አይቶ ስለ አቡነ ሰላማ ቤ/ክ ማዕጠንት መታጎል ታላቅ ኀዘን አዘነ፡፡ ያንጊዜም ሰይጣን ከሰይጣን ጋራ ‹‹…ወዳጄ ይህን መነኩሴ ዛሬ ጣልኩት፣ ከአገልግሎቱም አስታጎልኩት አየህን!›› እያለ ሲናገር ሰማው፡፡ ሌላኛውም ሰይጣን መልሶ ‹‹…ወዳጄ መልካም አድርገሃል፣ መጥጠተህ አፌን ሳመኝ›› አለውና ሁለቱም እርስ በእርሳቸው አፍ ለአፍ ሲሳሳሙ ያ መነኩሴ ይህን አይቶና ሰምቶ በመናደድ ድጋሚም በዚህ እንዳይፈተን በማሰብ ስለት ባለው ምላጭ አባለ ዘሩን ቆርጦ ጣለውና የብልቱን ቁራጭ ወደታላቅ ገደል ወረወረውና ለሰይጣን ‹‹ይህን እንካ እንደውሻ ቆጥሬልሃለሁና›› አለው፡፡

ሰይጣኑም ወዲያው በዱር አሞራ ተመስሎ የብልቱን ቁራጭ ጠልፎ ወሰደ፡፡ ነገር ግን የእግዚብሔር ሰው ድንቅ ተአምራትንም የሚያደርግ አባታችን ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ወዲያው ታላቅ የሆነ ነጭ ንስር መስሎ እየበረረ ሔዶ የመነኩሴውን የብልቱን ቁራጭ ከሰይጣን አፍ ቀምቶ ያንን ሰይጣን በሰይፍ ቆረጠውና ወደ አገልጋዩ መነኩሴ ቢሔድ ስለአገልግሎቱ መታጎል እያዘነ አገኘው፡፡ አባታችንም ‹‹…ወዳጄ አገልጋዬ ሆይ! እነሆ የሰውነትህን ብልት እንካ እንደቀድሞው ከሰውነትህ መልሼልሃሁ፤ እግዚአብሔር የፈጠረውን አካል ዳግመኛ አትቁረጥ፣ አስቀድሞም ከነበሩ በኋላም ከሚነሡ ይህንን ፈተና ታግሠው ካላላፉ ጽድቅ የለምና በቤተ ክርስቲያን ክህነትና ማዕረግ አይኖርህምና አካልህን አታጉድል፣ ሳትመረር ፈተናውን ታገሥ እንጂ፡፡ ያለመከራና ያለሥቃይ ጸጋ አትገኝምና…›› እያለ ከመከረው በኋላ ብፁዕና ቅዱስ ማር አቡነ ሰላማ ከመነኩሴው ተሰውሮ ዐረገ፡፡

ከዚህ በኋላ ያ መነኩሴ ፈጽሞ ፈጣሪውን አመሰገነ፡፡ እስካረፈበት ዕለት ድረስ ጸሎትን አበዛ፡፡ በሞት ባረፈም ጊዜ በአባታችን ጸሎት መንግሥተ ሰማያትን ወረሰ፡፡›› (ገድለ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ገጽ 81-82)

አባታችን ባረፈ ጊዜ በዚህ አስደናቂ ገዳም ላይ ራሱ ጌታችን በአካል ለአባታችን ተገልጦላቸዋል፡፡ አባታችን ማር ሰላማም ቡሩካን በሆኑ እጆቹ ምድሪቱን እንደመሶብ አንሥቶ በሥሉስ ቅዱስ መንበር ፊት አቅርቦ አስባርኳታል፡፡ የገዳሙ አቀማመጥ እጅግ አስገራሚ ነው-ልክ እንደ ግሸን መስቀለኛ ቅርጽ ያለው ሲሆን በአራቱም አቅጣጫ የተለያዩ ምሥጢራት አሉት፡፡ በገዳሙ ምዕራባዊ ክፍል አስደናቂው ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ፣ በስተምሥራቅ የጻድቁ ቅዱስ መካነ መቃብር፣ በስተደቡብ መግቢያ በሩ፣ በስተሰሜን ጻድቁ ከዐለት ላይ ያፈለቋቸው ፈዋሽ ጠበሎች ይገኛሉ፡፡

ለማር አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ከሰማይ የወረደላቸው የእጅ መስቀላቸውና ቅዱስ መካነ መቃብራቸው በዚሁ ገዳም ይገኛሉ፡፡ ታላቅ ጻዲቅ፣ መናኝ፣ ሐዋርያ፣ ጳጳስ....የሆነው ማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን በድፍን ኢትዮጵያ በአራቱ አቅጣጫ እየዞረ በተአምራቱ ድውያንን እየፈወሰ፣ ሙታንን እያስነሣ፣ ወንጌልን እያስተማረ፣ እያጠመቀ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እየሠራና አገልጋይ የሚሆኑ ቀሳውስትን እየሾመ በሀገራችን ላይ ብርሃንን የፈነጠቀ ለኢትዮጵያ መግለጽ ከሚቻለው በላይ ታላቅ ባለውለታዋ ነው፡፡ ከአቡነ ሰላማ በፊት እኛ ኢትዮጵያውያን ክርስቶስን ከማመን በቀር ጥምቀትና ሥጋ ወደሙ የመቀበል ልማድ አልነበረንም፡፡ በድንኳን ካለችው ታቦተ ጽዮን በቀርም ታቦታትና አብያተ ክርስቲያናትም ፈጽሞ አልነበሩንም፡፡ ይህን ሁሉ ያገኘነው በማር ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ነው፡፡ ይሄ ሁሉ ሲታሰብ ከአባ ሰላማ ውለታ አንጻርና እንደሠራላት እጅግ ታላቅ ሥራ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ጻድቁን እንደሚገባው መጠን አላከበረችውም ማለት ይቻላል፡፡ ጌታችንም በመጨረሻ ቃልኪዳን ሲሰጠው ‹‹ስለ ትምህርትህና ስለ ስብከትህ ኢትዮጵያን ከጨለማ አውጥተህ በሃይማኖት ስለ አበራሃት ከፍ ያሉ ክብራትንና ማዕረጋትን ፈጽሜ ሰጠሁህ›› ነው ያለው፡፡

የማር አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

(በአ.እ ኤግዚቢሽን ማዕከል ለ4 ቀናት የተዘጋጀው የመጻሕፍት ዐውደ ርእይ ነገ እሑድ (ሐምሌ 26) የመጨረሻው ዕለት ስለኾነ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ እስከ ምሽት 1:00 ድረስ ባለው ጊዜ የመጨረሻውን ዕድል ተጠቀሙ። ከሰኞ በኋላ ዋጋው ወደነበረበት ይመለሳል። የተለየ ችግር ያጋጠማችሁ እኅት ወንድሞች ካላችሁ በውስጥ መስመር ማስታወሻ አስቀምጡኝ በምትፈልጉት መልኩ እረዳችኋለሁ።)

እመቤታችንና ጠባቂዋ የነበረው የ83 ዓመቱ አረጋውያን ዮሴፍ በግብፅ ሳሉ ግብፃውያን እንደ ሕጋቸው ለአማልክቶቻቸው ላሞችን አርደው ሠውላቸው፡፡ በጎሽ፣ በአውራሪስ፣ በነጭ ዝንጀሮ የሚመሰሉ አጋ...
02/08/2026

እመቤታችንና ጠባቂዋ የነበረው የ83 ዓመቱ አረጋውያን ዮሴፍ በግብፅ ሳሉ ግብፃውያን እንደ ሕጋቸው ለአማልክቶቻቸው ላሞችን አርደው ሠውላቸው፡፡ በጎሽ፣ በአውራሪስ፣ በነጭ ዝንጀሮ የሚመሰሉ አጋንንትም መጡ፡፡ እመቤታችንም ከሩቅ ሆና ተመልክታቸው እነዚያን አጋንንት በጸሎቷ እንደጢስ በተነቻቸው፡፡ ግብፃውያንም ፈርተው እየጮኹ ሸሹ፡፡ በዚያም ወራት ‹‹ረዳት አማልክቶቻችንን ጠፉብን›› ብለው እያዘኑ ሳለ ዮሴፍን ሲጸልይ አግኝተውት አስረው በምድር ላይ አስተኝተው 40 ግርፋት ገረፉት፡፡ እርሱም በዚህ ጊዜ ‹‹እመቤቴ ሆይ ስለ አንቺና ስለ ልጅሽ ይህ መከራ አግኝቶኛልና እርጂኝ›› ብሎ በኀይል ጮኸ፡፡ እመቤታችንም ድምጹን ስትሰማ የሄሮድስ ጭፍሮች የመጡ መስሏት እጅግ ደነገጠች፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ተገልጦ ካረጋጋት በኋላ ዮሴፍን በኀይል ይደበድቡ የነበሩትን በእሳት ሰይፉ ጨረሳቸው፡፡ ዮሴፍንም በእጆቹ ዳሰሰውና ፈወሰው፡፡ እመቤታችንም ዮሴፍን ባየችው ጊዜ ‹‹ይህ ሁሉ መከራ ያገኘህ በእኔና በልጄ ምክንያት ነው›› ብላው አንገት ለአንገት ተቀቅፈው ተላቀሱ፡፡ መልአኩም ‹‹ይሄ ሀዘናችሁ በደስታችሁ ጊዜ ይረሳል…›› እያለ አረጋጋቸውና ዐረገ፡፡

ጌታችንን በእጆቹ ሥራ እየመገበ እንደ አባት ሆኖ ያሳደገው የአረጋዊው የቅዱስ ዮሴፍ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

(በአ.እ ኤግዚቢሽን ማዕከል ለ4 ቀናት የተዘጋጀው የመጻሕፍት ዐውደ ርእይ ነገ እሑድ (ሐምሌ 26) የመጨረሻው ዕለት ስለኾነ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ እስከ ምሽት 1:00 ድረስ ባለው ጊዜ የመጨረሻውን ዕድል ተጠቀሙ። ከሰኞ በኋላ ዋጋው ወደነበረበት ይመለሳል። የተለየ ችግር ያጋጠማችሁ እኅት ወንድሞች ካላችሁ በውስጥ መስመር ማስታወሻ አስቀምጡኝ በምትፈልጉት መልኩ እረዳችኋለሁ።)

"ንባብ ለሕይወት" የመጻሕፍት ዐውደ ርእይበአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከሐምሌ 23-26 (ከሐሙስ-እሑድ) ለአራት ቀናት ብቻ  ስለሚካሔድ እጅግ አስገራሚ የኾነ ፓኬጅ በታላቅ ቅናሽ አዘጋጅ...
29/07/2026

"ንባብ ለሕይወት" የመጻሕፍት ዐውደ ርእይ
በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል
ከሐምሌ 23-26 (ከሐሙስ-እሑድ) ለአራት ቀናት ብቻ ስለሚካሔድ እጅግ አስገራሚ የኾነ ፓኬጅ በታላቅ ቅናሽ አዘጋጅተናል። መቼም ቢኾን ድጋሚ የማይገኝ ዕድል ስለኾነ ለመጨረሻ ጊዜ ተጠቀሙበት።

፩. በማጠሪያ ሽያጭ መልክዐ ጉባኤው ከቨሩ ብቻ የተጎዳውን በ7ሺህ ብር ብቻ!!! (ከኹለቱ አንደኛው ቅጽ ምንም ዓይነት የከቨር እንከን የሌለው ነው። በ6ሺ ተብሎ የነበረው ኹለቱንም ቅጽ ከቨሩ የተጎዳ ለማድረግ አስበን ነበር።)

፪. ኹለቱም ቅጽ ምንም ዓይነት እንከን የሌለውን ገጹም ተለቅሞ ተስተካክሎ የተቀመጠውን ንጹሑን መልክዐ ጉባኤ በ8ሺህ ብር ብቻ!!!

መልክዐ ጉባኤው ከሌሎች ገድላት ጋር አንድላይ በፓኬጅ የተዘጋጀው ቀጥሎ ባለው መሠረት ነው፦

መልክዐ ጉባኤ + ገድለ ተስዐቱ ቅዱሳን + መሠረተ እምነት + የ3 ቅዱሳን ገድል (የእነ አቡነ አባለ ክርስቶስ ገድል) + የ2 ቅዱሳን ገድል (የእነ አቡነ አላኒቆስ ገድል) + የ2 ቅዱሳን ገድል (የእነ አቡነ ኢዮስያስ ገድል) እነዚኽ ናቸው። (መጻሕፍቱ በፎቶው ላይ የሚታዩት ናቸው።)

ማለትም በአጠቃላይ፦
መልክዐ ጉባኤው + መሠረተ እምነት + 16 የተለዩ የቅዱሳን ገድላት አጠቃላይ ዋጋቸው (8,000+600+600+500
+2,500+1,500 = 13,700) ሲኾን ከአጠቃላይ ፓኬጁ ተጨማሪ ከፍተኛ ቅናሽ በማድረግ (ከ13,700-2,700)= 11,000

ስለዚኽ በአጭሩ ንጹሑን መልክዐ ጉባኤ + መሠረተ እምነት + 16 የተለዩ የቅዱሳን ገድላትን እነዚኽን ኹሉንም በ 11,000 (ዐሥራ አንድ ሺህ) ብር ብቻ እንድትወስዱ ተፈቅዶላችኋል።

ይኽን ያህል እጅግ ታላቅ ቅናሽ ማድረግ ለምን አስፈላገ?
1ኛ. በኢኮኖሚ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ምእመናንን ታሳቢ በማድረግ፤

2ኛ. መጪውን የፍልሰታን ወቅት ምክንያት በማድረግ በርካታ ምእመናን መልክዐ ጉባኤውን ለሱባኤ ፈልገውት በተደጋጋሚ በቅናሽ እንድንሸጥላቸው ጠይቀውን ስለነበር ጥያቄያቸውን ለመመለስ፤

3ኛ. አሁን ያለንበትን ቢሮ በቅርቡ ስለምንቀይር store ውስጥ ተከማችተው የነበሩ ገድላትን በማጣሪያ ሽያጭ ወደ ምእመናን ለማዳረስ፤

4ኛ. በመጠን መልክዐ ጉባኤውን የሚያህሉ
ሌሎች አዳዲስ ሥራዎች በዚኽ ዓመት መጨረሻ ታትመው ስለሚወጡ በእነርሱ ላይ ለማተኮር የበፊቶቹን ቦታ ቦታ ማስያዝ የግድ ስለኾነ፤
5ኛ.
6ኛ.
✝️ ዐውደ ርእዩ ላይ የምንሳተፈው ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫና አባ በጸሎተ ሚካኤል አንድነት ገዳም መጻሕፍት መሸጫ ሱቅ ጋር በጋራ በመተባበር ስለኾነ ገዳሙም የራሱን የኅትመት ውጤቶች የኾኑ ድንቅ ድንቅ የአባ ጊዮርጊስ ድርሰቶችንና ሌሎችንም ቅዱሳት መጻሕፍትን በዐውደ ርእዩ ላይ ይዞላችሁ ቀርቧል።

✝️ በተራ ቁጥር ፩ና ፪ ላይ ከተጠቀሱት ከፓኬጁ በተጨማሪ መጻሕፍቱን በተናጠል መግዛት ይቻላል። ይኸውም በገድላቱ ላይ በኹሉም የመቶ ብር ቅናሽ የተደረገ ሲኾን መሠረተ እምነት የተደጎሰውን በ500 ብር ቅናሽ እና የ800 ቅዱሳንን ታሪክ የያዘውን የተደጎሰውን ትልቅ መጽሐፍ በ1000 ብር ቅናሽ ማግኘት ትችላላችሁ። ነገር ግን እነዚኽ የተደጎሱት ኹለቱ የቀሩት ትንሽ ቅጂዎች ብቻ ስለኾኑ ቀድመው የመጡ እንዲወስዷቸው ይደረጋል።

✝️ በዚኽ በዐውደ ርእዩ ላይ በተዘጋጀው የፓኬጅ ቅናሽ መሠረት ገዝታችሁ መጻሕፍቱን እኔ ጋር ማስቀመጥ በፍጹም የተከለከለ ነው። ከላይ እንደተገለጸው አንዱ ምክንያት የቢሮ ለውጥ ለማድረግና ለማስተካከል ነው።

✝️ በውጭ ሀገር ያላችሁ ምእመናን እዚኽ ሀገር ቤት ለሚገኙ ቤተሰቦቻችሁ ለወዳጅ ዘመዶቻችሁ ፓኬጁን ገዝታችሁ ብትሰጧቸው ነፍሳቸውን የዕድሜ ልክ ምግብ መገባችሁ ማለት ነው። (ክፍያውን እናንተ ለእኛ ከፍላችሁ እነርሱ መጻሕፍቱን መጥተው መረከብ ይችላሉ።) ሌላው ፓኬጁን በመግዛት ለጉባኤ ቤቶችም ስማችሁ መጻሕፍቱ ላይ ተጽፎ በስጦታ መስጠት ትችላላችሁ።

✝️ መረጃውን ለምታውቋቸው ወዳጅ ዘመዶቻችሁ አድርሱላቸው። ይኽ ፓኬጅና ታላቅ ቅናሽ ተግባር ላይ የሚውለው በእነዚኽ 4 ቀናት ውስጥ ብቻ ነው።

✝️ ዐውደ ርእዩ ላይ የምንገኝበት ቦታ (አቅጣጫ)፦ አዳራሹ ውስጥ በስተደቡብ በኩል ባለው በር አጠገብ የመጨረሻው ረድፍ ከቀኝ ወደ ግራ አራተኛው ጊዜያዊ ሱቅ። ወይም የዛሬ ዓመት የነበርበት አካባቢ ነው። (በትልቁ የሚታይ የአባ ጊዮርጊስ ገዳም ባነር እና የመልክዐ ጉባኤው ከቨር በባነር ተሠርቶ በሩ ላይ ስለተለጠፈ ከሩቅ ይታያል።)

ለተጨማሪ መረጃ፦
0912063211/0925119240

ሰማዕቱ ቅዱስ ኤስድሮስ ስለ ክርስቶስ ሲል የተቀበላቸው መከራዎች እጅግ ጽኑዕ ናቸው።  እንደ አምላኩ ቸንክረው ሰቀለውታል። በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከሥር እሳት አንድደውበታል። ታላቅ ድ...
27/05/2026

ሰማዕቱ ቅዱስ ኤስድሮስ ስለ ክርስቶስ ሲል የተቀበላቸው መከራዎች እጅግ ጽኑዕ ናቸው። እንደ አምላኩ ቸንክረው ሰቀለውታል። በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከሥር እሳት አንድደውበታል። ታላቅ ድንጋይ በአንገቱ ላይ አስረው ወደ ባሕር ጥለውታል። ለተራቡ አንበሶች በሰጡትም እነርሱ ግን ምንም ሳይነኩት ቀሩ። በድጋሚ ሰቀሉት፤ ነገር ግን ጌታችን ከሞት አስነሥቶ ድጋሚ ወደ ሰማዕታት ዐደባባይ ሔዶ እልፍ ነፍሳትን ከዲያብሎስ ማርኮ ለክርስቶስ መንግሥት ያበቃቸው ዘንድ አዘዘው።
ክፉዎችም ጣዖት አምላኪዎችም በሥቃይ ብዛት አልሞት ቢላቸው በመጨረሻ አንገቱን በሰይፍ አስቈርጠውታል።

ጌታችን 5 ጊዜ ከሞት እያስነሣው በተኣምራት እልፍ ነፍሳትን እንዲያሳምን አድርጎታል። ከእርሱም ጋር ማኅበርተኞቹ የሆኑ ከ800,000 (ከስምንት መቶ ሺህ) በላይ የሚኾኑ ሰዎች በቅዱስ ኤስድሮስ አምላክ አምነው እነርሱም በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ሰማዕት ቅዱስ ኤስድሮስ ይኽን ኹሉ አገልግሎት የፈጸመው ገና የ12 ዓመት ሕፃን ሳለ ነው። ግንቦት 19 በዓለ ዕረፍቱ ነው። ረድኤት በረኸቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን።

ሰላም ለዕርገትከ በዘባነ መብረቅ ወነጐድጓድ፤ ከመ ትፈኑ መንፈሰከ በአምሳለ ነፋስ ወነድ፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ዘመንግሥትከ ዋሕድ፤ ይቤሉከ ለለዕለቱ ሰማያውያን ነገድ፤ መንግሥቱ ዘለዓለም ...
21/05/2026

ሰላም ለዕርገትከ በዘባነ መብረቅ ወነጐድጓድ፤ ከመ ትፈኑ መንፈሰከ በአምሳለ ነፋስ ወነድ፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ዘመንግሥትከ ዋሕድ፤ ይቤሉከ ለለዕለቱ ሰማያውያን ነገድ፤ መንግሥቱ ዘለዓለም ወምኵናኑኒ ለትውልደ ትውልድ፡፡

(መድኀኔ ዓለም ሆይ! በዐውሎ ነፋስና በእሳት ነበልባል አምሳል መንፈስ ቅዱስን ትልክልን ዘንድ በነጐድጓድና በመባርቅት የሠረገላ ጀርባ ለተከናወነ ዕርገትህ ሰላም እላለሁ፤ ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ! በአንዲት መንግሥትህ ‹መንግሥቱ ለዘለዓለም አገዛዙም ለትውልደ ትውልድ ነው› እያሉ ሰማያውያን መላእክት በየዕለቱና በየሰዓቱ ያመሰግኑሃል፡፡)

ሰላም ለዕርገትከ ዘፈጸመ ቃሎ፤ ወለምጽአትከ ከዋላ እንተ ያስተጋብእ ኵሎ፤ እምኀበ አቡከ ክርስቶስ በመንበረ ስብሐት ዘሀሎ፤ አውረድከ መንፈሰ ቅዱሰ በአምሳለ ነፋስ ወዐውሎ፤ ሦከ ኀጢአትየ ያውዒ ወያርኢ ኀይሎ፡፡

(መድኀኔ ዓለም ሆይ! የቃል ኪዳን ሥነ ሥርዐት ለፈጸመ ዕርገትህና ኹሉን ለማዘጋጀት ለኋለኛው ዘመን አመጣጥህ ሰላም እላለሁ፤ ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ! ቅድመ ዓለም በጌትነቱ ክብር ከአባትህ ዘንድ የነበረ ወደዚኽ ዓለም በዓውሎ ነፋስ አምሳል የላከው እርሱ መንፈስ ቅዱስ የኀጢአቴን እሾህ በማቃጠል አቤቱ እርሱ ኀይሉን ይግለጽ፡፡)

(ስለ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዕርገት በተለያዩ መልካ መልኮች ላይ የተጠቀሱ ምስጋናዎችን ሙሉውን በ PDF ከቴሌግራም ቻናል ላይ ይመልከቱ።)

https://t.me/kegedilatandebet27217

በድጋሚ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!!!

Address

Addis Ababa

Telephone

+251912063211

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ከገድላት አንደበት-ke gedilat andebet posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ከገድላት አንደበት-ke gedilat andebet:

Shortcuts

Share