ZimareTube

ZimareTube በየዕለቱ የተመረጡ የንስሐና የዓውደ አመት መዝሙሮች ፣ ዕለቱንና ወቅቱን በተመለከተ ስብከተ ወንጌልና
ትምህርተ ኃይማኖትን፣ ያባቶቻችን ገድልና መንፈሳዊ
(556)

Ethiopian Orthodox Tewahido preaching video, Amharic Orthodox Mezmur,
Amharic Preaching, Amharic Sibket, Spiritual Movies and Testimony

ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ከታላቁ የአይሁድ መምህር ገማልያል ከተማሩና ሰፊ እውቀት ካላቸው አርድዕት አንዱ ነው፡፡በመጀመሪያ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር የነበረ ሲሆን ጌ...
25/04/2026

ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ከታላቁ የአይሁድ መምህር ገማልያል ከተማሩና ሰፊ እውቀት ካላቸው አርድዕት አንዱ ነው፡፡

በመጀመሪያ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር የነበረ ሲሆን ጌታችን ሲመጣ እርሱን ተከትሏል፡፡ ከጌታ ዕርገት በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ሲቀበሉም ጸጋው በዝቶ ከታደሉት አንዱ ነበር፡፡ 8 ሺውን የክርስቲያን ማኅበር እንዲመሩ ሰባት ዲያቆናት ሲሾሙም ቅዱስ እስጢፋኖስ ሊቀ ዲያቆናት ሆኗል፡፡ ወንጌልን እየሰበከ ሲጋደል አይሁድ ትምህርቱን ቢሳናቸው ክርስትናን ለማጥፋት እርሱን መግደል እንዳለባቸው ስላመኑ በድንጋይ ወግረው ሲገድሉት ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ ወልድን በአብ ቀኝ ይመለከተው ነበር። ስለ ወጋሪዎቹ ምሕረትን ሲለምን ሰማያዊ የሰማዕትነት አክሊል ተቀዳጀ።

ቅዱስ እስጢፋኖስ ከአረፈ ከ300 ዓመት በኋላ በኢየሩሳሌም የሚኖር ሉኪያኖስ የተባለ ደግ ሰው በተደጋጋሚ በራዕዪ እየተገለጸለት "ሥጋዬን አውጣ" ሲለው ለጳጳሱ ነገራቸው። ጳጳሱም ካህናትና ምዕመናንን ሰብስበው ወደ አፀደ ገማልያል ማለት ወደ መምህሩ ሄደ። ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ። መላዕክት ሲያጥኑም በጎ መዓዛ ሸተተ። ዝማሬ መላዕክትም ተሰማ። ሕዝቡና ጳጳሱም በቅዱስ እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው በታላቅ ዝማሬና በሐሴት ዐፅሙን ከዚያ አውጥተው በጽርሐ ጽዮን በተቀደሰችው ቤት አኖሩት። እለ እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰውም ቤተክርስቲያን አነጸለት ወደዚያ አገቡት።

ከአምስት ዓመታት በኋላም እስክንድሮስ ሲያርፍ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጎን አኖሩት። የእለ እስክንድሮስ ባለቤት ግን ወደ ሀገሩዋ ቁስጥንጥኒያ ስትመለስ የባሏ ሥጋ መስሉዋት የቅዱስ እስጢፋኖስን ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው። መንገድ ላይም ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው። እጅግም ደስ አላት አምላክ ለዚህ አድሉዋታልና። እርሷም ወስዳ ለታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጥንጢኖስ አስረከበችው። በከተማው ታላቅ ሐሴት ተደረገ። ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች። በዚያም ላይ ትልቅ ቤተክርስቲያን ታንጾለታል። ራሳቸውን ለእግዚአብሔር አሳልፈው የሰጡ ቅዱሳንና ሰማዕታትን የሚዘክሩ በአማላጅነታቸው የሚማጸኑ ገዳማውያን በረከታቸው የበዛ ነው፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት እና ምልጃዋ አይለየን🙏የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ...
24/04/2026

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት እና ምልጃዋ አይለየን🙏

የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል

ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡

ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡

ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል 🙏ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ ...
24/04/2026

የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል 🙏

ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡

ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡

ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ማልሁልሽ ቃል ኪዳንም ገባሁልሽ አላት🙏የእግዚአብሔር የምሕረት ቃል ኪዳን ለቅዱሳኑ ከሃይማኖታቸው ጽናት ከፍጹምነታቸውና ከሥራቸው ትሩፋት የተነሳ በቅድስና ክብር አክብሮ ለገድላቸው እንዲሁም በ...
23/04/2026

ማልሁልሽ ቃል ኪዳንም ገባሁልሽ አላት🙏

የእግዚአብሔር የምሕረት ቃል ኪዳን ለቅዱሳኑ ከሃይማኖታቸው ጽናት ከፍጹምነታቸውና ከሥራቸው ትሩፋት የተነሳ በቅድስና ክብር አክብሮ ለገድላቸው እንዲሁም በተጋድሎ ላሳለፉበት ቦታ ለረገጡት አፈር ሁሉ በረከታቸው ተርፎ ዛሬ እኛ ምእመናን በየመካናቱ እምነቱን በመተሻሸት በመጠጣት ከቅዱሳኑ በረከት እንሳተፋለንል፡፡ በዘጸአት 20÷2-6 እግዚአብሔር አምላክ ለሚወዱትም ትእዛዙን ለሚጠብቁ እስከ ሺህ ትውልድ ድረስ ምሕረትን እንደሚያደርግ ተጽፏል፡፡ በዘዳግም 7÷12 ደግሞ “እንዲህም ይሆናል፤ ይህችን ፍርድ ሰምተህ ብትጠብቃት ብታደርጋትም፥ አምላክህ እግዚአብሔር ለአባቶችህ የማለውን ቃል ኪዳንና ምሕረት ለአንተ ይጠብቅልሃል” ይላል፡፡ ኪዳነ ምህረት፣ የምህረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡

ይህም ፍጹም ከከበሩ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ የማይጠፋ የዘላለም ኪዳን የሰጠበት ዕለት መታሰቢያ ነው፡፡ ታላቁ የነገረ ማርያም መጽሐፍ እንደሚያስረዳን ጌታችን ካረገ በኋላ እመቤታችን ጌታ ወደ ተቀበረበት ጎልጎታ እየሄደች ትጸልይ ነበር፡፡ በየካቲት 16 ቀንም ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ “ልጄ ወዳጄ ሆይ ከሥጋዬ ሥጋ ከነፍሴ ነፍስ ነሥተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በቻለችህ ማኅፀኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለመሰደዴ መጥተህ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ እለምንሃለሁ” እያለች ጸለየች፡፡ ጌታችንም መጥቶ ምን እንዲያደርግላት እንደምትፈልግ ጠየቀችው፡፡

ቅድስት ድንግል ማርያም በስሟ ለሚማጸኑ መታሰቢያዋን ለሚያደርጉ፣ ለችግረኛ ለሚራሩ፣ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ለሚያንጹ፣ ዕጣን ዘይትና መብአ ለቤተ ክርስቲያን ለሚሰጡ ምሕረትን እንዲያደርግላቸው ጠየቀችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በአባቴ፣ በራሴና በመንፈስ ቅዱስ ማልሁልሽ ቃል ኪዳንም ገባሁልሽ አላት፡፡ ይህን የማያልፍ የምህረት ቃል ኪዳን ስለገባላትም ዕለቱ ኪዳነ ምሕረት የምሕረት የይቅርታ መሐላ፣ ውል፣ ስምምነት፣ ተብሎ በዝማሬ፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ ምዕመናንም ዘወትር በረከትን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ይቀበላሉ፡፡ ገዳማውያንም ይህን ቃል ኪዳኗን አስበው ዘወትር ምህረትን አማልጂ ይሏታልና ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ቅዱስ ቂርቆስ የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ 🙏የሚያገኛቸውን መከራ ሳይፈሩ ስለ ክርስቶስ አምላክነት ከመስከሩ የክብር አክሊል ከተቀዳጁ ሰማዕታት የሦስት ዓመቱ ሕጻን ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆ...
23/04/2026

ቅዱስ ቂርቆስ የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ 🙏

የሚያገኛቸውን መከራ ሳይፈሩ ስለ ክርስቶስ አምላክነት ከመስከሩ የክብር አክሊል ከተቀዳጁ ሰማዕታት የሦስት ዓመቱ ሕጻን ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ቅድስት ኢየሉጣ የሮም ግዛት በሆነው አንጌቤን በክርስትና ሃይማኖት ጸንታ የምትኖርና ልጇ ቅዱስ ቂርቆስንም በስርዓት ያሳደገችው ደግ ሴት ነበርች፡፡ በዘመኑ የነበረውን አረማዊ አስተዳዳሪ እለእስክንድሮስን በመፍራት ከልጇ ጋር ከሮም ወደ ጠርሴስ ብትሰደድም እለእስክንድሮስ ተከትሎ ባለችበት ቦታም አገኛት።

ወታደሮችም እርሷንና ልጇን ይዘው ወደ መኮንኑ አቀረቧቸው። መኮንኑም "ስምሽን ንገሪኝ" ቢላት "ስሜ ክርስቲያን ነው" አለችው። መኮንኑ በብስጭት ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስንም "ስምህን ንገረኝ" ሲለው "ስሜ ክርስቲያን ነው፤ እናቴ የሰየመችኝን ከፈለክ ግን ቂርቆስ ነው" ሲል መለሰለት። ቅድስት ኢየሉጣንም "ለጣዖት ልትሰግጂ ይገባል" ሲላት “የምንሰግድለት አንድ ክርስቶስ ብቻ ነው” አለችው፡፡ ቅዱስ ቂርቆስም እየደጋገመም "እኔ ክርስቲያን ነኝ" ብሎ በመጮሁ ምላሱን ቢያስቆረጠው እግዚአብሔር ፈውሶታል፡፡

መኮንኑ መከራ አጸናባቸው፤ በግርፋት የጀመረ ስቃይ ሊሰሙት ወደ ሚጨንቅ መከራ ቀጠለ። በፈላ ውሃ ውስጥ ሲከታቸውም ቅዱስ ገብርኤል አዳናቸው፡፡ እናትና ልጅ በክርስቶስ ታምነዋልና ጸኑ።

ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላም ጥር 15 ቅዱስ ቂርቆስን ጥር 16 ደግሞ ቅድስት ኢየሉጣን ሰይፏቸው ሰማዕትነት ተቀብለዋል፡፡ የሕጻኑን ሥጋ በሠረገላ ኤልያስ አኑሮታል፣ ብዙ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል።

ዛሬም በየገዳማቱ ዓለምን ንቀው የሚኖሩ መነኮሳትና ገዳማውያን በጸሎታቸው ኃይል ያደርጋሉ፡፡ ከዓለም ክብር የክርስቶስን ክብር፣ ከሥጋ ደስታ መንግስተ ሰማያትን መርጠዋልና፡፡ ገዳማቸውን እናግዝ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የጻድቁ አቡነ  አረጋዊ ረድኤት እና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን 🙏ጻድቁ ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ቢሆንም ሃገረ ሙላዳቸው የጥንቱ የሮም ግዛት የሆነችው ታናሽ እስያ ናት፡፡ አቡነ አረጋዊ...
22/04/2026

የጻድቁ አቡነ አረጋዊ ረድኤት እና ምልጃ ከሁላችን ጋር ይሁን 🙏

ጻድቁ ገድላቸውን የፈጸሙት በኢትዮዽያ ቢሆንም ሃገረ ሙላዳቸው የጥንቱ የሮም ግዛት የሆነችው ታናሽ እስያ ናት፡፡

አቡነ አረጋዊ ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ ናቸው፡፡ ዘጠኙ ቅዱሳን ዘራቸው ከቤተ መንግስት ሲሆን ተወልደው ያደጉት በአንድ የሮም ግዛት ሥር በተለያየ ቦታ ነው፡፡ አንድ ያደረጋቸው መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትን በሚገባ ያጠኑት እነዚህ አበው ሰማያዊውን ክብር መርጠው ክርስቲያኖች በሚሳደዱበት በ5ኛው ክፍለ ዘመን በቅድሚያ አባ ዸንጠሌዎንና አቡነ አረጋዊ ከዚያም ሌሎቹ ከሮም ወደ ግብጽ በርሃዎች፣ በ470ዎቹ ዓ.ም አልዓሜዳ በኢትዮዽያ ነግሦ ሳለ በአረጋዊ መሪነት ወደ ኢትዮጵያ በምናኔ መጥተዋል፡፡

ንጉሡም በመልካም ተቀብሎ በአክሱም ቤተ ቀጢን ማረፊያ ቦታ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም የግዕዝ ቋንቋ ተምረው እዛው አክሱም አካባቢ በአቡነ ሰላማ፣ በአብርሃ ወአጽብሐና በአቡነ ሙሴ ቀዳማዊ የተቀጣጠለውንና በተወሰነ መንገድ ተቀዛቅዞ የነበረውን ክርስትና እንደገና አቀጣጠሉት፤ ለዓመታትም ወንጌልን ሰበኩ በርካታ መጻሕፍትንም ተረጎሙ፡፡ በኋላም የየራሳቸው የምናኔ ቦታ በመምረጥ ወንጌልን እየሰበኩና ስለሀገራችን እየጸለዩ ኖረዋል፡፡

አባታችን አቡነ አረጋዊ በደብረ ዳሞ ታላቅ ገድል ፈጽመዋል፡፡ ማኅሌታዊው ቅዱስ ያሬድና አፄ ገብረ መስቀልም ወዳጆቻቸው ነበሩ፡፡ ጻድቁ ተጋድሏቸውን ፈጽመው በተወለዱ በ99 ዓመታቸው ተሰውረው ብሔረ ሕያዋን ገብተዋል፡፡

ጌታም የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ጥር 14ም ጻድቁ የተወለዱበት ቀን ነው፡፡

መናንያንና ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ስለ ክርስቶስ ፍቅር ብዙ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ የወንጌል ብርሃን እንዲበራ፣ ትልቅ ሥራ ሰርተዋል፡፡ ጸሎታቸው አሁንም ተአምር ያደርጋል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የልባችንን መልካም መሻት ይሙላልን፤ ረድኤቱ እና ምልጃውም አይለየን🙏ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣከእግዚአብሔር ዙፋን ትዕዛዝ ሲወጣ ኪሩቤልና ሱራ...
21/04/2026

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የልባችንን መልካም መሻት ይሙላልን፤ ረድኤቱ እና ምልጃውም አይለየን🙏

ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ

ከእግዚአብሔር ዙፋን ትዕዛዝ ሲወጣ ኪሩቤልና ሱራፌል ለሚካኤል ያስተላልፋሉ፡፡ ሚካኤል ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ መላዕክትን ያዛቸዋል፤ ኪሩቤልና ሱራፌል መላዕክቱም ሁሉ አቤቱ የእጅህን ስራ አታጥፋ እያሉ ቀንና ማታ ይለምናሉ። ድርሳነ ሩፋኤል ላይ ተጽፎ እደምናገኘው 7 ሊቃነ መላዕክት ሲኖሩ አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ የስሙ ትርጓሜ “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ነው። የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከዲያቢሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ እግዚአብሔር ይገስፅህ አለው እንጂ የስድብን ቃል አልተናገረውም ሲባል ሰምተናል፡፡ ሊቀ ነብያት ሙሴ እጅግ ታዛዥና የዋህ ስለነበርና ከነዓንን ለማየት ወደ ናባው ተራራ ሲወጣ 2 መላዕክት በአረጋውያን ተመስለው መቃብር ሲቆፍሩ ቢያይ ላግዛቹ ብሎ መቆፈሪያውን ተቀበላቸው፡፡ ቆፍረው ሲጨርሱም “ሰውየው በአንተ ልክ ነውና ገብተህ ለካልን” አሉት፡፡

ጉድጓዱ ውስጥ ገብቶ እንደተኛ እንደ እንቅልፍ አሸልቦት በዚያው ዐረፈ፤ መላዕክቱም ቀበሩት። እስራኤላዊያን ሙሴን እጅግ ስለሚወዱት የሙሴን መቃብር እንደ ጣዖት እንዳያመልኩት እግዚአብሔር የሙሴን መቃብር ሰወረው፤ ጠላት ዲያቢሎስ ግን ሊያሳያቸው በመነሳቱ ቅዱስ ሚካኤል ተቃወመው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል ዲያቢሎስን እግዚአብሔር ይገስጽህ ብሎ ከእርሱም ሰወረበት። በሐዋርያው ይሁዳ መልዕክት ቁጥር 8 የሚገኘው ቃል የቅዱስ ሚካኤልን ትዕግስት ያሳያል፡፡ ዳግመኛም አይሁድ ጌታን ሲሰቅሉት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በቁጣ ሰይፉን አወጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል ግን በአይሁድ ስራ አዝኖ፣ የፈጣሪን የትዕግስቱንና የፍቅሩን ብዛት እያደነቀ በአርምሞ አያቸው ይላል ድርሳኑ። መላዕክቱ በክንፋቸው የእግዚአብሔር ስም ተጽፎበታል፡፡

የመላዕክቱን ስም የመጨረሻውን ፊደል ስናይ ኤል ብሎ ይጨርሳል፡፡ ሚካ-ኤል ገብር-ኤል ኡራ-ኤል፤ ይህም “ስሜ በሱ ላይ ነውና” እንደሚል የእግዚአብሔር የምህረት ስም በክንፎቻቸው ስለተጻፈ መላዕክቱ ይጠብቁናል። “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለአንተ ያዛቸዋል፤ እግርህም በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቻቸው ያነሱሃል” ተብሎም በመዝሙር 90÷11 ተጽፋልና አህዛብን ጭምር ያለጊዜያቸው እንዳይሞቱ መላዕክት ይጠብቋቸዋል!!! በትንቢተ ዳንኤል 10÷13 እና 10÷21 ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲናገር ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፣ በተዘጋ ጉድጓድ ሲያጽናናው ደግሞ “ከሚካኤል በቀር የሚያጽናናኝ የለም” አለ፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 33÷7 “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል” ይለናል፡፡

በዓለም ፍፃሜም ስለህዝቡ የሚቆመው ሚካኤል ይነሳል። በማለት በዳንኤል 12÷1 ተጽፎልናል፡፡ በራዕይ 8÷3 “የቅዱሳኑ ፀሎት ከዕጣኑ ጢስ ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ” ተብሎ እንደተጻፈውም መላዕክት የቅዱሳኑን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርጋሉ፡፡

በዚህ ጸሎት ውስጥ ገዳማውያን እናቶችና አባቶች ከራሳቸው አልፈው ስለቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ስለሀገራችን ሰላምና መጽናት የሚያደርጉት ጸሎት እጅግ ኃይልን ያደርጋል፡፡ ምክንያቱም ገዳማውያንም የእግዚአብሔርን ቸርነት የመላእክቱን አማላጅነት አምነው ዘወትር በጸሎት ይተጋሉና። ገዳማቸውን እየረዳን በዓታቸውን እያጠናን የበረከታቸው ተካፋይ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

የሠራዊት ጌታ የልዑል እግዚአብሔር አገልጋይ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል 🙏የስሙ ትርጓሜም “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ሲሆን የ7 ሊቃነ መላዕክት አለቃቸው ነው ቅዱ ሚካኤል። ል...
20/04/2026

የሠራዊት ጌታ የልዑል እግዚአብሔር አገልጋይ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤል 🙏

የስሙ ትርጓሜም “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ሲሆን የ7 ሊቃነ መላዕክት አለቃቸው ነው ቅዱ ሚካኤል። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 33÷7 “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል” ይለናል፡፡ ከእግዚአብሔር ዙፋን ስር ትዕዛዝ በወጣ ግዜ ኪሩቤል ተቀብለው ለሱራፌል ያስተላልፋሉ፤ ሱራፌልም ለሚካኤልና ለገብርኤል ለሩፋኤልም ያደርሳሉ፡፡ ሚካኤል ለፍጥረቱ በጎም ይሁን ክፉ ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ መላዕክትን ያዛቸዋል፤ መላዕክቱም ሁሉ አቤቱ የእጅህን ስራ አታጥፋ እያሉ ቀንና ከማታ ይለምናሉ። በዓለም ፍፃሜም ስለህዝቡ የሚቆመው ሚካኤል ይነሳል። በማለት በምዕራፍ 12÷1 ጽፎልናል፡፡ በራዕይ 8÷3 “የቅዱሳኑ ፀሎት ከዕጣኑ ጢስ ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ” ተብሎ እንደተጻፈውም መላዕክት የቅዱሳኑን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርጋሉ፡፡

አይሁድ ጌታን ሲሰቅሉት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአይሁድ ስራ አዝኖ በቁጣ ሰይፉን አወጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል ግን በእግዚአብሔር ትዕግስት ተገርሞ፣ ፈጣሪን ፍጡራን ሰቀሉት እያለ በአርምሞና በትዕግስት አያቸው ይላል ድርሳኑ። ቅዱስ ሚካኤል ሰኔ 12 ቀን ዲያቢሎስን አሸንፎ በምትኩ ሊቀ መላዕክት ሆኖ የተሾመበትና አፎምያንም የረዳበት ቀን ስለሆነ በታላቅ ሥርዓት ይከበራል። ህዳር 12 ሕዝበ እስራኤልን በክንፎቹ ጥላ ከበረሃው ፀሐይ ከልሎ ከግብጽ ምድር እየመራና እየጠበቀ ከንዓን ያገባበት ዕለት ነው። መላዕክቱ በክንፋቸው የእግዚአብሔር ስም ስለተፃፈበት ህዝቡን ይጠብቃሉ፤ የመላዕክቱን ስም የመጨረሻውን ፊደል ስናይ ኤል ብሎ ይጨርሳል፡፡ ሚካ-ኤል ገብር-ኤል ኡራ-ኤል፡፡ ይህም “ስሜ በሱ ላይ ነውና” እንደሚል የእግዚአብሔር የምህረት ስም ስለሆነና በክንፎቻቸው ስለተፃፉ መላዕክቱ ይጠብቁናል።

“በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለአንተ ያዛቸዋል፤ እግርህም በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቻቸው ያነሱሃል” ተብሎም በመዝሙር 90÷11 ተጽፋልና አህዛብን ጭምር ያለጊዜያቸው እንዳይሞቱ መላዕክት ይጠብቋቸዋል፡፡ በትንቢተ ዳንኤል 10÷13 እና 10÷21 ደግሞ የስሙ ትርጉም እግዚአብሔር ዳኛዬ ነው የተባለው ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲናገር ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፣ በተዘጋ ጉድጓድ ሲያጽናናው ደግሞ “ከሚካኤል በቀር የሚያጽናናኝ የለም” አለ፡፡ ገዳማውያን የሚያደርጉት ጸሎትና የሚያቀርቡት መስዋዕት በእርሱ ምልጃ ያርጋልና ገዳማቸውን እየረዳን በዓታቸውን እያጠናን የበረከታቸው ተካፋይ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ሊቀ መልእክት ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏የስሙ ትርጓሜም “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ሲሆን የ7 ሊቃነ መላዕክት አለቃቸው ነው ቅዱ ሚካኤል። ልበ አምላክ...
20/04/2026

ሊቀ መልእክት ቅዱስ ሚካኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ🙏

የስሙ ትርጓሜም “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው” ማለት ሲሆን የ7 ሊቃነ መላዕክት አለቃቸው ነው ቅዱ ሚካኤል። ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 33÷7 “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል” ይለናል፡፡ ከእግዚአብሔር ዙፋን ስር ትዕዛዝ በወጣ ግዜ ኪሩቤል ተቀብለው ለሱራፌል ያስተላልፋሉ፤ ሱራፌልም ለሚካኤልና ለገብርኤል ለሩፋኤልም ያደርሳሉ፡፡ ሚካኤል ለፍጥረቱ በጎም ይሁን ክፉ ትዕዛዙን ይፈጽሙ ዘንድ መላዕክትን ያዛቸዋል፤ መላዕክቱም ሁሉ አቤቱ የእጅህን ስራ አታጥፋ እያሉ ቀንና ከማታ ይለምናሉ። በዓለም ፍፃሜም ስለህዝቡ የሚቆመው ሚካኤል ይነሳል። በማለት በምዕራፍ 12÷1 ጽፎልናል፡፡ በራዕይ 8÷3 “የቅዱሳኑ ፀሎት ከዕጣኑ ጢስ ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ” ተብሎ እንደተጻፈውም መላዕክት የቅዱሳኑን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርጋሉ፡፡

አይሁድ ጌታን ሲሰቅሉት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በአይሁድ ስራ አዝኖ በቁጣ ሰይፉን አወጣ፤ ቅዱስ ሚካኤል ግን በእግዚአብሔር ትዕግስት ተገርሞ፣ ፈጣሪን ፍጡራን ሰቀሉት እያለ በአርምሞና በትዕግስት አያቸው ይላል ድርሳኑ። ቅዱስ ሚካኤል ሰኔ 12 ቀን ዲያቢሎስን አሸንፎ በምትኩ ሊቀ መላዕክት ሆኖ የተሾመበትና አፎምያንም የረዳበት ቀን ስለሆነ በታላቅ ሥርዓት ይከበራል። ህዳር 12 ሕዝበ እስራኤልን በክንፎቹ ጥላ ከበረሃው ፀሐይ ከልሎ ከግብጽ ምድር እየመራና እየጠበቀ ከንዓን ያገባበት ዕለት ነው። መላዕክቱ በክንፋቸው የእግዚአብሔር ስም ስለተፃፈበት ህዝቡን ይጠብቃሉ፤ የመላዕክቱን ስም የመጨረሻውን ፊደል ስናይ ኤል ብሎ ይጨርሳል፡፡ ሚካ-ኤል ገብር-ኤል ኡራ-ኤል፡፡ ይህም “ስሜ በሱ ላይ ነውና” እንደሚል የእግዚአብሔር የምህረት ስም ስለሆነና በክንፎቻቸው ስለተፃፉ መላዕክቱ ይጠብቁናል።

“በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለአንተ ያዛቸዋል፤ እግርህም በድንጋይ እንዳይሰናከል በእጆቻቸው ያነሱሃል” ተብሎም በመዝሙር 90÷11 ተጽፋልና አህዛብን ጭምር ያለጊዜያቸው እንዳይሞቱ መላዕክት ይጠብቋቸዋል፡፡ በትንቢተ ዳንኤል 10÷13 እና 10÷21 ደግሞ የስሙ ትርጉም እግዚአብሔር ዳኛዬ ነው የተባለው ነብዩ ቅዱስ ዳንኤልም ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ ሲናገር ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፣ በተዘጋ ጉድጓድ ሲያጽናናው ደግሞ “ከሚካኤል በቀር የሚያጽናናኝ የለም” አለ፡፡ ገዳማውያን የሚያደርጉት ጸሎትና የሚያቀርቡት መስዋዕት በእርሱ ምልጃ ያርጋልና ገዳማቸውን እየረዳን በዓታቸውን እያጠናን የበረከታቸው ተካፋይ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

እንኳን ለዳግማዊ ትንሳኤ አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏ዳግማይ ትንሣኤ ማለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሑድ ደቀመዛሙርቱ በአንድነት ተሰ...
19/04/2026

እንኳን ለዳግማዊ ትንሳኤ አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏

ዳግማይ ትንሣኤ ማለት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሳ በስምንተኛው ቀን በዕለተ እሑድ ደቀመዛሙርቱ በአንድነት ተሰብስበው ሳሉ ለሁለተኛ ጊዜ ተገልጦ ትንሣኤው ፍጹም አማናዊ እንደሆነ ያሳየበት ዕለት ነው፡፡

በዮሐንስ 20÷24-30 እንደተጻፈው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ትንሣኤ ባለፈ የሚመጣውን እሑድ ሰይማ ታከብረዋለች፡፡ ጌታችን ለሐዋርያቱ ቀድሞ በተዘጋ ቤት ገብቶ ሰላም ለእናንተ ይሁን ብሎ ተገልጦላቸው ነበር፡፡ ዳግመኛም ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ግን ደቀ መዛሙርቱ መጥተው ጌታችንን በመካከላችን ተገልጦ አየነው ብለው ሲነግሩት የችንካሩን ምልክት በእጄ ካልዳሰስኩ አላምንም ብሎ ስለነበር ና ንካኝ ብሎታል፡፡ ቶማስ የተጠራጠረው በማቴዎስ 22÷23-33 እንደተገለጸው ትንሣኤ ሙታን የለም ብለው ከሚያምኑት ፈሪሳዊያን ወገን ስለነበረ ነው፡፡ የጌታችንን ጎን የነካች የቶማስ እጅ በኋላ ላይ ሳትበሰብስ በሕያውነት ለብዙ ዘመናት ኖራለች፡፡

በሀገረ ስብከቱና ሰማዕትነት በተቀበለባት በሕንድ ሀገር ከታቦት ጋር ከመንበሩ ላይ ያኖሯት ነበር፡፡ በዓመት በዓመት በእመቤታችን በዓል በአስተርዕ ሊያጥኑ ሲገቡ የሚሾመውን ወጥታ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች ዓመት አገልግሎ ያርፋል በዓመቱ ሊያጥን ሲገባ ትይዘዋለች እንዲህ እያለች ትኖራለች፡፡ ቶማስን “ና ጎኔን ንካ›” ሲለው በኋላ በዓለም ዞሮ ወንጌልን የሚሰብክ ነውና ሐዋርያ ከሆነ ዘንድ ደግሞ “ሐዋርያት እንዳሉት ጌታችን ተነስቷል” ብሎ ያስተምር ዘንድ አይገባውም ይልቁንም እንደ በ1ኛ ዮሐ1÷1-2 እንደተገለጸው “በጆሮአችን የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውንን የተመለከትነውን እጆቻችን የዳሰሱትን እንነግራችኋለን ሕይወት ለእኛ ተገልጻለችና አየናት” የሚል ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ነውና ቶማስን ና ንካኝ ብሎታል፡፡

አንድም የክርስቲያኖች ሰንበት የምንላት ዕለተ እሑድ ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ የተነሳባት በመሆኗ የእረፍት የመንግስተ ሰማይ አምሳል ብለን እናከብራታለን፡፡ የዕለቲቱን ክብርትነት፣ ዘወትር እሑድም ጌታችን የተነሳባትና ዳግሞ ትንሣኤውን የገለጠባት እንደሆነ እንድናስብ ለአክብሮተ ሰንበት ዳግሞ ተገለጠላቸው፡፡ አንድም በሉቃስ 24÷39 ጌታችን ራሱ የተገለጠበትን ዓላማ ሲነግራቸው “እጄን እግሬን እዩ ዳስሱኝም እኔ እንደሆንኩ ዕወቁ በእኔ እንደምታዩት ለምትሐት አጥንትና ሥጋ የለውምና እንዳላቸው የጌታችን ትንሳኤ ምትሐት ያይደለ አማናዊ በቀደመው ተዋሕዶ ባለመለወጥ እንደተነሳ ለማጠየቅ ተገለጠላቸው፡፡ ሲገለጥም በተዘጋ ቤት መግባቱ መለኮት አለመለየቱንና ወደ ሥጋ መለወጥ እንዳላገኘው ያስረዳል፡፡ ገዳማውያን ትንሣኤውን አምነው በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ዓለምን ንቀው ይገዙለታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯ...
18/04/2026

የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏

የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።

በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡

በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡

ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ቄርሎስ “ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርስዋን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡ለእርስዋ ሲል ታሥሮ መጎተት ...
17/04/2026

የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ቄርሎስ “ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርስዋን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡

ለእርስዋ ሲል ታሥሮ መጎተት የቻለ የበደለውም በደል ሳይኖር፣ ርኩስ ምራቅን ሲተፋበት የታገሠ መድኃኔ ዓለም በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ” በማለት ገለጸው፡፡ በመለኮቱ ሕያው ሲሆን በስጋው ግን ሞትን ቀመሰ፡፡ የአዳምን ሞት በሞቱ ሊሽር መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ ሰጠ፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ሰው ሆኖ እንደሚያድነን በመጀመሪያ ለአዳም ቃል ገባለት፡፡ ከዚያም በነቢያት ትንቢት አስነገረ፡፡ በስጋ በተገለጠ ጊዜም የሰቀሉትና የገደሉት አይሁድ ሳይቀሩ እንዲናገሩ አፋቸውን አስከፈታቸው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስም “ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን… አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን” ይላል፡፡ “ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፣ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች በአንድነት እንዲሰበስባቸው መጥቷል እንጂ።” ተብሎ ተጽፏልና፡፡ በድንቅ ተዋህዶ አምላክ ሰው፣ ሰውም አምላክ ሆኗልና ከኛ በነሳው ስጋም ወደ ሰማይ አረገ፡፡ ስለፍጹም የሰው ልጆች ፍቅር መድኃኔ ዓለም ተላልፎ ተሰጠ፡፡

በፊልጵ 2÷8 “በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፣ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ” ተብሎ እንደተጻፈው፡፡ በማዳኑ ስራ ውስጥ የቅድስት ድንግል ማርያም ድርሻ ታላቅ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በገላ 4÷4 “የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ልጁን ላከ፡፡” ሲል ጽፏል፡፡

ዕለት ዕለት ፍቅሩን የከፈለልንን ዋጋ፣ ይህን መከራውንና ማዳኑን ዕለት ዕለት የሚያስቡ ገዳማውያን ሌሊትና ቀን በስግደትና በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቱን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጸና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ZimareTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ZimareTube:

Share