አቢሲኒያ

አቢሲኒያ ✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ መረጃዎችን እና የታሪክ ፅሁፍች

መልካምነት ለራስ ነው ሰላም እንዴት ናችሁ አፋልጉኝ የሚሉ የኛው ቤተሰቦች እንተባብራቸው ደቡብ ሱዳን ያላችሁ ይሄን ቪዲዮ ላይ ያለውን ወንድማችን ካያቹሁ አሳውቁን ሙሉ መረጃ ቪዲዮ ላይ አለ ...
20/10/2025

መልካምነት ለራስ ነው
ሰላም እንዴት ናችሁ አፋልጉኝ የሚሉ የኛው ቤተሰቦች እንተባብራቸው ደቡብ ሱዳን ያላችሁ ይሄን ቪዲዮ ላይ ያለውን ወንድማችን ካያቹሁ አሳውቁን ሙሉ መረጃ ቪዲዮ ላይ አለ

የአፋልጉኝ ጥሩ #አፋልጉኝ #ደቡብሱዳን #መረጃ @ዘማሪ ብርሃኑ ተረፈ zemari birhanu te Lidiya Tadesse @መቅዲ ✝️ዘ ማኀበር ሥላሴ ✝️✝️ WALLPAPER

እንኳን ለእመቤታችን ጾም 🔔ጾመ🎤ፍልሰታ🔔 በሰላም አደረሳችሁ።የበረከት ጾም ያድርግልን ሕዝበ ክርስቲያን ።              1, ጾመ ፍልሰታን ማን ጾማት ?              2, ጾመ ...
06/08/2025

እንኳን ለእመቤታችን ጾም 🔔ጾመ🎤ፍልሰታ🔔 በሰላም አደረሳችሁ።የበረከት ጾም ያድርግልን ሕዝበ ክርስቲያን ።
1, ጾመ ፍልሰታን ማን ጾማት ?
2, ጾመ ፍልሰታን ለምን እንጾማለን ?
የ2014 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ እሁድ ነሐሴ 1 ይያዛል። ፍልሰታ በ ዋናነት የእመቤታችን ጾም ሲሆን ሐዋርያት የእመቤታችን እረገቷን ትንሳኤዋን ለማየት 2 ሱባኤ ይዘው ጾመውታል።

"ፍልሰታ" ቃሉ የግዕዝ ሲሆን ትርጓሜው ፈለሰ,ተነጠለ, ተለየ ተሰደደ ተዘዋወረ ተካፈለ ማለት ነው። አንድ ላይ ሲነበብ ደግሞ"ፍልሰታ ለ ማርያም" እያልን እንጠራታለን ይህም የእመቤታችንን በድነ ስጋዋ መፍለስ ማለት ነው።

አንድም እመቤታችን ከሚያልፈው ዓለም ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበትን የተነሳችበት ቀን ማለት ነው። ወይንም ደግሞ እመቤታችን ከስጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊ ዓለም የተሸጋገረችበት ቀን ማለት ነው።

ፍልሰታ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መፍለስ (መሄድ)። ያመለክታል ። እመቤታችን ካረፈች በኋላ የስጋዋን መፍለስ አስመልክቶ ሐዋርያት የእመቤታችን ስጋ የት እንደተቀበረ አላወቁም ነበርና እግዚአብሔር አምላክ የእመቤታችንን ስጋ እንዲገልጥላቸው የጾሙት ጾም ነው።

ሐዋርያት ሁለት ሱባኤ ጾመው ጌታችን የእመቤታችንን በድነ ስጋዋን ሰጥቷቸዋል።ትንሳኤዋን እና እርገትዋን በማየት ታላቅ በረከት ያገኙበት ጾም ነው።

ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እንዲጠብቃት ከተደረገ በኋላ ሐዋርያት የእመቤታችን ነገር እንዴት ነው ብለው በጠየቁት ጊዜ ዮሐንስም እመቤታችንማ በገነት በእፀ ሕይወት ስር ናት አላቸው።

በዚህን ጊዜ ሐዋርያት እመቤታችን ከመቃብር መነሳቷን ማረጓን ማየት አለብን እንዴት ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን በሚል መንፈሳዊ ቅናት ተነሳስተው ነሐሴ 1 በእለተ ሰኞ ቀን ሁለት(7) ሱባኤን ያዙ ።በአስራ አራተኛው ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ስጋ አንስቶ ሰጣቸውና በጌቴ ሴማኒ ቀበሯት።

እመቤታችን በ 64 አመቷ ጥር 21 ቀን አርፋ ነሐሴ 14 ቀን ተቀብራለች።ይኁንና ሐዋርያት ቢቀብሯትም ትንሳኤዋንና እርገትዋን አላዩም ነበር። ትንሳኤዋንና እርገቷን ያየው ሲቀብሯት ያላየው ሐዋርያው ቶማስ ነው።

ሐዋርያው ቶማስም እንዲያስተምር ወደ ሕንድ ሀገር ዕጣ ደርሶት ሄዶ ነበርና አስተምሮ በደመና ሲመለስ ነሐሴ 16 ቀን እመቤታችን ስታርግ እያለ በደመና ሕዋ ላይ ተገናኙ ለምልክት ይሆነው ዘንድ ሰበኗን ሰጠችው።

ጾመ ፍልሰታ ከ 7ቱ የአዋጅ አፅዋማት አንዷ ስትሆን የአመቱ የመጨረሻ የአዋጅ ጾም ናት። ስለኾነም ምዕመናን በየአመቱ ጾመ ፍልሰታን ከልጅ እስከ አዋቂ ሳይል ንቅል ብለው በጾም በፀሎት በመቁረብ በጋራ በፍቅር በደስታ የእመቤታችንን በረከት ያፍሳሉ ይቋደሳሉ።

በእውነቱ በዚህ ፆም እመቤታችን የሀገራችን የሐይማኖታችን የቤተክርስቲያናችን የህዝባችንን ሰላም ወደ ቀደመው ሰላም
ትመልሰልን።

ጾሙን ጾመን እቀድሰን ቆርበን ለትንሳኤዋ ብርሀን በሰላም ያድርሰን።

✞✞✞ የበረከት ጾም ይሁንልን ✞✞✞

ጀበና እንደዚህ እንደሚፈነዳ ማን ያውቃል
02/07/2025

ጀበና እንደዚህ እንደሚፈነዳ ማን ያውቃል

“ቅዱስ ሚካኤል «ቅዱስ» ማለት ልዩ፥ ክቡር ማለት ነው፤ ሚካኤል ማለት ደግሞ «መኑ ከመ አምላክ፥ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው?» ማለት ነው።  #ሚካኤል የሚለው ስም ቃሉ  #የዕብራይስጥ ነ...
18/06/2025

“ቅዱስ ሚካኤል «ቅዱስ» ማለት ልዩ፥ ክቡር ማለት ነው፤ ሚካኤል ማለት ደግሞ «መኑ ከመ አምላክ፥ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው?» ማለት ነው።
#ሚካኤል የሚለው ስም ቃሉ #የዕብራይስጥ ነው፤
#ሚ - የሚለው «መኑ» ማለት ነው፥
#ካ - የሚለው «ከመ» ማለት ሲሆን፥
#ኤል - ማለት ደግሞ «አምላክ» ማለት ነው።
ይህን ማለትም የቅዱስ ሚካኤልን ስም በጠራን ቊጥር የምንመሰክረው ስለ እግዚአብሔር ነው፤
በመሆኑም እግዚአብሔርን በባሕርይ የሚመስለው፥ በሥልጣንም የሚተካከለው፥ በምድርም በሰማይም እንደሌለ የሚናገር ልዩ፥ ክቡር ስም ነው።
የነቢያት አለቃ ሙሴ ባሕረ ኤርትራን ለሁለት ከፍሎ ሕዝቡን ያሻገረለትንና ፈርዖንን ከነሠራዊቱ ያሰጠመለትን አምላክ እግዚአብሔርን በመዝሙር ሲያመሰግን፥ «አቤቱ በአማልክት መካከል (በስም አማልክት ከሚባሉ፥ በስመ አማልክት ከሚጠሩ፥ አንድም አማልክት ዘበጸጋ ከተባሉ ከነቢያት ከካህናት መካከል) አንተን የሚመስል ማነው? በቅዱሳንም ዘንድ እንደ አንተ የከበረ ማነው?» ብሏል። ዘጸ ፲፭፥፲፩። ቅዱስ ዳዊትም፦ «አቤቱ፥ ከአማልክት የሚመስልህ የለም፤» ብሏል። መዝ ፹፭፥፰
እግዚአብሔር ግን ኢያሱን አስነስቶ አረጋግቷቸዋል:: ቅዱስ ሚካኤል 40ውን ዘመን እሥራኤልን ደመና ጋርዶ: መና አውርዶ: ክንፉን ዘርግቶ: ጠላትን መክቶ ከሙሴ ጋ እንደ መራቸው ከኢያሱ ጋርም ይሆን ዘንድ ከሰማይ ወረደ::
+በኢያሪኮ አካባቢም የተመዘዘ ሰይፉን ይዞ በግርማ ለኢያሱ ታየው:: ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ "አንተ ከእኛ ወገን ነህን? ወይስ ከጠላቶቻችን?" ሲል ጠየቀው:: ቅዱስ ሚካኤልም መልሶ "እረዳህ ዘንድ እነሆ የሠራዊት አለቃ ሆኜ ተሹሜ መጥተቻለሁ" አለው ረድኤቱ አይለየን።

ምሕረቱ ፥ ርኅራኄው ፥ ይቅርታው ባህሪው የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ለኛም ምሕረት ይቅርታን ያድለን ዘንድ ከጌታህ አማልደን”

ይቆየን

”አንኳን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሰችሁ!”“በማርያም ልደት ዛሬ ደስታ ሆነ!” (ቅዱስ ያሬድ)በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት ፩ ቀን የእመቤታችን የ...
09/05/2025

”አንኳን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል አደረሰችሁ!”

“በማርያም ልደት ዛሬ ደስታ ሆነ!” (ቅዱስ ያሬድ)

በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት ፩ ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት እግዚአብሔር አስቀድሞ በትንቢት፣ በምሳሌና በራእይ የሰውን ልጅ ድኅነት በጉጉት ሲጠባበቁ ለነበሩ ነቢያት ገልጿል፡፡

ተአምር በእንተ ልደታ

ልመናዋ ክብሯም በኛ ለዘላለም በውነት ይደርብንና አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ፣በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ያደረገችው ተአምር ይህ ነው፡፡

የእመቤታችንን ልደቷንና ከዘመዶቿና ከሰውም ሁሉ ይልቅ ፈጽማ እንድትከብር ታውቁ ዘንድ እንነግራችኋለን፡፡

የእስራኤል ወገኖች ግን በልቡናቸው ሰይጣን አድሮባቸዋልና ወገናቸውን ሰብስበው የምትረቡት እንደሌለ አታውቁምን ኢያቄምና ሐና በኛ በጠላትነት ተነሥተውብናልና ብለው ተማከሩ፡፡

እኛ ባሮቻቸው ሁነን እነሱ በኛ ነግሠው ይኖራሉና፣ ሁላችሁም ታውቁ ዘንድ ሐና በፀነሰች ጊዜ ያደረገቸውን አይታችኋል፡፡

የጦሊቅ ልጅ ሳምርም በኢያሪኮ ባለች በዶይቅ በሞተ ጊዜ ወደ መቃብር ስንወስደው ሐና በጐዳና መካከል መጥታ ያባቷ ወንድም ስለ ሆነ ያንን ፈጽማ ትወደው ነበርና እያለቀሰች ያልጋውን ሸንኮር ያዘች፡፡

ያን ጊዜ ተነሥቶ የውነተኛ ፀሐይ እናቱ ሆይ አንድነት፣ፍቅር ይገባሻል ብሎ ተናገራት፡፡

ሁለተኛም ካንች የምትወለደውን ማርያምን መልአክ የሷን ነገር ሲናገር ሰማይና ምድርን የፈጠረ እናቱ ናት ሲል ሰምቻለሁና አላት፡፡

እንስሳትንና ሰውንም የሚታየውን፣የማይታየውንም የፈጠረ፡፡

አሁንም የእስራኤል ወገኖች ሆይ ለምን ታንቀላፋላችሁ የፈራሽ በስባሽ ወገን የሚሆኑ የኢያቄምና የሐናንስ ነገር ለምን ቸል ትላላችሁ ዛሬ በቤተ መቅደስ ሳለች ከሳቸው ስለ ተወለደች የሷን ነገር ሰምታችኋልና፡፡
ሰምተው እርስ በርሳቸው ሌሊት ወደ ቤተ መቅደስ ሒደን እንግደላት ባገር የተውናት እንደሆነ ሕዝቡን ታሳምፃቸዋለች ተባባሉ፡፡

በነጋውም በመንፈቀ ሌሊት ተነሥተው ወደ ምኵራብ ገቡና ከዚያ መላእክት ሲወጡ፣ሲወርዱ፣ባማረና ተነግሮ በማይፈጸም ምስጋናም ሲያመሰግኑ አገኙ፡፡

ልዩ እግዚአብሔር፣ልዩ ኃይል፣ልዩ ሕይወት፣የማይሞት ድንግል ክብርት ከምትሆን ከእመቤታችን የተወለደ አቤቱ ይቅር በለን፡፡ ልዩ እግዚአብሔር፣ልዩ ኃይል፣ልዩ ሕይወት፣የማይሞት በወዳጆቹ አድሮ የሚኖር በትሑታን የሚመሰገን እያሉ ሲያመሰግኑ አገኙ፡፡
ደጃፎቿም ሁሉ እንደሚነድ እሳት ሁነው አገኙ፣ አይተውም አፍረው ወደ ኋላ ተመለሱ፡፡

ልመናዋ ክብሯም በኛ ለዘለዓለም በውነት ይደርብን በአማላጅነቷ አትለየን፣
የእግዚአብሔር ቸርነት አይለየን፡፡

ምንጭ፡- ተአምረ ማርያም መጽሐፍ

https://youtu.be/9PAi7aMJs08
20/03/2025

https://youtu.be/9PAi7aMJs08

የስውሯ ማርያም ያልተሰማ ጉድ ስውሯ ማርያም ድጋሚ አንሄድም ብለው አማረሩ የሌባ ተባባሪዎችን አንፋታም አሉ

https://youtu.be/q4OcmX_VtOE
13/03/2025

https://youtu.be/q4OcmX_VtOE

ስለ ስውሯ ማርያም ዝም አልልምስለ እውነት ከሆነ ስውሯ ማርያም እመቤቴ ለኔ ብዙ ጊዜ ሄጃለሁ ብዙ ነገርም ተደርጎልኛል ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ከተወሰነ ጊዜ በኃላ ግን ያየሁት ነገር ...

ተአምር የትንሣኤው ሕያው ምስክር የኾነው ተአምራዊው ብርሃን ዛሬም በሰዓቱ በርቷል።ጌታችን ከሞት ከተነሣ በኋላ በተቀበረበት ጎልጎታ ባለው ቅዱስ መቃብር ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት የሚፈጸሙ ሲ...
04/05/2024

ተአምር
የትንሣኤው ሕያው ምስክር የኾነው ተአምራዊው ብርሃን ዛሬም በሰዓቱ በርቷል።

ጌታችን ከሞት ከተነሣ በኋላ በተቀበረበት ጎልጎታ ባለው ቅዱስ መቃብር ብዙ ድንቅ ድንቅ ተአምራት የሚፈጸሙ ሲሆን ከእነዚህ ተአምራት ውስጥ በየዓመቱ የማይቀረውና በትንሣኤው ዋዜማ የሚደረገው የትንሣኤው ብርሃን ነው።

ከጌታችን ትንሣኤ በዓል አስቀድሞ በመላው ዓለም ያሉ ምሥራቃዊውንም የኦሬንታል ኦርቶዶክሳውያን አብያተክርስቲያናት ታላቁን የጌታን ጾም ጾመው እንደጨረሱ በትንሣኤው ዋዜማ በየዓመቱ ይኸው ብርሃን ለምስክርነት ሳይቀር በየዓመቱ በዛሬው ዕለት ብቻ በተአምር ይበራል።

ይኸ ብርሃን ከጌታችን የመቃብር ስፍራ ላይ በቅድስት ዕሌኒ ንግሥት በተሠራው ቤተክርስቲያን ውስጥ ልክ በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር 8:30 ሲሆን ከመላው ዓለም የተሰባሰቡ ክርስቲያኖች በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ተሰባስበው በፓትርያርክ ቴዎፍሎስ አራተኛ መሪነት ጸሎት በማድረግ እየተጠበቀ ሰዓቱ ሲደርስ ብርሃኑ በተአምር በሻማዎቹ ላይ ይበራል።

ብርሃኑ ተአምራዊ ስለሆነ በምንም ከሳይንሳዊ ምርምር ሁሉ በላይ የሆነ ሲበራም ምንም የማያቃጥል ከተፈጥሮአዊ እሳት የተለዬ ነው።

ፓትርያርኩ ሰዓቱ ሲደርስ 33 ሻማዎችን ይዘው ይገባሉ ከየት የማይባል ብርሃን በሻማው ይበራል ከቤተክርስቲያኑ ውስጥ ያሉ ሻማዎችን ሁሉ ያቀጣጥላቸዋል አስደናቂ የሚያደርገውም ከበራ በኋላም ለ33 ደቂቃዎች ቆይቶ የሚጠፋ መሆኑ ነው ይኸ ተአምር ከጌታችን ትንሣኤ ጋር ተያይዞ በየዓመቱ ሳይታጎል የሚደረግ ልዩ ተአምር ነው።

>+"+ አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ:: አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በዪ:: እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው:: ትሑትም ሆኖ በአህያም: በአህያይቱ ግልገል በውርንጫይቱ ላ...
28/04/2024

>+"+ አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ:: አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በዪ:: እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው:: ትሑትም ሆኖ በአህያም: በአህያይቱ ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል:: +"+ (ዘካ. 9:9)

>

  #መጋቢት 27  #ጥንተ ስቅለት።††† "እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን"(ትንቢተ ኢሳይያስ፦፶፫፥፭)†††የዓለሙ ቤዛ የዓለሙ ፈጣሪ አም...
05/04/2024


#መጋቢት 27
#ጥንተ ስቅለት።

††† "እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን"(ትንቢተ ኢሳይያስ፦፶፫፥፭)†††

የዓለሙ ቤዛ የዓለሙ ፈጣሪ አምላካችን
መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህቼ ዕለት
በመልዕልተ መስቀል እርቃኑን የተሰቀለበት
የድኃነታችን ቀን ናት።
መድኃኔዓለም ወኃቤ ሰላም
መኃርኩ ሰረይኩ ይበለን
በፈቃዳችን ላበድን በኪሎዋችን ልክ አፈር መሸከማችንን ለዘነጋን በዘረኝነት ለታወርን ማስተዋልን ያድለን ፍቅርን ይናኝብን ቅዱስ ዳዊት"አቤቱ ለአፌ ጠባቂ አኑር፥የከንፈሮቼንም መዝጊያ ጠብቅ"(መዝ፥፻፵፥፫)እንደለ ክፉ ተናግረን እግዚአብሔርን ከማሳዘን ሰዎችን ከማስቀየም እንቆጠብ ዘንድ ቅዱስ ፍቃድህ ይሁን #አሜን #አሜን #አሜን

Address

Addis Ababa
BOLE

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቢሲኒያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to አቢሲኒያ:

Share