አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ 2

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ 2 በቅዱስ ሚካኤል ስም በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።
(2)

+*" አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ "*+[በሕይወተ ሥጋ የሌለ ወዳጃችሁን ሻማ በማብራት በአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ስም ዘክሩት፥ ትምህርቱን ለብዙ ሰው share በማድረግ አዳርሱት።]=>አቡነ ...
18/11/2025

+*" አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ "*+
[በሕይወተ ሥጋ የሌለ ወዳጃችሁን ሻማ በማብራት በአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ስም ዘክሩት፥ ትምህርቱን ለብዙ ሰው share በማድረግ አዳርሱት።]

=>አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ አባታቸው መልአከ ምክሩ : እናታቸው ወለተ ማርያም ይባላሉ፡፡ የተወለዱበት ልዩ ቦታው ወሎ ክፍለ ሀገር ዳውንት ነው፡፡ በተወለዱ ዕለትዐተነስተው በእግራቸው ቆመው ሦስት ጊዜ "ስብሐት ለአብ: ስብሐት ለወልድ : ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ" ብለው አመስግነዋል፡፡
+የስማቸው ትርጓሜ "የአብ : የወልድ : የመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ" : አንድም "የክርስቶስ እስትንፋስ" ማለት ነው፡፡

ቅዱስ ሚካኤል እየጠበቃቸውና በመንገዳቸው ሁሉ እየመራቸው ነው ያደጉት፡፡ መንፈስ ቅዱስ ልቡናቸውን ብሩህ አድርጎላቸው በ5 ዓመታቸው የቅዱሳት መጽሐፍት ቃላትን፣ ብሉያትንና ሐዲሳትን፣ ድርሳናትንም ጠንቅቀው ዐውቀዋል፡፡
+በተወለዱ በ14 ዓመታቸው ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ደብረ ሐይቅ ገዳም ሄደው ከባሕር ዳር ቆመው የሙሴን ጸሎት ወደ እግዚአብሔር በጸለዩ ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ባህሩን አሻግሯቸው ወደ ቤተክርስቲያን ገብተዋል፡፡ ለ3 ዓመትም በኃይቅ ገዳም ለመነኮሳት
እንጨት በመልቀምና ውሃን በመቅዳት : ለአባቶች መነኮሳት ምግብ ሊሆናቸው ከባህር ውስጥ አሳን በማውጣት አገልግለዋል፡፡

+አባታችን እስትንፋሰ ክርስቶስ 40 መዓልትና 40 ሌሊት ከጾሙ በኋላ ምንም እህል ሳይቀምሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ ለሙሴ በደብረ ሲና እንደሰጠው ለአባታችንም ወደ እርሳቸው መጥቶ ዓሥሩን ቃላተ ኦሪትና ስድስቱን ቃላተ ወንጌል በውስጣቸው የተጻፈባቸው ሁለት
ጽላቶችን ሰጥቷቸዋል፡፡
+አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከሠሩ በኋላ ዕለቱን ስንዴ ዘርተው፣ ወይን ተክለው፣ ጽድን ወይራንና ግራርን ተክለው በአንዲት ቀን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ዕለቱን አድርሰዋል፡፡ ስንዴውን ለመስዋዕት
ወይኑን ለቁርባን በታምራት አድርሰዋል፡፡
+አባታችን በጸሎት ላይ እንዳሉ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ተልኮ መጥቶ አባታችንን በደመና ጭኖ ወስዶ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፊት አቆማቸው፡፡

ጌታንም በቅዱሳኖቹ ሁሉ እንዲባረኩ ካደረጋቸው በኋላ መልአኩን ‹‹ወደ ተወለድኩባትና ወደ ኖርኩባት ቦታ ወደ ኢየሩሳሌም አድርሰው›› ብሎት ኢየሩሳሌምን አሳልሞ ሀገራችን መልሶ አምጥቷቸዋል፡፡ ሁሉንም የኢትዮጵያን ቅዱሳት ገዳማትንም ተዘዋውሮ ሲጎበኙ በሕይወተ ሥጋ
የሌሉት የየገዳማቱ ቅዱሳን ሁሉ በአካል ይገለጡላቸው ነበር፡፡

+ጎጃም ውስጥ እያስተማሩ፣ እያጠመቁ፣ የታመሙትን እየፈወሱ፣ የዕውራንን ዐይን እያበሩና ሙታንን እያስነሱ ብዙ ካገለገሉ በኋላ ለዘጠኝ ዓመታት በባሕር ውስጥ ገብተው ቁልቁል ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ጸልየው የምሕረት ቃልኪዳን ተቀብለዋል፡፡ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ጌታችን መጥቶ ‹‹ከመነኮሳት ሁሉ ብልጫ ያለህ ወዳጄ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ምሬልሃለሁ ከዚህች ባሕር ውጣ›› በማለት በሞት የሚያርፉበትን ቦታ ነግሯቸዋል፡፡
+ጻድቁ ወደ ደብረ አስጋጅ በሚሄዱበት ጊዜ ጸሐይ ልትገባ ስትል ‹‹በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አውግዤሻለሁ፡፡ ለመስፍን ኢያሱ በገባኦን እንደቆምሽ አሁን ቀጥ ብለሽ ቁሚ›› ብለው ገዝተው ፀሐይን
አቁመዋል፡፡

+አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስም ደብረ አስጋጅ ሲደርሱ ፀሐይ አፍ አውጥታ ‹‹አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ሆይ እገባ ዘንድ ፍታኝ›› ስትላቸው ‹‹እግዚአብሔር ይፍታሽ›› ባሏት ጊዜ ጠልቃለች፡፡

ጻድቁ ሌላው በእጅጉ የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡
+በአምላክ ፣ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ፣ በቅዱስ ሚካኤልና በቅዱስ ገብርኤል ልቡና የሚገኝ እንደ መልክአ ኢየሱስ ያለች እጅግ አስገራሚ ጸሎት አለቻቸው፤ እርሷን ጸሎት በጸለዩ ጊዜ እልፍ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጣሉ፡፡ ጸሎቷም የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች እያንዳንዱ የሰውነት ክፍሎቹ የተቀበሉትን ጸዋትዎ መከራዎች ሁሉ ታዘክራለች፡፡ በእያንዳንዱ ክፍልም የጸሎት ማሳረጊያ አቡነ ዘበሰማያት ይደግማሉ፡፡

+ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡ እያንዳንዱን የመድኃኔ ዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች መከራዎቹን
የምታዘክረውን ይህቺን በአምላክ ልቡና ያለች ግሩም የሆነች ጸሎት "ነፍሳትን ከሲኦል አታወጣም" ብሎ የሚጠራጠር ቢኖር ግን መንግስተ ሰማያትን አያያትም፡፡

+ጻድቁ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ታህሳስ 9 ቀን ተወልው ሚያዝያ 9 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡
(ገድለ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ)
=>አምላከ ቅዱሳን በጻድቁ አማላጅነት ሃገራችንን
ይጠብቅልን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ 2

በ23ኛ ዙር የበገና እጣ በ200 ብር የተያዙ ቁጥሮች እጣውን ለማግኘት ቴሌግራም ላይ ይቀላቀሉ። t.me/abizeeotcwin134567810121516181921222324262728293031353...
17/11/2025

በ23ኛ ዙር የበገና እጣ በ200 ብር የተያዙ ቁጥሮች እጣውን ለማግኘት ቴሌግራም ላይ ይቀላቀሉ። t.me/abizeeotcwin

1
3
4
5
6
7
8
10
12
15
16
18
19
21
22
23
24
26
27
28
29
30
31
35
39
43
44
47
53
55
58

በ23ኛ ዙር የበገና እጣ ለመሳተፍ

ከ1-60 ካሉት መርጣችሁ

እጣውን በቴሌብር 0933143133
በንግድ ባንክ 1000145090176
አቢሲኒያ ባንክ 47056497
አዋሽ ባንክ 013200909837300
አቤኔዘር ገዛኸኝ ስሜ

እጣውን ቆርጣችሁ
ስም ስልክ ሪሲት እጣ ቁጥር በቴሌግራም t.me/abigezenige ይላኩ።

እጣው ተቆርጦ ሲያልቅ በፌስቡክ ቀጥታ ስርጭት ይወጣል ።

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

https://youtu.be/E5a-9079ur4?si=SL_F0rOOjQRWqMHH
31/10/2025

https://youtu.be/E5a-9079ur4?si=SL_F0rOOjQRWqMHH

ይህ አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ነው ከተለያዩ ሰዎች ጠቃሚ የሕይወት ተሞክሮዎች የምንዳስስበት እንዲሁም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን እየጋበዝን እንጠይቃለን ታሪካዊ ቭሎጎች አዝናኝ እና ት...

ዛሬ በእመቤታችን ዕለት ቀን 20ኛ ዙር እጣ ተጀምሯል። በ200 ብር በገና። ገቢው ለቅድስት አርሴማ ንግሥ ለነዳያን መዘከሪያ ይሆናል። እጣው የሚወጣው መስከረም 27 ምሽት 3 ምሽት በፌስቡክ ...
01/10/2025

ዛሬ በእመቤታችን ዕለት ቀን 20ኛ ዙር እጣ ተጀምሯል።
በ200 ብር በገና። ገቢው ለቅድስት አርሴማ ንግሥ ለነዳያን መዘከሪያ ይሆናል። እጣው የሚወጣው መስከረም 27 ምሽት 3 ምሽት በፌስቡክ ቀጥታ ስርጭት ይሆናል።
19ኛ ዙር እጣ ወጥቷል።
1ኛ እጣ 2 ቁጥር ሰሎሞን የበግ አሸናፊ
2ኛ እጣ 90 ቁጥር ሙሉ የበገና አሸናፊ ሆነዋል።

20ኛ ዙር የበገና እጣ ተጀምሯል።

እጣውን በቴሌብር 0933143133
በንግድ ባንክ 1000145090176
አቢሲኒያ ባንክ 47056497
አዋሽ ባንክ 013200909837300
አቤኔዘር ገዛኸኝ ስሜ

እጣውን ቆርጣችሁ
ስም ስልክ ሪሲት እጣ ቁጥር በቴሌግራም t.me/abigezenige ይላኩ።

🌹 +         + 🌹                መስከረም  21🍂 እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ 🙏 🍂   በቤተ ክርስቲያናችን...
30/09/2025

🌹 + + 🌹
መስከረም 21

🍂 እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ 🙏

🍂

በቤተ ክርስቲያናችን ከሚዘከሩ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ክብረ በዓላት መካከል መስከረም ፳፩ ቀን የሚውለው በዓል ‹‹ብዙኃን ማርያም›› በመባል ይታወቃል፡፡
በዓሉ በሁለት ዐበይት ምክንያቶች ይከበራል፤

#የመጀመሪያው በቤተክርስቲያን ታሪክ በ፫፻፳፭ ዓ/ም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ውሳኔ ለማዘጋጀት ከሩቅም ከቅርብም በኒቂያ የተሰባበሰቡት ቀን፤

#ሁለተኛው ደግሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ዕፀ መስቀል / ግማደ መስቀሉ / በግሸን ደብረ ከርቤ የተቀመጠበት ዕለት መኾኑ ነው፡፡

+ + + + + +

🍂 በ፫፻፳፭ ዓ.ም አርዮስ የሚባል መናፍቅ የእግዚአብሔር ወልድን የባሕርይ አምላክነት አልቀበልም በሚል ክህደት እርሱ ተሰናክሎ ለሌሎችም መሰናክል ኾነ፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት አርዮስ ክህደቱን እንዲተው ቢመክሩትም ሊመለስ አልቻለም፡፡ ይህ የአርዮስ ክህደትም በሊቃውንቱ መካከል መለያየትን ፈጥሯል፡፡

🍂 ጊዜው ታላቁ ንጉሥ #ቈስጠንጢኖስ ‹‹አብያተ ጣዖታት ይትአጸዋ አብያተ ክርስቲያናት ይትረኀዋ፤ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ! አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ!›› የሚል ዐዋጅ የነገረበት ወቅት ነበርና ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ በአርዮስ ክህደት ምክንያት በኒቅያ የሃይማኖት ጉባኤ እንዲካሔድ በየአገሩ ላሉ ሊቃውንት መልእክት አስተላለፈ፡፡

🍂 በዚህም መሠረት ከሚያዝያ ፳፩ ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም ፳፩ ቀን ድረስ ፳፫፻፵፰
/ / ሊቃውንት በኒቅያ ተሰበሰቡ፡፡

#ኒቅያ ለዚህ ጉባኤ የተመረጠችበት ምክንያትም ጳጳሱን ከማኅበረ ካህናቱ፤ ንጉሡን ከሠራዊቱ ጋር አጠቃላ ለመያዝ የምትችል ሰፊና ምቹ ቦታ ከመኾኗ ባሻገር ለኹሉም አማካይ ሥፍራ ስለ ነበረች ነው፡፡

🍂 በጉባኤው ከተሰበሰቡ ሊቃውንት መካከልም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ሙታንን ያስነሡ፣ ለምጽ ያነጹ፣ አንካሳ ያረቱ፣ የዕውራንን ዓይን ያበሩ ድውያንን የፈወሱ፣ ሌላም ልዩ ልዩ ተአምር ያደረጉ፤ እንደዚሁም ስለ ርትዕት ሃይማኖታቸው በመጋደል ዓይናቸው የፈረጠ፣ እጃቸው የተቈረጠ ይገኙበታል፡፡

ሊቃውንቱ ሱባዔ ይዘው በጸሎት ከቆዩ በኋላ ኅዳር ፱ ቀን በንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት፣ በ #እለእስክንድሮስ አፈ ጉባኤነት ጉባኤው ተጀመረ፡፡ ንጉሡ ሊቃውንቱን "ስማችሁን፣ አገራችሁንና ሃይማኖታችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ" ባላቸው ጊዜም ከ፳፫፻፵፰ቱ (2348) መካከል ፫፻፲፰ (318) ሊቃውንት ሃይማኖታቸውን ሲገልጹ እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ኾነው
" ፤ ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በመለኮት፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ፣ በህልውና አንድ ነው" ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡

🍂 ንጉሡም " #ሃይማኖት እንደ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት ይኹን"
ብሎ ዐዋጅ አስነግሯል፡፡ እነዚህ ሊቃውንት በኦሪት ዘፍጥረት የተጠቀሱት ፫፻፲፰ቱ የአብርሃም ብላቴኖች ምሳሌዎች ናቸው
/ዘፍ.፲፬፥፲፬/፡፡

፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት በጉባኤው አርዮስን አውግዘው በመለየት

"ነአምን በአሐዱ አምላክ፤ በአንድ አምላክ እናምናለን" የሚለውን የሃይማኖት ጸሎት (የሃይማኖት መሠረት) እና ሌሎችንም የሃይማኖት ውሳኔዎችን ደንግገዋል፡፡

🍂 ሊቃውንቱ ጉባኤውን ያካሔዱት ኅዳር ፱ ቀን ይኹን እንጂ በአንድነት የተሰባሰቡት ቀን ስለ ነበረ ይህ ዕለት " " እየተባለ ይጠራል፡፡ ብዙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ለሃይማኖታዊ ጉባኤ የተሳባሰቡበት ዕለት ነውና፡፡

+ + + + + +

🍂 በሌላ በኩል መስከረም ፳፩ ቀን የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በአምባሰል ተራራ በግሸን ደብረ ከርቤ የገባበትና በዓሉ የከበረበት ዕለት ነው፡፡ ታሪኩም በአጭሩ የሚከተለው ነው፤

መንፈሳዊና ደግ ንጉሥ ነበሩ፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ቸነፈር ተከሥቶ ሕዝቡ ስለ ተሰቃየባቸው እጅግ አዘኑ፤ በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱም ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላኩ ባሕታዊ መጥተው "የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል አስመጥተህ በአገርህ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሠርተህ ብታስቀምጥ ረሃቡ፣ ቸነፈሩ ኹሉ ይታገሥልሃል" አሏቸው፡፡

🍂 ከብዙ ገጸ በረከት (ስጦታ) ጋር
"የጌታችንን መስቀል ላኩልኝ" የሚል መልእክት አስይዘው መልእክተኞችን ወደ ኢየሩሳሌም ሰደዱ፡፡ መልእክተኞቹም በታዘዙት መሠረት መስቀሉን ይዘው መምጣታቸውን ዐፄ ዳዊት ሲሰሙ "ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት" ብለው መስቀሉን ለመቀበል ጉዞ ጀመሩ፡፡

ዐፄ ዳዊት ስናር (ሱዳን) ደርሰው ከመልእክተኞቹ ጋር ተገናኝተው መስቀሉን በክብር አጅበው ወደ መካከል ኢትዮጵያ ለማስገባት ሲነሡም ከበቅሏቸው ወድቀው ጥቅምት ፱ ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፤ በዚህም ሠራዊታቸው ተደናግጠው የጌታችንን መስቀል እዚያው ትተው የዐፄ ዳዊትን አስከሬን ይዘው ተመለሱ፡፡

🍂 #መስቀሉ በስናር ከቆየ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዘርዐ ያዕቆብ ሲነግሡ ወደ መሃል ኢትዮጵያ አምጥተው ቤተ ክርስቲያን አሠርተው ለማስቀመጥ ቢያስቡም ምቹ ቦታ ግን ሊያገኙ አልቻሉም ነበር፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው ምቹ ቦታ ሲፈልጉ መስቀሉን በኤረር ተራራ፣ በደብረ ብርሃን፣ በመናገሻ ማርያም ዓምባ፣ በእንጦጦ ጋራ ብዙ ጊዜ አስቀምጠውት ቆይተዋል፡፡

🍂 #መስቀሉ በእንጦጦ ጋራ ሳለ እግዚአብሔር አምላክ "አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል፤ መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" የሚል ቃል ለንጉሡ በራእይ ነገራቸው፡፡ መስቀሉን ወደ ወሎ ሀገረ ስብከት እንዲወስዱትም አዘዛቸው፡፡ ንጉሡና ሠራዊታቸው በእግዚአብሔር መሪነት መስቀሉን ይዘው ወሎ ሲደርሱም ጌታችን ወደ አምባሰል እያመለከተ

" ፤
መስቀሌን በመስቀለኛ ተራራ ላይ አስቀምጥ" ይላቸው ነበር፤ ንጉሡ መስቀሉን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ መስቀለኛው የግሸን ተራራን አገኙ፤ በዚያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተው በ፲፬፻፵፮ (1446) ዓ.ም የጌታችንን መስቀል በክብር አስቀምጠውታል፡፡

🍂 ከዚህ በኋላ ንጉሡ ‹‹መካከሏ ገነት፤ ዳሯ እሳት ይኹን! የበረረ ወፍ፣ የሠገረ ቆቅ አይታደንባት! በድንገት ሰው የገደለ፣ ቋንጃ የቈረጠ ወንጀለኛ አይያዝባት!›› ብለው ዐዋጅ ነግረዋል፡፡ የእመቤታችን ጽላትም አብሮ በግሸን ደብረ ከርቤ እንዲቀመጥ አድርገዋል፡፡ ስለዚህም መስከረም ፳፩ ቀን በየዓመቱ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡

ኀጢአታቸውን ለካህን ተናዘው፣
ንስሐ ገብተው በዚህ ዕለት ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ በመሔድ የሚጸልዩና የሚማጸኑ ምእመናን ኹሉ እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ የምሕረት ቃል ኪዳን እንደሚያገኙም
ጤፉት በተባለችው መጽሐፍ ተጠቅሷል፡፡

🍂 + + + 🍂

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት 🙏

የቅዱስ መስቀሉ ረድኤት ጥበቃ አይለየን 🙏

በዓሉም የሰላም የበረከት የረድኤት በዓል ይሁንልን🙏





አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ
በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው

የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://youtube.com/channel/UC4n7gQxnj7V189_uU_Jqpkg

የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፤ ፈጣን መረጃዎችን ያግኙ https://t.me/abizeeotc

አጫጭር ትምህርታዊ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የቲክ ቶክ አማራጫችንን ይመልከቱ
https://www.tiktok.com/?_t=8VvQdXCnxY6&_r=1

30/09/2025

መስከረም 21 ወደ ጻድቃኔ ማርያም ደርሶ መልስ ጉዞ ተዘጋጅቷል።
መነሻ መስቀል አደባባይ መገናኛ እና ጣፎ
11:30
0933143133 ይደውሉ።

17ኛ እጣ 60 ሰው በ200 ብር ብቻየክርስትና ስም ስልክ ቁጥር እጣ ቁጥር በቴሌግራም t.me/abigezenige ይላኩ።የተያዙ ቁጥሮች6716171924272935384143531ኛ እጣ በገና2ኛ...
13/08/2025

17ኛ እጣ 60 ሰው በ200 ብር ብቻ
የክርስትና ስም ስልክ ቁጥር እጣ ቁጥር በቴሌግራም t.me/abigezenige ይላኩ።

የተያዙ ቁጥሮች
6
7
16
17
19
24
27
29
35
38
41
43
53

1ኛ እጣ በገና
2ኛ እጣ አርጋኖን የጸሎት መጽሐፍ የተደጎሰ
3ኛ እጣ የአቡነ እጨጌ ቅዱስ ስዕል

እጣውን በቴሌብር 0933143133
በንግድ ባንክ 1000145090176
አቢሲኒያ ባንክ 47056497
አዋሽ ባንክ 013200909837300
አቤኔዘር ገዛኸኝ ስሜ

በነገራችን ላይ በእጣው የምትሳተፉ ሰዎች የክርስትና ስም ላኩልኝ ያልኳችሁ በጾመ ፍልሰታ በኪዳንና በቅዳሴ ላይ እንዲነሳ ስማችሁን ለደብራችን ለመስጠት ነው።
200 ብሩ እጣው ባይደርሳችሁም በጸሎት ስማችሁ ይነሳል፤ ለዝክር እና ለቆራቢያን ነጭ ልብስ መግዣ ይሆናል።
አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ
https://t.me/abizeeotc
🇯 🇴 🇮 🇳 &🇸 🇭 🇦 🇷 🇪
✥┈┈•◦●◈◎❖◎◈●◦•┈┈✥
✧━━━━━━━━━━━━━━━━━✧
❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ

ሰኔ -21 "የሰኔ ጎልጎታ" ሙሉ ጸሎት። ጸልዩትና በረከት አግኙ። ለወዳጆቻችሁ ሼር አድርጉት።አንድ፡ አምላክ፡ በሚሆኑ፡ በአብ፡ በወልድ፡ በመንፈስ ቅዱስ፡ ስም፡ በእውነት፡ እናምናለን፡፡ ልመ...
27/06/2025

ሰኔ -21 "የሰኔ ጎልጎታ" ሙሉ ጸሎት።
ጸልዩትና በረከት አግኙ። ለወዳጆቻችሁ ሼር አድርጉት።

አንድ፡ አምላክ፡ በሚሆኑ፡ በአብ፡ በወልድ፡ በመንፈስ ቅዱስ፡ ስም፡ በእውነት፡ እናምናለን፡፡ ልመናዋ፡ ክብሯ የልጅዋም፡ ቸርነት፡ ከወዳጆችዋ ፡ከሁላችን፡ ጋር፡ ይኑር ለዘለዓለሙ፡ አሜን፡፡

አምላክን፡ የወለደች፡ በውስጥ፡ በአፍአ ንጽሕት: የምትሆን፡ የብርሃን፡ እናቱ፡ እመቤታችን እግዝእትነ፡ ማርያም፡ በሰኔ፡ ሃያ፡ አንድ፡ ቀን በጎልጎታ፡ ይኸውም፡ የጌታችን፡ የመድኃኒታችን፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ መካነ፡ መቃብር፡ በሚሆን እንዲህ፡ ስትል፡ የጸለየችው፡ጸሎት፡ ይህ፡ ነው፡፡

ልጄ፡ ወጃዴ፡ ጌታዬ፡ አምላኬና፡ ንጉሤ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ሆይ፡ ሰውን፤ ለማዳን፡ ስትል፡ በፈቃድህ፡ እኔ፡ ተወልደህ፡ ጡቶቼንም፡ጠብተህ፡ በግዕዘ፡ ህጻናት ብታድግ፡ ሰማይና፡ ምድር ፡ አይችሉህም እኮን፡፡ የዓለም፡ ዳርቻዎች፡ አይወስኑህም፡ ምድርም፡ ልትሸከምህ፡ አትችልም፡ ቀላያትና፡ አብርሕትም ከጥልቀታቸው፡ የተነሳ፡ የክረምት፡ ማዕበል፡ በእልፍኝህ አይመሉም፡ ኃያላት፡ መላእክትም፤ ቢሆኑ፡ ወደ፡ አንተ ሊቀርቡ፡ አይችሉም በማህፀኔ፡ ዘጠኝ፡ ወር፡ ከአምስት፡ ቀን ተሸክሜሃለሁና፡ ጡቶቼንም፡ አራት፡ ዓመት፡ እየጠባህ አድገሀልና፡ እለምንሃለሁ፡ አማልድሀለሁ፡ ሄሮድስ በምቀኝነት፡ ሊገድልህ፡ በፈለገ፡ ጊዜ፡ አንተን፡ በጀርባዬ አዝዬ፡ አራት፡ ዓመት፡ ከአንዱ፡ ሀገር፡ ወደ፡ አንዱ ሀገር፡ ተሰድጃለሁና፡አቤቱ፡ ጌታዬና ፡ አምላኬ፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ሆይ፡ ጸሎቴንና፡ ልመናዬን፡ ስማኝ፡፡ አቤቱ ማህፀኔን ፡ ዓለም፡ አድርገህ፡ ዘጠኝ፡ ወር፡ ከአምስት ቀን ተሸክሜአለሁና፡እለምንሃለሁ፡ አማልድሀለሁ፡፡ አቤቱ በቁርና፡ በብድር፡ ወራት፡ ከቤተልሔም፡ ከኔ መወለድህን አስብ፡፡

አቤቱ፡ ከአንተ ፡ ጋር፡ ከሀገር፡ ወደ፡ ሀገር፡ መሰደዴን፡ ስለአንተም፡ የደረሰብኝን፡ ጭንቅና፡ መከራ ረሀብና፡ ጥም፡ አስብ፡ የምለምንህም፡ ለደጋጎች ለጻድቃን፡ ብቻ፡ አይደለም፡ በዚህ፡ ዓለም ሳሉ ስሜን፡ ለሚጠሩ፡ መታሰቢያዬን፡ለሚያደርጉ በአማላጅነቴ፡ ለሚተማመኑ፡ ኃጥአንም፡ ነው፡ እንጂ፡፡ አቤቱ፡ ጸሎቴንና ፡ ልመናየዬን፡ አስተውል ከአንተ ፡ ዘንድ ፡ የምሻውን፡ የቃሌን፡ ልመና፡ ትሰማኝ ዘንድ፡ የልቦናዬን፡ ሀሳብ፡ ትፈጽምልኝ ዘንድ፡ በዚህች፡ ዕለትና ፡በዚህች፡ሰዓት፡ አስራ ሁለት የብርሃን፡ መላእክት፡ ሁለት፡ የይቅርታ መላእክት ሃያ፡ አራት፡ የምህረት፡ መላእክት ከእኔ ፡ ጋር፡ በመቆም፡ የልመናዬን፡ ቃል ይፈጹሙልኝ፡ ዘንድ፡ ላክልኝ፡፡ ካንተ ፡ ዘንድ፡ የምሻውን፡ ቸርነትህን አታርቅብኝ፡፡ ልጄ፡ወዳጄ፡ ሆይ፡ የዓለም፡ ሳይፈጠር፡ አስቀድሞ ከአንተ ፡ ጋር፡ በነበረ፡ በእግዚአብሔር፡ አብ፡ ባህርይ አባትህ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ ፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ፡ ሰማይና፡ ምድር፡ ተራሮችና ኮረብታዎች፡ ሰውና፡መላእክት፡ ፀሐይና፡ ጨረቃ ከዋክብት፡ ሳይፈጠሩ፡ ቀንና ሌሊት፡ ሳይለዩ፡ በነበረ በእግዚአብሔር፡ ስምህ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! የአብ፡ የባሕርይ፡ ሕይወቱ፡ የሆነ፡ ከአብ፡ የተገኘ፡ የአንተም፡ የባሕርይ፡ ሕይወትህ፡ በሆነ፡ ከአንተ፡ ጋር፡ የተካከለ፡ በጰራቅሊጦስ፡ መንፈስ ቅዱስ፡ ከኮከብ፡ መውጣት፡ በፊት፡ ከአንተ፡ ጋር፡ በነበረ፡ ፡አሁንም፡ ያለ፡ለዘለዓለምም፡ በሚኖር፡ በአብና፡ በመንፈስ ቅዱስ፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! እለ፡ ብዙኃት አዕይንቲሆሙ፡ በተባሉ፡ ፀወርተ፡ መንበርህን፡ በረዓድ፡ እየተንቀጠቀጡ መንበርህን፡ የሚሸከሙ፣ አንተን፡ ባዘለችህ፡ ጀርባዬ፡ ቃል፡ ኪዳን ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡
ልጄ፡ ወጃጄ፡ሆይ! አንተን ፡ ይገድሉሃል፡ እያልኩ ሳስብ፡ ከዓይኖቼ፡ እንደ ፡ ጠል፡ ውሃ፡ እየፈሰሱ በክብርት ሥጋህ፡ ላይ፡ በወረዱት ፡ ዕንባዎቼ፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ምን፡ ምን፡ ሊቀርብህ፡ የማይችል፡ አንተን፡ በሳሙ፡ ከንፈሮቼ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ከአንተ፡ ጋር፡ ቃል፡ ለቃል በተነጋገረ፡ አንደበቴ፡ ሱራፉኤል ፡ ኪሩቤል፡ድምፅህን ሰምተው፡ ፀንተው፡ ለመቆም፡ የማይቻላቸው፡ ጥዑማት ቃላትህን፡ በሰሙ፡ ጆሮዎቼ፡ ሰላሳ፡ ሶስት፡ ዓመት ከአውራጃ፡ ወደ አውራጃ፡ ከአንተ፡ ጋር፡ በተመላለሱ እግሮቼ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ወዳጄ፡ ሆይ! ልብሱ፡ እሳት፡ ክዳኑ፡ እሳት እየተባልክ፡ የምትመሰገን፡ አንተ፡ እሳተ፡ መለኮት ስትሆን፡ በጨርቅ፡ ተጠቅልለህ፡ በተጣልክበት፡ ዋሻ (በረት)፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ ፡ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! መልአከ፡ምክርህ፡ በሆነ፡ በቅዱስ፡ ሚካኤል፡ አንተን፡ በክብር፡ እወልድ፡ ዘንድ፡ የመወለድህንም፡ ዜና፡ (ምስራች)፡ በነገረኝ፡ በቅዱስ ገብርኤል፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! በምጥ፡ የተያዙትን፡ ሴቶች
ማህፀን፡ ይፈታ፡ ዘንድ፡ ሥልጣን፡ በሰጠኸው በቅዱስ፡ ሩፋኤል፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ ሆይ! የሰላምና ፡ የድኀንነት፡ መልአክ በሆነ፡ በቅዱስ፡ ዑራኤል፡ መልአክ፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ዙፋንህን፡ በሚሸከሙ፡ አርባዕቱ፡ እንስሳ፡ ኪሩቤል፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ፡ እግዚአብሔር፡ እያሉ፡ አኗኗርህን፡ በማመስገን መንበርህን፡ በሚያጥኑ፡ ሃያ፡ አራቱ ፡ ካህናተ፡ ሰማይ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ተልእኮቻቸውን፡ ለማፋጠን በሚፋጠኑ፡ ዘጠና፡ ዘጠኙ፡ ነገደ፡ መላእክት፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! እልፍ፡ ሆነው፡ በፊትህ በሚቆሙ፡ እልፍ፡ ሆነው፡ በኋላህ፡ በሚቆሙ፡ እልፍ ሆነው ፡ በቀኝህ፡ በሚቆሙ፡ እልፍ፡ ሆነው፡ በግራህ፡ በሚቆሙ፡ መላእክት፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ተራሮችና፡ ኮረብቶች ከመፈጠራቸው፡ አስቀድሞ፡ በፀሐይና፡ በጨረቃ ውስጥ፡ በሚመላለሱ፡ ብርሃናውያን፡ መላእክት፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ ፡ ወዳጄ፡ ሆይ!በሰማይ፡ ተድላ፡ መንበርህ በእግርህ፡ መረገጫ፡ በሆነ፡ በምድር፡ ቃል፡ ኪዳን ትገባልኝ ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! በኢየሩሳሌም፡ ሰማያዊት ሀገርህ፡ ብርሃነ፡ መለኮትህ፡ በተገለጠበት፡ በደብረታቦር ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! በደብረዘይት፡ በበአተ መንግስህ፡ በደብረ፡ ጽዮንም፡ ቃል፡ ኪዳን ትገባልኝ ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ሥርዓተ፡ ጥምቀትን ለመመሥረት፡ በትሕትና፡ በቆምክበት፡ በማዕከለ ዮርዳኖስ፡ በቅዱስ፡ መንፈስንና፡ ከአንተም፡ ዘንድ ፡ በወጣው፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ፡ በተቸነከሩት፡ እጆችህ፡ እና እግሮችህ፡ በቅዱስ፡ ሥጋህና፡ በክቡር፡ ደምህን፡ ቃል ፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ ፡ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ለሰው፡ ልጅ፡ ስትል በተቀበልከው፡ መከራና፡ ሞትህ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ቃል፡ ኪዳን ትገባልኝ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ሦስት፡ ሌሊትና፡ ሦስት መዓልት፡ በከርሠ፡ መቃብር፡ ባደርክበት፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! አዳምን፡ ከነልጆቹ፡ ለማውጣት በአካለ፡ ነፍስ፡ ወደ፡ ሲኦል፡ በመውረድህ፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ሙስና፡ መቃብርን፡ አጥፍተህ በሦስተኛው፡ ቀን፡ ከሙታን፡ ተለይተህ፡ በመነሳትህ በታላቅ፡ ምስጋና፡ ወደ፡ ሰማይ፡ በማረግህ፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! በማይሻረው፡ መንግሥትህ በሚያልፈው፡ ዘመንህ፡ ጉድለት፡ በሌለበት፡ የደስታ ወንዝ፡ ዝቅ፡ ከፍ፡ ዓፅንኖ በሌሉበት፡ መንበርህ፡ ቃል፡ ኪዳን ትገባልኝ ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ጼቃና ፡ ሴቃ፡ በተባሉ፡ ስሞችህ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ጠላትን፡ በሚያሸንፍ፡ በኢያኤል በጠላት፡ በማይጠቃ፡ በታዳኤል፡ ስምህ፡ ቃል፡ ኪዳን ትገባልኝ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ለመናገር፡ በማይቻል፡ በኀቡእ ስምህ፡ ለመተርጎም፡ በማይቻል፡ በክሱት፡ ስምህ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ሳዶር፡ አላዶር፡ ዳናት፡ አዴራ ሮዳስ፡ በተባሉ፡ በአምስቱ፡ ቅንዋተ፡ መስቀልህ፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ለመናገር፡ በማይቻል፡ በኀቡእ ስምህ፡ ለመተርጎም፡ በማይቻል፡ በክሱት፡ ስምህ ቃል፡ ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡

ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ሳዶር፡ አላዶር፡ ዳናት፡ አዴራ ሮዳስ፡ በተባሉ፡ በአምስቱ፡ ቅንዋተ፡ መስቀልህ፡ ቃል ኪዳን፡ ትገባልኝ፡ ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ከኔ፡ ጋር፡ ቆመህ፡ የልቦናዮን ሃሳብ ትፈጽምልኝ፡ ዘንድ የተዘጉ፡ በሮችን፡ ተከፍተው፡ የሞት፡ ስልጣን፡ ይወገድ ዘንድ፡ የርኩሳን፡ መናፍስት፡ ሥልጣን፡ ተሸሮ የጨለማ፡ ኃይል፡ ከሁሉ፡ ቦታ ፡ እንደ፡ ስም፡ ቀልጦ እንደ፡ ውሃ፡ ፈሶ፡ ይቀር፡ ዘንድ፡ ጣኦታትም ተደምስሰው፡ የጣኦታትም፡ ቦታና፡ አዳራሽ ተመዝብረውና፡ ተቀጥቅተው፡ ይጠፋ፡ ዘንድ እማልድሃለሁ፡፡ ዳግመኛ፡ በዚህ፡ ጸሎት የሚተማመኑትን፡ ከኃጢያት፡ ማሠሪያ፡ ሰማያዊ በሆነ በአባትህ፡ ሥልጣን፡ ማሕያዊ፡ በሚሆን በአንተ ስልጣን፡ የኃጢያት፡ ሥር፡ ተቆራርጦ የሚጥል፡፡ ነፍስን ከሥጋ፡ የሚለይ፡ ስሑል፡ ነበልባላዊ በሆነ፡ በመንፈስ ቅዱስ፡ ስም፡ ቃል የተፈቱ፡ እና ነፃ፡ የወጡ፡ ይሆኑ ፡ዘንድ፡ እማልድሃለሁ፡፡ ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ! ጸሎቴንና፡ ልመናዬን፡ ሰምተህ ወደ፡ እኔ፡ ትመጣ፡ ዘንድ፡ አለምንሃለሁ እማልድሃለሁ፡፡

ከመዓርና፡ ከወተት፡ ይልቅ፡ ስሟ፡ ጣፋጭ፡ የሆነው፡ አምላክን፡ የወለደች፡ የብርሃን፡ እናቱ እመቤታችን፡ ማርያም፡ እንዲህ፡ ብላ፡ በጸለየች፡ ጊዜ ምድር፡ ተነዋወጠች፡ ድንጋዮች፡ (አለቶች)፡ ተሰነጣጠቁ መቃብራትና፡ የተዘጉ፡ በሮችም፡ ተከፈቱ፡፡ በዚህ፡ ጊዜ ዘጠና፡ ዘጠኙ፡ ነገደ፡ መላእክት፡ ከአለቆቻቸው፡ ጋር ከሰማይ፡ ወርደው፡በግራ፡ እና በቀኝ፡ ቆሙ፡ ጌታ ኢየሱስ፡ ክርስቶስም፡ ከፀሐይና፡ ከጨረቃ፡ ሰባት፡ እጅ፡ የሚያበሩ፡ አራቱ፡ ብርሃናት፡ ከፊት፡ እና ከኋላው፡ እያበሩ፡ እልፍ፡ አእላፋት፡ ወትእልፊት አእላፋት፡ መላእክት በግራ፡ በቀኝ ተሰልፈው፡ ወረደ፡፡
እመቤታችን፡ ማርያም፡ ይኸን፡ ባየች፡ ጊዜ፡ ልጅዋን፡ ወዳጅዋን፡ በታላቅ፡ ግርማ፡ አየችው ፈጽሞም፡ አደነቀች፡፡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም፡ እናቱ፡ ማርያምን፡ ይህ ያስደንቅሻልን? ዘጠኝ፡ ወር፡ ከአምስት፡ ቀን፡ በማኀፀንሽ የተሸከምሺኝ፡ አይደለምን? አላት፡ ቡርክት ማርያምም፡ እንዲህ፡ ስትል፡ መለሰችለት ቀድሞ፡ በዚህ፡ አኳኋን፡ አላየሁህም፡ የሰውን፡ ሥጋ፡ ለብሰህ በማህፀኔ፡ ተሸከምኩህ፡ እንጂ፡ ዛሬ ግን እጅግ በሚያስደነግጥና፡ በሚያስፈራ፡ በመለኮት፡ ግርማ አየሁህ፡፡

ጌታችንም፡ መለሰ፡ እንዲህም፡ አላት፡ እናቴ ወላዴ፡ ሆይ፡ ዘጠኝ፡ ወር ከአምስት ፡ ቀን፡ በማህፀንሽ የተሸከምሽኝ፡ በጀርባሽም፡ ያዘልሽኝ ከመዓር ከስኳር፡ ይልቅ፡ የሚጣፍጥ፡ ከበረድ፡ የነፃ፡ ከገነት ፈሳሽም፡ ይልቅ፡ የሚጣፍጥ፡ ከበረድ፡ የነፃ፡ ከገነት ፈሳሽም፡ ውሃም፡ ንጹህ፡ የሆነ፡ ጡትሽን፡ ያጠባሽኝ እናቴ፡ ማርያም፡ ሆይ! ምን፡ ላደርግልሽ፡ ትፈቅጃለሽ እነሆ፡ የለመንሽውን ፡ ሁሉ፡ የምትሽውንም እፈጽምልሻለሁና፡፡

ቡርክት፡ መርገመ፡ ሥጋ፡ መርገመ ነፍስ፡የሌለባት፡ ማርያም፡ ለልጅዋ፡ ለወዳጅዋ፡ እንዲህ፡ ስትል፡ መለሰች፡-
ልጄ፡ ወዳጄ ኢየሱስ፡ ክርስቶስ፡ ሆይ፡ ተስፋዬ፡ አምባ፡ መጠጊያዬ አንተ፡ ነህ፡ እምነቴም፡ በአንተ፡ ላይ፡ ነው፡ ገና፡ በእናቴ፡ ማህፀን፡ ሳለሁ፡ አንተ፡ ጠበቅኸኝ፡
አፀናኸኝም፡ ለሁል፡ ጊዜም፡ መታሰቢያዬ፡ እና አለኝታዬ አንተ፡ ነህ፡ በኋለኛውም፡ ዘመን፡ ትንቢቱ ሲፈጸም፡ ሰዓቱ፡ ሲደርስ፡ በአንተ፡ ፈቃድ፡ በአባትህም ፈቃድ፡ ማኀየዊ፡ በሚሆን፡ በመንፈስ፡ ቅዱስም፡ ፈቃድ፡ ከእኔ፡ ተወልደሃልና፡ ዛሬ፡ የአንደበቴንም፡ ቃል፡ ጸሎቴን፡ እና ልመናዬን፡ ስማኝ፡ እኔ፡ ወላጅ፡ እናትህ፡ ማርያም፡ የምነግርህን፡ሁሉ፡አድምጥ፡ መታሰቢያዬን፡ ለሚያደርጉ፡ በስሜ ቤተክርስትያን ስለሚሰሩ፡ አንተ፡ የብርሃን፡ ማህደር፡ አዘጋጅህላቸው፡፡
አቤቱ ፡ ስለእኔ፡ የታረዘውን፡ ያለበሰ፡ በሰው፡ እጅ ያልተሰራውን፡ ዕፁብ፡ ድንቅ፡ የሆነውን የማይጠፋውን፡ የማያረጅውን፡ ዕውነተኛውን፡ ልብስ አልብሰው፡፡ አቤቱ፡ በእኔ፡ ስም፡ በሽተኞችን፡ የጎበኘ፡ (የጠየቀ) በቸርነትህ፡ እና ፡ በይቅርታህ፡ ጎብኘው፡ አቤቱ ስለስሜም፡ ብሎ፡ ለተራበ፡ ያበላውን፡ የሕይወት እንጀራ፡ አብላው፤ ሰማያዊ፡ በሆነ፡ ማዕድህም አስቀምጠው፣ ለተጠማ፡ ያጠጣውንም፡ በዔዶም፡ ገነት ከሚፈሰው፡ የሕይወት፡ ውሃ፡ አጠጣው፡፡
አቤቱ፡ ስለኔ ፡ ስም፡ ያዘነውን፡ ያረጋጋ፡ ነፍሱ ከሥጋው፡ በምትለይበት፡ ጊዜ፡ አጽናናው፡ ያዘነውንና የተከዘውንም፡ ያስደስተ፡ እና ፡ ያጽናናው፡ ስለስሜ፡ ብለህ አስደስተው፡ እድል፡ ፈንታውንም ፡ በዚህ ፡ ዓለም፡ ሳሉ፡ አንተን፡ በምግባር፡ በሃይማኖት፡ ደስ፡ ካሰኙህ ከቅዱሳን ፡ ጋር፡ አድርገው፡፡ አቤቱ፡ ምስጋናዬን፡ የሚናገሩትን፡ መጸሐፍት፡ የጻፈ ያጻፈ፡ በእኔ ፡ ስምም፡ የጸለየ፡ ሰማያዊ በሆነ፡ ዓምደ ብርሃን ፡ ስሙን፡ ጻፈው፡ በጸሎቱ፡ ተማምኖ፡ ይህን መጽሐፍ፡ በአንገቱ፡ ያነገተ፡ በሰው፡ ልብ ያልታሰበውን፡ ዓይን፡ ያላየውን፡ ጆሮ፡ ያልሰማውን መልካሙን፡ ዋጋ፡ ክፈለው፡፡ አቤቱ፡ በስሜ፡ የሚያምኑ፡ ሁሉ፡ ከሲዖል፡ ሞት ነፃ፡ የወጡ፡ ይሆኑ፡ ዘንድ፡ አለምንሃለሁ እማልድሃለሁ፡፡ አስቦ፡ መታሰቢያዬን፡ ያደረገ፡ (ዝክሬን የዘከረ)፡ በበዓሌም ፡ ቀን፡ በምመሰገንበት፡ ምስጋና የሚያመሰግኑ፡ እና፡ የሚዘምሩትን፡ አቤቱ ዝማሬ፡ መላእክትን፡ አሰማቸው፡፡

ጌታችንም፡- ይሁን፡ እንደወደድሽ፡ ይደረግልሽ፡ አላት፡፡ በአንቺ፡ ስም፡ ቤተክርስትያን፡ ያሳነፀ የብርሃን ቦታ፤ አዘጋጅለታለሁ፤ በመንግስተ ሰማያትም፡ ንፁህ ማደሪያ፡ እሰጠዋለሁ፡፡ ከባሕርይ፡ አባቴ፡ ከአብ ከባሕርይ፡ ሕይወቴ፡ ከመንፈስ፡ ቅዱስ ፡ ፊት አቀርበዋለሁ፡፡ የታመመን፡ በስምሽ፡ የጎበኘ፡ ታሞ በአልጋ፡ ላይ፡ በተኛ፡ ጊዜ፡ አጎበኘዋለሁ፡፡ ከዚህ ከሚያልፈው፡ ዓለም፡ ወደማያልፈው፡ ዓለም፡ በሞት፡ በተለየ፡ ጊዜም፡ መሪር፡ የሆነ፡ የሞት፡ ጽዋዓ አላጠጣውም፡ ወደ፡ መንግሥተ፡ ሰማያት፡ እስኪገባ ድረስ፡ አልለየውም፡ ርኩሳን፡ መናፍስትም በተከራከሩት፡ ጊዜ ፡ እኔ ጠበቃ፡ እሆነዋለሁ፡፡ በችግሩ ጊዜም፡ እድርስለታለሁ፡፡

ዳግመኛም፡ በስምሽ ለታረዘ (ለተራቆተ)፡ ያለበሰ፡ በሰው፡ እጅ፡ ያልተፈተለ እና ያልተሰራ፡ ኀብሩ፡ ዕጹብ፡ ድንቅ፡ የሆነ፡ የሕይወት ልብስ፤ አለብሰዋለሁ፡፡ የማይጠፋ፡ የማይጠወልግ የሕይወት ፡ አክሊልም፡ አቀዳጀዋለሁ፡ ስለ፡ አንቺም ብሎ፡ ከዕለት፡ ጉርሱ፡ ለተራበ፡ ያበላ ምድራዊ፡ ያይደለ፡ ሰማያዊ፡ የሆነ፡ የሕይወት፡ እንጀራ፡ አበላዋለሁ፡ ለተጠማ፡ ያጠጣ፡ ከመዓር ከስኳር፡ የሚጣፍጥ፡ ወተት፡ እጅግ፡ ነጭ፡ የሆነ ከዔዶም፡ ገነት፡ ከሚፈሰው፡ የሕይወት፡ ውሃ አጠጣዋለሁ፡፡ በስምሽ፡ ያዘነውን፡ የተከዘውን፡ ያስደሰተ፡ ስለ፡ ስምሽ፡ ብዬ
በሰማያዊ፡ አባቴ፡ ፊት፡ ደስ፡ አሰኘዋለሁ፡፡ የምስጋና መጽሐፍሽን፡ የጻፈ፡ ያጻፈ፡ እኔ በሕይወት፡ መፅሐፍ ስሙን፡ እጽፈዋለሁ፡ ስለ ፡ አንቺ፡ መብራት፡ ዘይት፡ ዕጣንም፡ ለቤተክርስቲያን፡ መብዓ፡ የሰጠ፡ እኔ ከፀሐይ፡ ከጨረቃ፡ ይልቅ፡ሰባት፡ እጅ፡ የሚያበራ መብራት፡ በመንግሥተ፡ ሰማያት፡ አበራለታለሁ፡፡ ንፁህ መዓዛ፡ ዕጣንም፡ የሰጠ፡ መዓዛ፡ ሽታውን፡ እንደ መላእክት፡ መዓዛ፡ አደርገዋለሁ፡፡

ሴት ፡ ወይንም፡ ወንድ፡ ልጁን፡ በአንቺ ስም፡ የሰየመውን፡ በምድራውያን፡ ሰዎች፡ እና በሰማያውያን፡ መላእክት፡ ዘንድ ፡ ከፍ፡ ያለ፡ ግርማ ሞገስ፡ ያገኛል፡፡ ይህ፡ መጽሐፍ፡ ባለበት፡ ቦታ፡ሁሉ፡ እስከ፡ ዘለዓለም ድረስ፡ ምሕረት፡ቸርነት፡ ተድላ፡ ደስታ፡ ጥጋብ በረከት፡ ይሁን፡፡ ስምሽ፡ በተጠራበት፡ ስእልሽም፡ ባለበት፡ መታሰቢያሽም፡ በተደረገበት፡ በስምሽም በሚጸለይበት፡ ቦታ፡ ሁሉ፡ እኩያን፡ አጋንንት አይቀርቡም፡ በረቂቅ፡ ሰውን፡ የሚያሰቃዩ፡ ጸሊማን ዛር፡ውላጆችም፡ ይርቃሉ፡፡ ይህን መጽሐፍ በክብር ይዞ ፡ ለሚጸልይ፡ የጨለማ ፡ ኃይል፡ አይጋርደውም ርኩሳን፡ መናፍስትም፡ የቀትር፡ አጋንንትም፡ ሊቀርቡት፡ አይችሉም፡፡

በሌሊት፡ በህልም የሚያስደነግጡ፡ በመዓልት፡ በእሾህ፡ መውጋት፡ ቢሆን በእንቅፋት፡ የሚመሰሉ፡ በምግብ ማሳነቅ፡ ወይም ፡ በውሃ ትንታ፡ የሚመሰሉ፡ በስካር እና ፡ በቁጣ፡ የሚመሰሉ፡ ልብን፡ በመፋቅ፡ በቃር የሚመሰሉ፡ በጥርስ፡ በሽታ፡ አፍን፡ በማምረር፡ በራስ ምታት፡ እና፡ በዓይን፡ ህመም፡ ወይም፡ በሆድ ቁርጠት፡ የሚመሰሉ፡ በንዳድ፡ (በወባ)፡ በማነቅ የሚመሰሉ፡ በባህር፡ እና ፡ በየብስ፡ በእንጨት፡ በድንጋይ፡ የሚመሰሉ፡ በእሳት፡ እና ፡ በዲን የሚመሰሉ፡ በፍቅር፡ እና ፡ በሰላም ወይም፡ በጠብ የሚመሰሉ፡ በአራዊት፡ እና፡ በአዕዋፋትም፡ የሚመሰሉ በፀሀይ፡ ሐሩር፡ ወይም፡ በቁርና፡ በአመዳይ፡ በውርጭ በነፋስ፡ ንውጽውጽታ፡ ኃይል፡ ወይም ፡ በውሻ፡ መንከስም የሚመስሉ፡ በእፍኝት፡ መንደፍም፡ ቢሆን፡ በእሳት ማቃጠል፡ የሚመሰሉ በሌሊት፡ ጨለማ ፡ በቀን ብርሃንም፡ የሚመሰሉ፡ እነዚህ፡ ሁሉ፡ አይቀርቡም ይህን፡ መፅሐፍ፡ በንጹህ፡ ህሊና፡ በቅን፡ ልቦና፡ የያዘ የቡዳ፡ ዓይን፡ አያስፈራውም፡

ይህ፡ መጽሐፍ በምትደገምበት፡ ቦታ፡ ሁሉ፡ ሰላቢዎች፡ ሟርተኞች መድኃኒተኞች፣ የሌሊትና፡ የቀን፡ የዱር ፡ አራዊቶች የሚታየውም፡ የማይታየውም፡ በረድ፡ ከብኩባ አንበጣም፡ ቢሆን፡ ሊቀርቡ፡ አይችሉም፡፡ ከብቶችም ቢታመሙ፡ ይህን፡ ጸሎት፡ ቢደግሙላቸው፡ ክፉ በሽታ፡ አይነካቸውም፡፡ ይህን፡ መጽሐፍ፡ በንጽህና የሚይዝ፡ ሁሉ፡ ከደዌው፡ አድነዋለሁ፡፡ ከሚያስጨንቅ ችግርም፡ እሠውረዋለሁ፡ ኃጥአትም፡ ቢኖርበትም ይሠረይታል፡ ደዌው፡ ለሞት፡ የሚያዘዝ፡ ቢሆን እኔ አስቀድሜ፡ መላእክተ፡ ብርሃን፡ እልክለታለሁ ነፍሱንም፡ በክብር፡ ተቀብለው፡ ወደ፡ እኔ ያመጧታል፡ ፡ ከሦስተኛው ፡ ሰማይም፡ በደረሰ፡ ጊዜ፡ መናፍስተ ርኩሳን፡ አይቃወሙትም፡ ጸዋጋን፡ አጋንንት፡ ከእርሱ ጋር፡ አይቆሙም፡ ሊቀርቡትም፡ አይችሉም፡፡

ዳግመኛም ፡ እኔ፡ በዚያን፡ አስፈሪ፡ በሆነ፡ ሰዓት፡ እረዳት፡ እሆነዋለሁ፡ እኔ፡ እና፡ የባሕይ፡ አባቴ፡ አብ፡ የባሕርይ፡ ሕይወቴ፡ የእውነት፡ መንፈስ፡ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ፡ ወደ፡ እርሱ፡ እንመጣለን፡፡ አስራ፡ ሁለቱም፡ ሊቃነ፡ መላእክትም፡ ከዝርግፍ፡ ወርቅ፡ ጋር የወርቅ፡ ጥናቸውን፡ ይዘው፡ ይመጣሉ፡፡ ቀስተ፡ ደመና በመሰለ፡ በናርዱ፡ ሽቱ፡ መብረቅም ፡ በመሰለ፡ የእሳት ሰረገላ ፡ ሆነን፡ ይህን፡ መጽሐፈ፡ ጸሎት፡ የያዘን፡ ሰው እንቀበለው፡ ዘንድ፡ እስከ፡ አምስተኛው፡ ሰማይ፡ ድረስ እንወርዳለን፡ በደረቴ፡ አቅፌ፡ ባህረ፡ እሳትን አሻግረዋለሁ፡፡ ወደ፡ መንበረ፡ መንግሥቴም፡ አቀርበዋለሁ፡፡ መንፈሳውያን፡ የመላዕክት፡ አለቆችም፡ በአዩት፡ ጊዜ ደስ፡ ይላቸዋል፡፡ ይህን ፡ ጸሎት፡ በንጽህና፡ እየፀለየ የያዘን፡ ሰው፡ እያሸበሸቡ፡ ይቀበሉታል፡፡ በቅዱስ ወንጌል፡ የተነገረውን፡ አልሰማሽምን፡ መቶ፡ በጎች ያሉት፡ ሰው፡ ከመቶው፡ አንዷ፡ ብትጠፋበት፡ ዘጠና ዘጠኙን፡ በዱር፡ ትቶ፡ የጣፋችውን፡ በግ፡ ሊፈልግ እንደሄደ፡ በአገኛትም፡ ጊዜ፡ በትከሻው፡ ተሸክሞ ካልጠፉት፡ ከዘጠና፡ ዘጠኙ፡ በጎች፡ ይልቅ፡ ጠፍታ በተገኘችው፡ በግ፡ ደስ፡ እንደሚለው፡ ባልንጀሮቹን እና ጎረቤቶቹን፡ ጠርቶ፡ የጠፋችው፡ በጌ፡ ተገኝታለች እና፡ ደስ፡ ይበላችሁ፡ ይላቸዋል፡፡

እውነት፡ እውነት፡ እላችኋለሁ፡ ንስሐ፡ ከማይገቡ ፃድቃን፡ ይልቅ፡ ንሰሐ፡ በሚገባ፡ አንድ፡ ኃጥአ፡ ሰው በሰማይ፡ ታላቅ፡ ደስታ፡ እንደሚደረግ፡፡ ሁለተኛም ይኸን፡ መጽሐፍ፡ የሚደግም፡ እና ፡ በሚይዝ፡ ሰው ሰማያውያን፡ መላእክት፡ ደስ፡ ይሰኛሉ፡፡ ከዚህ ከሚያልፈው፡ ዓለም፡ ወደ፡ ማያልፈው፡ ዓለም፡ ነፈሱ ከሥጋው፡ ተለይታ፡ በምትወጣበት፡ ሰዓት፡ ደብረ መቅደሴን፡ አወርሰዋለሁ፡፡ ከባሕርይ፡ አባቴ፡ ከአብ ከባሕርይ ፡ ሕይወቴ፡ ከመንፈስ፡ ቅዱስም፡ ዘንድ አቀርበዋለሁ፡፡ ይህ፡ መጽሐፍ፡ ካለበት፡ ቦታ፡ ይቅርታ ቸርነት፡ ምህረት፡ ጥጋብ፡ ተድላ፡ ደስታ፡ እስከ ዘለዓለም፡ ድረስ፡ ይሆናል፡፡

በእውነት፡ ይህ፡ ጸሎት በተደገመበት፡ እና፡ በተነበበበት፡ ቦታ፡ ንዳድ እንቅጥቅጥ፡ በያይነቱ፡ በሽታ፡ ሁሉ፡ አይቀርቡም፡፡ ይህን፡ የጸሎት፡ መጽሐፍ፡ በንጹህ፡ የያዘ፡ እርሱን ልጆቹን፡ ገንዘቡን፡ ሀብቱን፡ እባርካለሁ፡፡ በዚህ መጽሐፍ፡ አምኖ፡ በንጹህ፡ ልቦና፡ በቀና፡ ሃይማኖት ያለጥርጥር፡ በማየ፡ ጸሎቱ፡ የተጠመቀ፡ የጠጣ፡ በቤቱ (በስራው፡ ቦታ) ፡ የረጨ፡ እኔ፡ ጸሎቱን፡ እሰማዋለሁ እንደ፡ ልቡም፡ ፈቃድ፡ እፈጽምለታለሁ፡፡ ሚካኤልና ገብርኤልም፡ ፈቃዱን፡ ይፈጽሙለት፡ ዘንድ፡ ዘወትር፡ ወደ ፡ እርሱ፡ ይመጣሉ፡፡ ይህን፡ መጽሐፍ በንጽህና የያዘ፡ ሁሉ፡ የሰራዊተ፡ መላእክት፡ አለቆች፡ ዘወትር እየመጡ፡ ይጎበኙታል፡፡ እናቴ ማርያም፡ ሆይ፡ በሰማይና ፡ በምድር፡ ይህን፡ሁሉ፡ ቃል፡ ኪዳን (አስራት) ሰጠሁሽ፡፡

ቡርክት፡ መርገመ፡ ሥጋ፡ መርገመ፡ ነፍስ የሌለባት፡ እመቤታችንም፡- ልጄ፡ ወዳጄ፡ ሆይ ይህ፡ የምትለኝ፡ ሁሉ፡ እውነት፡ ነውን፡ አለችው፡፡ ጌታም፡ መለሰ፡ እንዲህም፡ አላት፡- እናቴ፡ ማርያም፡ ሆይ በእግዚአብሔር፡ አባቴ፡ በክርስቶስ፡ ስሜ፡ በዕውነት መንፈስ፡ በጸቅሊጦስ፡ እውነት እንደሆነ፡ ቃል ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡ አላት፡፡ መልአከ ምክሬ፡ በሆነው በሚካኤል፣ የመወለዴን፡ ዜና በአበሰረሽ፡ በገብርኤል ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡ አላት ክንፋቸው፡ ስድስት በሆኑ፡ ምሉዓነ፡ አዕይንት፡ በሆኑ መንበሬን በሚሸከሙ፡ ዐራቱ፡ እንስሳት፡ (ኪሩቤል) ቃል፡ ኪዳን ገባሁልሽ፡፡ አኗኗሬን፡ በአንድነት፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ፡ እያሉ፡ እያመሰገኑ፡ መንበሬን፡ በሚያጥኑ፡ በሃያ ዐራቱ፡ ካህናተ፡ ሰማይ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡ እልፍ፡ ሆነው ፡ በቀኝ ፡ እልፍ፡ ሆነው፡ በግራ፡ እልፍ ሆነው ፡ በኋላ፡ እልፍ፡ ሆነው በፊቴ፡ በሚቆሙ፡ መላእክት፡ ቃል፡
ኪዳን ገባሁልሽ፡፡ በእልፍ፡ አእላፋት፡ ብዙ፡ የብዙ፡ ብዙ፡ በሚሆኑ ትጉሃን፡ መላእክት፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ የፍጥረት ተቀዳሚ፡ በሆነ፡ በአዳምና፡ በልጆቹም፡ በአቤልና፡ በሴት፡ በቃይናን በመላልኤል፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡

በኄኖክና፡ በኄኖስ፡ በያሬድ፡ እና፡ በማቱሳላም፡ ቃል ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ ዳግመኛም፡ ምድርን፡ በንፍር፡ ውሃ፡ እንዳላጠፋት ኪዳነ፡ ሰማይ፡ ወምድር፡ በሰጠሁት በባሪያዬ፡ በኖህ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ የትዕዛዜ፡ ጠባቂ፡ በኩር፡ በሆነ፡ በሴም፡ ምሳሌየ፡ በሆነ፡ በመልከ፡ ጼዴቅ ካህን፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ ስለ፡ ወዳጄ፡ ስለ አብርሃም ስለ፡ ባለሟሌ፡ ስለ፡ ይስሐቅ፡ ዘሩን፡ በአስራ፡ ሁለቱ ነገድ፡ ከፍዬ ፡ ስለ አከበርኩት፡ ስለ፡ ያዕቆብ፡ ቃል፡ ኪዳን ገባሁልሽ፡፡ ንጹሃን፡ ቅዱሳን ፡ በሆኑ፡ በቀደሙ፡ አባቶች በይሁዳ፡ እና፡ በፋሬስ፡ በዮሴፍ፡ እና፡ ብንያም፡ በሌዊ እና፡ በይሳኮር፡ በአስራ፡ ሁለቱ፡ ነገደ፡ እስራኤል፡ ቁጥር፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡
ጸሐፍተ፡ ትዕዛዝ፡በሆኑ፡ በሄኖክ፡ እና፡ በኤልያስ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ ዘጠኝ፡ ወር ከአምስት፡ ቀን በተቀመጥኩባት ፡ ንጽህት፡ በሆነች ማኀፀንሽ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ ጣፋጭቱ፡ ከመዓር፡ ከስኳር፡ የሚጥመው፡ ንጹሕነቱ፡ ከኤዶም ምንጭ፡ ውሃ፡ ንጣቱ፡ ከበረዶ፡ እና፡ ከወተት የበለጠውን፡ ወተት፡ መግበው፡ ባሳደጉኝ፡ ጡቶችሽ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ ትእዛዜን፡ እና፡ ሕጌን ባስተማሩ፡ አስራ፡ አምስቱ፡ ነብያት ሄሮድስ ባስገደላቸው፡ አስራ፡ አራት፡ እልፍ፡ የቤተልሔም ሕፃናት፡ ቃል ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ የወንጌልን፡ መንግስት፡ ለዓለም፡ በሰበኩ፡ ሐዋርያት ስለ፡ እኔ፡ ነፍሳቸውን፡ ለሞት፡ አሳልፈው፡ ስለ፡ ሰጡ ሰባ፡ ሁለቱ፡ አርድእት፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡

ዙፋኔ፡ በተዘጋጀባት፡ ሉዓላዊት፡ ሰማይ፡ የእግሬ መረገጫ ፡ በሆነች፡ ታህታዊት፡ ምድር፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ ነደ፡ እሳት፡ በሆነ፡ የእሳት፡ መጋረጃዬ ፍጹም፡ ማደሪያዬ ፡ በሆነ በአርያም ፡ ሰማይ፡ ቃል ፡ ቃል ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ በተሰቀልኩበት፡ ዕፀ፡ መስቀል እጅና እግሬ፡ በተቸነከረበት ቅኖት፡ (ችንካር)፡ በጦር በተወጋው፡ ጎኔ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ በዕለተ ዓርብ፡ በፈሰሰው፡ ደሜ፡ በሕመሜ፡ እና፡ ሞቴ፡ ሦስት፡ መዓልትና፡ ሦስት፡ ሌሊትም፡ በከርሰ፡ መቃብር፡ ባደርኩበት፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡ ፡ ከመቃብር፡ ወጥቼ፡ አዳምን፡ ከነ፡ ልጆቹ፡ ከሲኦል ለማውጣት፡ ወደ፡ ሲኦል፡ በመውረዴ፡ በሦስተኛው፡ ቀን፡ ከሙታን፡ ተለይቼ፡ ሙስናን፡ መቃብርን፡ አጥፍቼ በመነሳቴ፡ በዐርባኛው፡ ቀን፡ ወደ፡ ሰማይ፡ በማረጌ ዳግመኛው፡ ዓለምን፡ ለማሳለፍ፡ በታላቅ ፡ ምስጋና በምመጣበት፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡

ክቡር ፡ በሆነ ደሜ፡ ቅዱስ፡ በሆነ፡ ስጋዬም፡ ቃል፡ ኪዳን ገባሁልሽ፡፡ ሰማያዊት ፡ በሆነች፡ በኢየሩሳሌም፡ ሀገሬ በክቡር፡ በምስጋና፡ በተጌጠች፡ በጽዮን፡ ቃል፡ ኪዳን ገባሁልሽ፡፡ የሙሽራ፡ አምሳል፡ በሆነች፡ በቅድስት፡ ቤተ፡ ክርስትያን፡ ከዕለታት፡ መርጬ፡ የተወለድኩባት የተጠመቅኩባት፡ ለሰው፡ ልጅ፡ ድኀንነትን፡ የምታስገኝ ትንሳኤዬንም፡ በገለጥኩባት ሰንበተ፡ ክርስትያን፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ በደብረ ዘይት፡ በተቀደሰውም፡ በጽዮን፡ በደብረ፡ መንግስቴ በመቃብሬ፡ በጎልጎታ ንጹህ፡ ብሩሕ፡ በሆነ፡ ደም፡ ግባትሽ፡ ንጹሐት፡ ክቡራት፡ በሆኑ፡ ልብሾችሽ፡ በዚህ ሁሉ፡ ቃል፡ ኪዳን፡ ገባሁልሽ፡፡ አናቴ፡ ድንግል ማርያም፡ ሆይ፡ የሰጠሁሽን፡ ቃል፡ ኪዳን፡ እንዳልነሳሽ እማንዬ፡ ብዬ፡ በራሴ፡ ማልሁልሽ፡፡ በአንቺ፡ ስምም የሚቀደስበትን፡ ቦታ፡ እኔ፡ እባርካለሁ፡፡ እንደ፡ አቤልም መሥዋዕት፡ እቀበለዋለሁ፡፡

መርገመ፡ ሥጋ፡ መርገመ ነፍስ፡ የሌለባት እመቤታችንም፡ መለሰች፡ እንዲህም አለች፡- እንተ ብሩክ ፡ ነህ፡ ሰማያዊ፡ አባትህም፡ ብሩክ ፡ ነው፣ የባሕርይ፡ ሕይወትህ፡ መንፈስ፡ ቅዱስም የተባረከ፡ ነው፡፡ ይህን፡ ሁሉ፡ በቸርነትህ፡ ስለሰጠኸኝ፡ አቤቱ፡ ለአንተ፡ ምስጋና ፡ ይገባል፣ ለቸር አባትህም፡ ምስጋና፡ ይገባል፡ ማኀየዊ፡ ለሚሆን፡ ለመንፈስ፡ ቅዱስም፡ ምስጋና፡ ይገባል፡ ዛሬም፡ ዘወትርም፡ ለዘለዓለሙ፡ አሜን፡፡

ጌታችን፡ ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ለእናቱ፡ ይህን፡ ነግሯት፡ ከፈጸመ፡ በኋላ ሰላምታ፡ ሰጥቷት፡ በታላቅ፡ ምስጋና፡ ወደ፡ ሠማይ፡ ዐረገ፡ እርሷም፡ እግዚአብሔርን፡ እያመሠገነች፡ ወደ ቤቷ፡ ተመለሠች፡ እንዲህ፡ እያለች፡-
አቤቱ፡ አንተ የተመሠገንህ፡ ነህ፡ ስምህም፡ የተመሠገነ፡ ነው፣ የመንግሥትህም፡ ስም፡ ይባረክ፡ ከመንፈስ፡ ቅዱስ ጋር፡ ክብር፡ ጽንዕ፡ ለአንተ፡ ይገባል፡ ዛሬም፡ ዘወትርም፡ ለዘለዓለሙ፡ አሜን፡፡
+++

እመቤቴ፡ ማርያም ሆይ፡ በዚህ፡ ቃል፡ ኪዳንሽ፡ ከተንኮለኞች፡ ሠዎች፡ ከጸዋጋን፡ አጋንንት፣ መከራና፡ከመከራ፡ ሥጋ፡ ከመከራ፡ ነፍስ፡ ከዕለት፡ ዕኪት፡ ዘመን፡ መንሱት፡ እኛን፡ ደካሞች አገልጋዮችሽን አድኚን፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር!

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

23/06/2025

ሰኔ 17

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ 2 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share