አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ 2

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ 2 በቅዱስ ሚካኤል ስም በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።
(2)

ነሐሴ ሰባት በዚች አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ፅንስቷ ነው፣ የሐዋርያት አለቃ የከበረ ሐዋርያው ጴጥሮስ በዓል ነው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ አረፈ፣ የ...
13/08/2026

ነሐሴ ሰባት በዚች አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ፅንስቷ ነው፣ የሐዋርያት አለቃ የከበረ ሐዋርያው ጴጥሮስ በዓል ነው፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ አረፈ፣ የራኄል ልጅ ቅዱስ ዮሴፍ ተወለደ።

በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም

ነሐሴ ሰባት በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ከበረና ከፍ ከፍ ወዳለ ጻድቅ ኢያቄም ላከው አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ፅንስቷንና ልደቷን በእርሷም ለዓለሙ ሁሉ ድኅነትና ተድላ ደስታ እንደሚሆን ነገረው።

ይህ ጻድቅም ሰው ኢያቄምና የከበረች ሚስቱ ሐና ልጅ ሳይወልዱ ሸመገሉ የከበረች ሐና መካን ሁናለችና ስለዚህም እጅግ ያዝኑ ነበር የእስራኤል ልጆች ልጅ ያልወለደውን ከእግዚአብሔር በረከትን ያጣ ነው እያሉ ያቃልሉት ነበርና። እነርሱም ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ፈጽሞ ይለምኑ ነበር። ከዚህም በኋላ ወንድ ልጅን ወይም ሴት ልጅን ቢወልዱ ለእግዚአብሔር ቤት አገልጋይ ሊያደርጉ ስለትን ተሳሉ።

የከበረ ኢያቄምም በተራራ ላይ ሳለ ሲጸልይና ሲማልድ እነሆ በላዩ እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎት አሸለበ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የተላከ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተገለጸለት እንዲህም አለው ሚስትህ ሐና ትፀንሳለች ዓለሙ ሁሉ ደስ የሚሰኝባትን የብዙዎችም ዐይነ ልቡ ናቸው በእርሷ የሚበራላችውን በእርሷም ድኅነት የሚሆንባትን ሴት ልጅን ትወልድልሃለች።

በነቃ ጊዜም ወደ ቤቱ ሒዶ ለሚስቱ ለቅድስት ሐና ነገራት ራእይዋን እውነት እንደሆነች አመኑዋት ከዚህም በኋላ ነሐሴ ሰባት በዚች ቀን የከበረች ሐና ፀነሰች ለዓለም ሁሉ መመኪያ የሆነች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የአምላክ እናት እመቤታችንን ማርያምን ወለደቻት።

ቅዱስ ጴጥሮስ ሐዋርያ

በዚህችም ቀን የሐዋርያት አለቃ የከበረ ሐዋርያ ጴጥሮስ በዓል ነው። በዚች ቀን ጌታችን የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ እርሱ እንደሆነ በሐዋርያት መካከል ታምኗልና።

በከበረ ወንጌል እንደተባለ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ብሎ ጠየቃቸው እርሱ ልብን ኲላሊትን የሚመረምር ሰዎች የሚያስቡትን ሁሉ የሚያውቅ ሲሆን።

ያን ጊዜ ሐዋርያት ተጠራጣሪዎች ስለነበሩ ስለዚህ ያሰቡትን በልባቸው ያለውን እንዲናገሩ ከከተማ ውጭ አወጣቸው። ከእርሳቸውም ኤልያስ እንደሆነ የሚአስቡ አሉ ወይም ከቀደሙት ነቢያት አንዱ እንደሆነ የሚሉም ነበሩ። ጴጥሮስም በእነርሱ ላይ ተቆጥቶ ለምን እንዲህ ታስባላችሁ እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነው እንጂ አላቸው።

ስለዚህም የጴጥሮስን ሃይማኖት በመካከላቸው ይገልጥ ዘንድና ግልጥ ሊያደርግ ወደ ውጭ አወጣቸው። እንዲሁም በጠየቃቸው ጊዜ ኤልያስ እንደሆንክ ወይም ከቀደሙት ነቢያት አንዱ እንደሆንክ ሰዎች ይናገራሉ በማለት እነርሱ የልባቸውን ተናገሩት። ጴጥሮስ ግን አንተ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነህ ብሎ በእውነት ምስክርን ሆነ።

ስለዚህም ጌታችን አመሰገነው የመንግሥተ ሰማያትንም ቊልፍ ሰጠው ። ከዚያች ቀን ወዲህ የሐዋርያት ሁሉ አለቃ ሆነ በእርሱም የሊቃነ ጳጳሳት የኤጲስቆጶሳት የቀሳውስትና የዲያቆናት ሹመት ተሰጠ። የቤተ ክርስቲያንም መሠረት ተባለ።

አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ዻዻሳት

በዚህችም ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ ስድስተኛ የሆነ የከበረ አባት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ጢሞቴዎስ አረፈ። ይህንንም ቅዱስ በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ይሆን ዘንድ የክብር ባለቤት ጌታችን መርጦት ተጋዳይ የነበረ አባ ዲዮስቆሮስ በደሴተ ጋግራ ከአረፈ በኋላ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ።

ይህም አባት ጢሞቴዎስ ብዙ መከራ ደርሶበታል። ንጉሥ መርቅያን ለእስክንድርያ አገር ሌላ መናፍቅ ሊቀ ጳጳሳት ሹሞ አባት ጢሞቴዎስን አስቀድሞ አባ ዲዮስቆሮስ ተሰዶባት ወደ ነበረች ደሴተ ጋግራ አጋዘው። መርቅያንም ከሞተ በኋላ የእስክንድርያ ሰዎች ተነሥተው መርቅያን የሾመውን ሊቀ ጳጳሳት ገደሉት አባት ዲዮስቆሮስ እንዳዘዘ አባ ጢሞቴዎስን መልሰው ሾሙት።

ከዚህም በኋላ የመርቅያን ልጅ ልዮን ነገሠ ያን ጊዜ አባ ጢሞቴዎስን ሁለተኛ ወደ ደሴተ ጋግራ አጋዘው በዚያም ዐሥር ዓመት ኖረ ልዮን እስከ ሞተ ድረስ ከእርሱም ኋላ ዘይኑን ነገሠ። ያን ጊዜም አባ ጢሞቴዎስን ወደ መንበረ ሢመቱ በታላቅ ክብር መለሰው ሕዝቡንም እያስተማራቸውና እየመከራቸው በቀናች ሃይማኖትም እያጸናቸው ኖረ።

በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበርም ሃያ ሁለት ዓመት ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ

በዚህችም ቀን የራኄል ልጅ ዮሴፍ ተወለደ።

(ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ 7 ና ከገድላት አንደበት)

🗓 የነሐሴ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.በዓለ ጽንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱስ ገብርኤል መበሥር
4.ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
5.አፄ ናዖድ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮጵያ)
6.ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ (ወልደ ያዕቆብ-ልደቱ)
7.አባ ጢሞቴዎስ ሊቀ ጳጳሳት

🗓ወርሐዊ በዓላት

1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
5.አባ ባውላ ገዳማዊ
6.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
7.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)

የነሐሴ 7 ቀን የእለቱ ግጻዌ

መልእታት
👇

ዕብራ 9÷1-11

1ጴጥ 2 ÷6-18

ሐዋርያት 10፥ 1-30

ምስባክ 👇

"ብጹዕ ብእሲ ዘእንተ ገሠጽኮ እግዚኦ። ወዘመርሀኮ ሕገከ። ከመ ይትገኅሥ እመዋዕለ እኩያት። መዝ.93÷12-13

ትርጉም➣"ለኃጢአተኛ ጕድጓድ እስኪቈፈር ድረስ ከክፉዎች ዘመናት ይወገድ ዘንድ፥ አቤቱ፥ አንተ የገሠጽኸው ሕግህንም ያስተማርኸው ሰው ምስጉን ነው።" መዝ.93÷12-13

የእለቱ ወንጌል📖
👇
ማቴዎስ 16÷13-24

የሚቀደሰው ቅዳሴ
👇
ቅዳሴ ዘእግዝእትነ ነው።

የነሐሴ 7 ቀን ወንጌል ሙሉ ንባብ📖

ማቴዎስ 16

¹³ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።
¹⁴ እነርሱም፦ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት።
¹⁵ እርሱም፦ እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
¹⁶ ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፦ አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ።
¹⁷ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ።
¹⁸ እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።
¹⁹ የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል።
²⁰ ያን ጊዜም እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ለማንም እንዳይነግሩ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው።
²¹ ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ይሄድ ዘንድ ከሽማግሎችና ከካህናት አለቆች ከጻፎችም ብዙ መከራ ይቀበልና ይገደል ዘንድ በሦስተኛውም ቀን ይነሣ ዘንድ እንዲገባው ለደቀ መዛሙርቱ ይገልጥላቸው ጀመር።
²² ጴጥሮስም ወደ እርሱ ወስዶ፦ አይሁንብህ ጌታ ሆይ፤ ይህ ከቶ አይደርስብህም ብሎ ሊገሥጸው ጀመረ።
²³ እርሱ ግን ዘወር ብሎ ጴጥሮስን፦ ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል አለው።

ነሐሴ ስድስት በየዓመቱ ነሐሴ ሁለት ቀን ሶሀባ በሚባለው ቦታ ቆመው በጸለዩበት ወንዝ ላይ ዓሣ ከሰማይ የሚዘንብላቸው መናኔ መንግሥት አቡነ ኢዮስያስ ዕረፍታቸው ነው። ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ...
11/08/2026

ነሐሴ ስድስት በየዓመቱ ነሐሴ ሁለት ቀን ሶሀባ በሚባለው ቦታ ቆመው በጸለዩበት ወንዝ ላይ ዓሣ ከሰማይ የሚዘንብላቸው መናኔ መንግሥት አቡነ ኢዮስያስ ዕረፍታቸው ነው። ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ጌታችን ቅድስት ትንሣኤውን ከሁሉም አስቀድሞ ከሐዋርያቶቹም እንኳን በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ የገለጠላት ቅድስት ማርያም መግደላዊት ዕረፍቷ ነው፡፡ የቂሣርያዋ ሰማዕት ቅድስት ኢየሉጣ የሰማዕትነቷ ፍጻሜ ሆነ፡፡ የታላቁ አባት የአቡነ ሲኖዳ ደቀ መዝሙር የሆነውና ገድሉንም የጻፈ አባ ዊፃ ዕረፍቱ መሆኑን ስንክሳሩ በስም ይጠቅሰዋል።

ቅድስት ማርያም መግደላዊት

ነሐሴ ስድስት በዚህች ቀን ጌታችን ሰባት አጋንንትን ከእርሷ ያወጣላት የከበረች መግደላዊት ማርያም አረፈች። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስን ተከትላ ያገለገለችው በመከራውም ጊዜ ከባልንጀሮቿ ጋራ የነበረች እስከ ቀበሩትም ድረስ ያልተለየች እናት ነች።

በእሑድ ሰንበትም ገና ጨለማ ሳለ በማለዳ ማርያም ወደ መቃብር ገሥግሣ ሔደች ደንጊያውንም ከመቃብሩ አፍ ተገለባብጦ መልአክም በላዩ ተቀምጦ አየችው ከእርሷም ጋራ ጓደኛዋ ማርያም አለች። መልአኩም እናንተስ አትፍሩ ጌታ ኢየሱስን እንድትሹት አውቃለሁና ግን ከዚህ የለም እነሣለሁ እንዳለ ተነሥቷል አላቸው ።

ለእርሷም ዳግመኛ ተገልጾላት ሒደሽ ለወንድሞቼ እኔ ወደ አባቴ ወደ አባቴታችሁ ወደ አምላኬ ወደ አምላካችሁ እንደማርግ ንገሪያቸው አላት። ወደ ሐዋርያትም መጥታ የመድኃኒታችንን መነሣቱን እንዳየችውና ንገሪ እንዳላትም አበሠረቻቸው።

ከዕርገቱም በኋላ ሐዋርያትን እያገለገለቻቸው ኖረች። በኃምሳኛው ቀንም መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮቼ ላይ ቅዱስ መንፈሴን አሳድራለሁ አለ ብሎ ኢዩኤል ትንቢት እንደ ተናገረ ያንን አጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ከሐዋርያት ጋር ተቀብላለች።

ከዚህም በኋላ ከሐዋርያት ጋራ ወንጌልን ሰበከች ብዙዎች ሴቶችንም የክብር ባለቤት ወደሆነ ወደጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት መልሳ አስገባቻቸው። ሴቶችን ስለ ማስተማርም ሐዋርያት ዲያቆናዊት አድርገው ሾሟት ከአይሁድም በመገረፍ በመጐሳቈል ብዙ መከራ ደረሰባት። ተጋድሎዋንም ፈጽማ በሰላም በፍቅር አረፈች።

ረድኤት በረከቷ ይደርብን፤ በጸሎቷ ይማረን

አርኬ
ሰላም ለመግደላዊት ማርያም ስማ። ለኢየሱስ ዘርእየቶ እምሐዋርያት ቀዲማ ወለአንስት ሰላም ዘተሳተፋ ድካማ። እንዘ ይትራወጻ ኀበ መቃብሩ ለፌማ። እንበለ ያፍርሆን ዘሌሊት ግርማ።

ቅድስት ኢየሉጣ (ዘቂሣርያ)

በቀድሞው የግሪክ ግዛት (ቂሣርያ ውስጥ) በዘመነ ሰማዕታት አካባቢ የነበረችው ቅድስት ኢየሉጣ ክርስትናን የወረሰችው ከወላጆቿ ነው፤ ገና ወጣት እያለች ወላጆቿ በማረፋቸው የሃብታቸው ወራሽ ሆነች፤ ነገር ግን አንድ ክፉ ሰው መጥቶ ሃብቷን ነጠቃት፡፡

በዚህ አዝና ለዳኛ ለመክሰስ ወደ ፍርድ ቤት ብትሄድ የጠበቃት ግን ያልጠበቀችው ነገር ነው፤ የተገፋችው እርሷ ሆና ሳለ ጭራሽ ተከሳሽም እርሷው ሆነች፤ ገፊው ደግሞ ከሳሹዋ ሆነ፡፡ የክሱም መነሻ ‹‹ክርስቲያን ነሽ›› የሚል ነበር፤ በወቅቱ በመኮንንቱ ፊት ክርስትናዋን ብትክድ በቀጥታ ሃብቷን ማግኘት ትችል ነበር እርሷ ግን ለአፍታ አሰበች፡፡

‹‹እንዴት ዘላለማዊ ሃብቴን (ሃይማኖቴን) በኃላፊው ንብረት እለውጣለሁ›› ብላ ሁሉም እየሰሙ ጮክ ብላ ‹‹ክርስቲያን ነኝ›› አለች፤ ወዲያውም ሞት ተፈርዶባት በዚህች ዕለት በሰማዕትነት ተገደለች፡፡

ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ ስለ ሰማዕታት በጻፈው ድርሳን ላይ በስፋት አመስግኗታል፤ ለሴቶችም ታላቅ ምሳሌ መሆኗን መስክሮላታል፡፡

የቅድስት ኢየሉጣ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፤ በጸሎቷ ይማረን

አርኬ
ሰላም ለኢየሉጣ እንበይነ ምግባራ ሠናይ። በውስተ እቶን ዘእብእዋ በውዴተ ብእሲ እኩይ። እንዘ ኢሀሎ ላዕሌሃ አሠረ ዋዕይ። ወጽአት እምእሳት ከመ ዘወጽአ እማይ። አምሳለ ፍቱን ወርቅ ወብሩር ጽሩይ።

አቡነ ኢዮስያስ (መናኔ መንግሥት)

አቡነ ኢዮስያስ ትውልዳቸው ሸዋ ሲሆን የንጉሥ ዓምደ ጽዮን ልጅ ናቸው፤ ጥር 6 ቀን ሲወለዱ ቅዱሳን መላእክት ከበዋቸው ታይተዋል፤ የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በዓለም ነግሠው መኖርን ንቀው በመመነን በመጀመሪያ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ገቡ፡፡

አቡነ ኢዮስያስ በሐይቅ ገዳም ለ14 ዓመታት በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፤ በዚያም ብሉይንና ሐዲስን፣ መጽሐፈ መነኮሳትንና መጽሐፈ ሊቃውንትን አጠናቀው ተምረዋል፤ በኋላም በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ ትግራይ ደብረ በንኮል ገዳም ሄዱ፡፡

በደብረ በንኮልም በታላቅ ተጋድሎ ኖረው በታላቁ አባት በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ መነኮሱ፤ ቆብ የተቀበሉት ግን ከአቡነ ተክለሃይማኖት ነው፡፡

አቡነ መድኃኒነ እግዚእም ሰባት ዓመት ከእሳቸው ጋር ካቆዩአቸው በኋላ አቡነ ኢዮስያስን ወንጌልን ዞረው እንዲሰብኩና ገዳም እንዲገድሙ በማዘዝ መርቀው ሸኝተዋቸዋል፡፡

አቡነ ኢዮስያስም ወደ አዱዋ አውራጃ ዛሬ በስማቸው ወደተጠራው ገዳም ሄደው በቦታው ላይ በተጋድሎ ኖሩ፤ ገዳሙንም ከገደሙት በኋላ በርካታ መነኮሳትን አፍርተዋል፡፡

ጻድቁ ያፈለቁት ጠበል በፈዋሽነቱ የታወቀ ነው፤ በየዓመቱ በዕረፍታቸው ዕለት ነሐሴ 6 ቀን ሶሀባ በሚባለው ቦታ ቆመው በጸለዩበት ወንዝ ላይ ዓሣ ከሰማይ ይዘንባል፡፡

ይህ አሁንም ድረስ በየዓመቱ ነሐሴ 6 ቀን በግልጽ እየታየ ይገኛል፤ አቡነ ኢዮስያስን ከሃዲያን የሆኑ አረማውያን ቢያስቸግሯቸው ጻድቁም በጸሎት ቢያመለክቱ ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ነጭ የንብ መንጋ መጥቶ አረማውያኑን አንጥፍቶላቸዋል፡፡

ጻድቁ በጸሎታቸው አራት ሙታንን በአንድ ጊዜ ከሞት ያስነሡ ታላቅ አባት ናቸው፤ በገዳማቸው ውስጥ በበዓላቸው ቀን ገድላቸው ሲነበብ አጋንንት ከሰው ልቡና እንደ ትቢያ በነው ይጠፋሉ፡፡

ጻድቁን እንደ ረድእ ሆኖ የሚያገለግላቸው አንበሳ ነበራቸው፤ ወደ ገዳማቸው መጥቶ መካነ ዐፅማቸውን የተሳለመውን እስከ 14 ትውልድ ድረስ እንደሚምርላቸው ጌታችን ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፤ ልጁን በስማቸው የተሰመ ቢኖር የሰይጣንን ፊት ፈጽሞ እንደማያይ ገድላቸው ይናገራል፡፡

በረከታቸው ረድኤታቸው ይደርብን፤ በጸሎቱ ይማረን

(ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ 6 ና ከገድላትአንደበት )

🗓 የነሐሴ 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅድስት ማርያም መግደላዊት (ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት)
2.ቅድስት ኢየሉጣ ሰማዕት (ዘቂሣርያ)
3.አባ ዊጻ (የታላቁ ሲኖዳ ደቀ መዝሙር)

🗓ወርሐዊ በዓላት

1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

የነሐሴ 6 ቀን የእለቱ ግጻዌ

መልእታት
👇

1ቆሮ 3÷10-22

1ጴጥ 3 ÷1-7

ሐዋርያት 16፥ 13-19

ምስባክ 👇

"ወይሰግዱ ሎቱ አዋልደ ጢሮስ በአምኃ። ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኵሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር። ኵሉ ክብራ ለወለተ ንጉሠ ሐሴቦን። መዝ.44÷12-13

ትርጉም➣"የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ። ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብርዋ ነው፤ ልብስዋ የወርቅ መጐናጸፊያ ነው"። መዝ.44÷12-13

የእለቱ ወንጌል📖
👇
ማርቆስ 16÷9-19

የሚቀደሰው ቅዳሴ
👇
ቅዳሴ ዘእግዝእትነ ነው።

የነሐሴ 6 ቀን ወንጌል ሙሉ ንባብ📖

ማርቆስ 16

⁹ ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ማልዶ በተነሣ ጊዜ፥ አስቀድሞ ሰባት አጋንንት ላወጣላት ለመግደላዊት ማርያም ታየ።
¹⁰ እርስዋ ሄዳ ከእርሱ ጋር ሆነው ለነበሩት ሲያዝኑና ሲያለቅሱ ሳሉ አወራችላቸው፤
¹¹ እነርሱም ሕያው እንደ ሆነ ለእርስዋም እንደ ታያት ሲሰሙ አላመኑም።
¹² ከዚህም በኋላ ከእነርሱ ለሁለቱ ወደ ባላገር ሲሄዱ በመንገድ በሌላ መልክ ተገለጠ፤
¹³ እነርሱም ሄደው ለሌሎቹ አወሩ፤ እነዚያንም ደግሞ አላመኑአቸውም።
¹⁴ ኋላም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ተገለጠ፥ ተነሥቶም ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ።
¹⁵ እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።
¹⁶ ያመነ የተጠመቀም ይድናል፥ ያላመነ ግን ይፈረድበታል።
¹⁷ ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፤ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፤ እባቦችን ይይዛሉ፥
¹⁸ የሚገድልም ነገር ቢጠጡ አይጎዳቸውም፤ እጃቸውን በድውዮች ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይድናሉ።
¹⁹ ጌታ ኢየሱስም ከእነርሱ ጋር ከተናገረ በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ በእግዚአብሔርም ቀኝ ተቀመጠ።

ነሐሴ አምስት እንደ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በጥላቸው ድውያንን ይፈውሱ የነበሩት የደብረ ቢዘኑን አቡነ ፊሊጶስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት በዘመኑ ሁሉ በጥርሱ ስቆ በከንፈሩም ...
10/08/2026

ነሐሴ አምስት እንደ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በጥላቸው ድውያንን ይፈውሱ የነበሩት የደብረ ቢዘኑን አቡነ ፊሊጶስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት በዘመኑ ሁሉ በጥርሱ ስቆ በከንፈሩም አልባሌ ነገርን ተናግሮ የማያውቀውና የክርስቶስን ሕማም እያሰበ ዕንባውን ያለማቋረጥ ሲያፈስ የኖረው አባ አብርሃም ዕረፍቱ ነው፡፡ ወታደሩ ቅዱስ ዮሐንስ ዐረፈ።

አባ አብርሃም

ወላጆቹ ባለጸጎች የነበሩ ሲሆኑ በተግሣትና በፈሪሃ እግዚአብሔር አሳደጓቸው፤ ካደጉም በኋላ ያለ ፈቃዳቸው አጋቡአቸው፤ ፈቃደ እግዚአብሔርም አነሳስቶአቸው ከጫጉላ ቤት በ7ኛው ቀን ወጥተው ሲሄዱ ብርሃን እየመራቸው አንድ ባዶ ቤት አደረሳቸው፤ እሷንም በዓት አድርገው ተቀመጡባት፡፡

ከ10 ዓመት በኋላ ወላጆቻቸው እጅግ ብዙ ሀብት ትተውላቸው ሞቱ፤ እርሳቸው ግን ንብረቱን በሙሉ ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች ሰጥተው አንድ ሰሌን ብቻ ላራሳቸው ገዙ፡፡

በታላቅ ተጋድሎም ሆነው 10 ዓመት ተቀመጡ፤ ጳጳሱም የአባ አብርሃምን ጸጋ ተጋድሎ አይቶ ቅስና ከሾሟቸው በኋላ አስተምረው እንዲመልሷቸው ወደ አረማውያን ዘንድ ላኳቸው፤ አረማውያንንም ሲያስተምሩ ክፉዎች ይዘው እጅግ አሠቃዩቸው፤ በሕይወት እያሉም ቆፍረው ቀበሯቸው ነገር ግን ጌታችን አዳናቸው።

ከእነርሱም ጋር ሲጋደሉ 10 ዓመት ከኖሩ በኋላ ሁሉንም አስተምረው አጠመቋቸው፤ ወላጆቿ በ6 ዓመቷ የሞቱባት ማርያ የምትባል እኅታቸውን እስከ 20 ዓመቷ ድረስ ፈሪሃ እግዚአብሔርንና ትሕትናን እያስተማሩ በሚገባ አሳደጓት፡፡

ሰይጣንም አባ አብርሃምን ፈትኖ ሊጥላቸው ብዙ ጊዜ የሞከረ ቢሆንም እሳቸው ግን ሁልጊዜ በትሕትና ያሸንፉት ነበር፤ አሁን ግን በዚህች ብላቴና ላይ በቅናት ተነሳባትና በፈተና ጣላት፤ ከአንድ መነኩሴ ጋር በመዋደድ ንጽሕናዋን እንዲታጣ አደረጋት፡፡

አባ አብርሃምም በዚያች ሌሊት ከይሲ ርግቢቱን ሲውጣትና ከጥቂት ቆይታ በኋላ ከእግሩ በታች ሲተፋት በራእይ ተመከቱ፤ ሰይጣንም በፈተናው እንዲትወድቅ ካደረጋት በኋላ ልብሰ ምንኩስናዋን ጥላ ወደ ሌላ ሀገር እንዲትሄድ አደረጋት፡፡

አባታችንም እኅታቸውን ከቦታዋ ሲያጧት ደንግጠው ስለ እርሷ በልቅሶ እግዚአብሔርን ጠየቁት፤ ከወራትም በኋላ ያለችበትን ስምተው የምንኩስና ልብሳቸውን ለውጠው የወታደር ልብስ ለበሱ፤ ፊታቸውንም ተከናንበው ማርያ ወደላችበት ሄዱ፤ ሴተኛ አዳሪም ሆና አገኟት፡፡

እሳቸውም ለርካሽ ተግባር የሚፈልጓት መስለው ለአሽከሯ ብርና ወርቅ ሰጥተው ማርያ ወዳለችበት የውስጠኛ ክፍል ገቡ፤ በሩን ከውስጥ ከዘጉ በኋላ ራሳቸውን ገለጡላት፡፡

እርሷም ስታውቃቸው በጣም ደንግጣ እንደ በድን ስትሆን እሳቸው ግን ‹‹ልጄ ሆይ አይዞሽ ከእግዚአብሔር በቀር ከኃጢአት ንጹሕ የሆነ የለም...›› እያሉ መክረው አጽናንተው በንስሓ እንድትመለስ ካደረጉ በሁዋላ በመጡበት ፈረስ ከኋላ አስቀምጠው ወደ ገዳም ወሰዷት፡፡

ማርያም ከበዓቷ ገብታ ማቅ ለብሳ እየተጸጸተች ብርቱ ተጋድሎዋን ጀመረች፤ ሌሊትና ቀን እያለቀሰች ትኅርምትን በማብዛት በጾም በጸሎት እየተጋደለች 5 ዓመት ኖረች፤ ቅዱሳንም በፊቷ ያለውን ብርሃን እያዩ እስኪያደንቁ ድረስ ተጋድሎዋን ፈጽማ ነሐሴ 5 ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡

አባ አብርሃምም በዘመኑ ሁሉ በጥርሱ ስቆ በከንፈሩም አልባሌ ነገርን ተናግሮ አያውቅ የክርስቶስን ህማም እያሰበ እንባው ያለማቁዋረጥ ሲፈስ ኖሮ በዚህች ቀን ዐረፈ፡፡

ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፤ በጸሎታቸው ይማረን

ጻድቅ ቅዱስ ዮሐንስ

ይህ ቅዱስ የነበረው በዘመነ ሰማዕታት ቢሆንም እንደ ሰማዕታት ስቃይ አልደረሰበትም፤ ክርስቲያኖችን እንዲገድሉና አብያተ ክርስቲያናትን እንዲያቃጥሉ ከተመደቡ ወታደሮች አንዱ ነበረ፤ ታዲያ እንዲገድላቸው የሚሰጡትን ክርስቲያኖች እየወሰደ ይደብቃቸው ነበር።

የመከራው ዘመን እስኪያልፍ ድረስም ይንከባከባቸው ነበር፤ ሌሎች ወታደሮች እንዳይነቁበት ሁሌም "ክርስቲያኖችን በጣም እጠላለሁ" እያለ ያወራ ነበር።

እርሱ በሌሊት ሁሌም ለጸሎት ይተጋ ነበር፤ በእንዲህ ያለ ግብር ኑሮም በዚህች ቀን በሰላም ዐርፏል::

አርኬ
ሰላም ለአብርሃም ዘተሰደ ወተዘብጠ። እምሕርትምና ወካህድ አረማውያነ እስከ ሜጠ። ወነፍስ እኅቱ ፄዊዎ እምአፈ ከይሲ መሠጠ። እስመ ኢጸግበ እምተጋድሎ እስከ ዕድሜሁ ሰለጠ። መዋዕለ ዓመታት ፸ ኮናሁ ኅዳጠ።

ቅዱስ ዮሐንስ ጻድቅ

በዚችም ቀን የከበረ ተጋዳይ ወታደር ዮሐንስ አረፈ፤ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ክርስቲያኖች ናቸው እርሱም በከሀዲ በዑልያኖስ ሠራዊት ውስጥ ወታደር ሆነ፤ ንጉሡም ከባልንጀሮቹ ወታደሮች ጋራ ላከው የክርስቲያን ወገኖችንም በሚኖሩበት ቦታ ሁሉ እንዲአሠቃዩአቸው አዘዛቸው።

እርሱም ለባልንጀሮች ጭፍሮች ክርስቲያኖችን እጅግ እንደሚጠላቸውና እንደሚጣላቸው ይገልጽላቸዋል በጭልታም ገብቶ በጎ ነገርን የሚሹትን ሁሉ ይሰጣቸዋል ያጽናናቸዋልም፤ ሁል ጊዜም ይጸልያል ይጾማል ይመጸውታልም የቅዱሳንንም አኗኗር ኖረ ምስጉን እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

ለእርሱም ለጌታ ምስጋና ይሁንየቅዱሳንም በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
አርኬ
ሰላም ዕብል ለዮሐንስ ሐራዊ። እምአብያጺሁ ዘኀብአ ሕገ ክርስቲያናዊ። ለምእመናን ያሠኒ በይነ ይቀትል ወያደዊ። ጸውዖ እንበይነዝ እግዚአብሔር ማሕየዊ ለከብካብ ሰማይ ድልው ለዝንቱ መርዓዊ።

አቡነ ፊሊጶስ ዘደብረ ቢዘን

እንደ ነቢዩ ኤርሚያስ በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ ስለተመረጡ ገና እንደተወለዱ ነው ሰማንያ አንዱን የብሉይ መጻሕፍትን አጠናወቅ ያወቁት፤ በ12 ዓመታቸውም ለመመንኮስና ገዳም ለመግባት ወስነው ወላጅ እናታቸውን አሰናብቺኝ በማለት ጠይቁ፡፡

ቅድስት እናታቸውም መርቀው ሸኟቸውና ትግራይ ውስጥ ወደሚገኘውና ደብረ ጸራቢ ወደሚባለው ገዳም ገቡ፤ የገዳሙ አስተዳዳሪ አቡነ በኪሞስም የምንኩስና ቀንበሩና ሸክሙ እጅግ ከባድ መሆኑን በመንገር ወደ እናታቸው እንዲመለሱ ቢመክሯቸውም አቡነ ፊሊጶስ ግን ለምንኩስና የታጩ ሙሽራ መሆናቸውን ነገሯቸው፤ ከብዙ ፈተናም በኋላ አመነኮሷቸው፡፡

በገዳሙም እንጨት እየለቀሙና እየፈለጡ፣ ውኃ እየቀዱ፣ የክርስቶስን ሕማሙን ሞቱን እያሰቡ በጾም ጸሎት ሲጋደሉ ከኖሩ በኋላ ጌታችን ተገልጦላቸው ወደ ሽሬ እንዲሄዱ ነገራቸውና ሽሬ አደያቦ ወደሚባለው ስፍራ ሄዱ፤ ብዙ አስደናቂ ተአምራት እያደረጉ ወንጌልን በሀገሩ ዞረው ሰበኩ፤ እንደ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በጥላቸው ድውያንን ይፈውሱ ነበር፡፡

ከዚህ በኋላ ወደ ደብረ ቢዘን እንዲሄዱ ተነግሯቸው የእርሳቸውን በረከት ለመቀበል ከመጡ 16 ደጋግ መነኮሳት ጋር ወደ ደብረ ቢዘን ሄዱ፤ ይኸውም በኤርትራ ክፍለ ሀገር በሐማሴን አውራጃ ከአሥመራ ከተማ በስተምሥራቅ 25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው አስደናቂው ገዳም ነው፡፡

ጻድቁ የሐይቅ እስጢፋኖስን ባሕር በተአምራት ያቃጠሉት አባት ናቸው፤ በንጉሡ በዐፄ ዳዊት ዘመን ሰንበትን አንድ ብቻ ናት እያሉ በአንደኛዋ ሰንበት ሥራ ሲሠሩ ጻድቁ አቡነ ፊሊጶስ ይህን ሰምተው አንዲት ሰንበት የሚሉትን ሁሉ ተቃወሟቸው፡፡

ከግብፅ የመጡት ጳጳስም ቀደም ብሎ ከአቡነ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ አሁንም ከአቡነ ፊሊጶስ ጋር ንጉሡ ዐፄ ዳዊት አከራክረዋቸው ጳጳሱ ተረቱ፤ ክፉዎችም በአቡነ ፊሊጶስ ላይ በክፋት ተነሱባቸው፤ በአቁማዳ ጠቅልለው ሐይቅ ባሕር ውስጥ ጣሏቸው፡፡

በዚህም ጊዜ እሳቸው የተጣሉበት ባሕር በእሳት ተቃጥሎ ጽድቃቸውን መስክሮላቸዋል፤ ዛሬም ድረስ በሐይቅ እስጢፋኖስ ባሕር ዳርቻ ላይ የተቃጠለው ድንጋይ ምልክቱ በግልጽ ይታያል፤ በወቅቱ የንጉሡ ሚስት በዋናተኛ አስፈልጋ ከሐይቁ ውስጥ አስወጣቻቸው፡፡

እግራቸውንም አጥባቸው ስትጨርስ የእግራቸውን እጣቢ ጠጣችው፤ ወዲያውም ‹‹ከማኅፀንሽ ፍሬ ታላቅ ጻድቅ ልጅ ይወጣል›› ብለው ትንቢት ነገሯት፤ በትንቢታቸውም መሠረት ታላቁ ጻድቅ ንጉሥ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ተወልዱ፡፡

በወቅቱ በተፈጠረው አለመግባባትና ክፉዎችም በባሕር ውስጥ ስለጣሏቸው ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም አቡነ ፊሊጶስን ከልብ ይቅርታ ጠይቀው ወዲያው ታርቀዋል፤ በዘመናቸውም ርኃብ ስለነተሳ ጻድቁን ከገዳማቸው አስጠርተው ‹‹ምን ባደርግ ይሻለኛል›› ብለው አማክረዋቸዋል፡፡

አቡነ ፊሊጶስም ‹‹የጌታችንን መስቀል ያስመጡ›› ብለው መከሯቸው፤ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም በአቡን ፊሊጶስ ምክር መሰረት ከኢየሩሳሌም፣ ከቍስጥንጥንያና ከእስክንድርያ መንግሥታት ጋር ተጻጽፈው ዓሥሩን ታላላቅ ቅዱሳን ይዘው ሄደው መስቀሉን መስከረም 10 ቀን አምጥተውታል፡፡

ቅዱስ መስቀሉን ያመጡት ዓሥሩ ቅዱሳንም የደብረ ቢዘኑ አቡነ ፊሊጶስ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ ኂሩተ አምላክ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ እንድርያስ፣ አቡነ በትረ ማርያም፣ አቡነ ዮሐንስ፣ አቡነ ታዴዎስ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ፣ አቡነ ዘካርያስ፣ አቡነ ያሳይና አቡነ ቶማስ ናቸው፡፡

አቡነ ፊሊጶስ ዘደብረ ቢዘን በታላቅ ተጋድሎ ኖረው ከጌታችን ዘንድ ታላቅ ቃልኪዳን ከተቀበሉ በኋላ ነሐሴ 5 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡

የአቡነ ፊሊጶስ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፤ በጸሎታቸው ይማረን
አርኬ
ሰላም ለፊልጶስ እንተ ክህለ ያዕዱ። ለዘጸውዖ ብእሲ ለውኂዘ ክረምት እምነ ሞገዱ። ወእምኔሁ አብ እለ በመንፈስ ተወልዱ። እንዘ ይዜንዉ ኃይሎ ወምግባረ ጽድቁ ይንዕዱ። ስሙዓቲሁ ወጽአ ለዓለም በዐውዱ።

(ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ 5)

🗓 የነሐሴ 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ቅዱስ አባ አብርሃም ገዳማዊ
2.ቅድስት ማርያ እህቱ
3.ቅዱስ ዮሐንስ ጻድቅ
4.አባ ፊልዾስ ዘደብረ ቢዘን

🗓ወርሐዊ በዓላት

1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም
3.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
4.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
5.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
6.ቅድስት አውጋንያ (ሰማዕትና ጻድቅ)

የነሐሴ 5 ቀን የእለቱ ግጻዌ

መልእታት
👇

2ቆሮ 12÷10-17

1ዮሐ 5 ÷14-ፍጻ

ሐዋርያት 15፥ 1-13

ምስባክ 👇

"ወትሠይመኒ ውስተ ርእሰ ሕዝብ።
ሕዝብ ዘኢየአምር ተቀንየ ሊተ።
ውስተ ምስማዐ እዝን ተሰጥዉኒ።" መዝ. 17፥43

ትርጉም➣"የአሕዛብም ራስ አድርገህ ትሾመኛለህ። የማላውቀው ሕዝብም ይገዛልኛል።በጆሮ ሰምተው ተገዙልኝ።"መዝ. 17፥43

የእለቱ ወንጌል📖
👇
ሉቃስ 15÷1-11

የሚቀደሰው ቅዳሴ
👇
ቅዳሴ ዘእግዝእትነ ነው።

የነሐሴ 5 ቀን ወንጌል ሙሉ ንባብ📖

ሉቃስ 15

¹ ቀራጮችና ኃጢአተኞችም ሁሉ ሊሰሙት ወደ እርሱ ይቀርቡ ነበር።
² ፈሪሳውያንና ጻፎችም፦ ይህስ ኃጢአተኞችን ይቀበላል ከእነርሱም ጋር ይበላል ብለው እርስ በርሳቸው አንጐራጐሩ።
³ ይህንም ምሳሌ ነገራቸው እንዲህ ሲል፦
⁴ መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ፥ ዘጠና ዘጠኙን በበረሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሄድ ከእናንተ ማን ነው?
⁵ ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል፤
⁶ ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ፦ የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ ይላቸዋል።
⁷ እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።
⁸ ወይም አሥር ድሪም ያላት አንድ ድሪም ቢጠፋባት፥ መብራት አብርታ ቤትዋንም ጠርጋ እስክታገኘው ድረስ አጥብቃ የማትፈልግ ሴት ማን ናት?
⁹ ባገኘችውም ጊዜ ወዳጆችዋንና ጐረቤቶችዋን በአንድነት ጠርታ፦ የጠፋውን ድሪሜን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ ትላቸዋለች።
¹⁰ እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል።

35ኛው ዙር የበገና እጣ እንደቀጠለ ነው60 ሰው በ200 ብርከ1 እስከ 60 ቁጥር ቀድሞ ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በመምረጥ Awash👉🏦 013200909837300CBE👉🏦 1000510909...
10/08/2026

35ኛው ዙር የበገና እጣ እንደቀጠለ ነው

60 ሰው በ200 ብር
ከ1 እስከ 60 ቁጥር ቀድሞ ያልተያዘ የፈለጋችሁትን ቁጥር በመምረጥ

Awash👉🏦 013200909837300

CBE👉🏦 1000510909635

BOA👉🏦 47056497

Tele birr👉🏦 0933143133

አቤኔዘር ገዛኸኝ ብለው ከፍለው

ስም ስልክ ሪሲት t.me/abigezenige ላይ ይላኩ።

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

ያልተያዙ ቁጥሮች

20
26
30-36
38-42
44
46
48-51
53-55
57-60

ነሐሴ አራት የበግ ጸጉር ለብሶ በበረሃ የሚኖር ተጋዳይ የሆነ አቡነ ማቴዎስ ዕረፍቱ ነው። ዳግመኛም በዚኽች ዕለት በገባው ንስሓ በዘመኑ ላይ 15 ዓመት የተጨመረለትና ከዳዊት ዘር የሆነው የአ...
10/08/2026

ነሐሴ አራት የበግ ጸጉር ለብሶ በበረሃ የሚኖር ተጋዳይ የሆነ አቡነ ማቴዎስ ዕረፍቱ ነው። ዳግመኛም በዚኽች ዕለት በገባው ንስሓ በዘመኑ ላይ 15 ዓመት የተጨመረለትና ከዳዊት ዘር የሆነው የአካዝ ልጅ ንጉሡ ሕዝቅያስ ዕረፍቱ ነው፡፡

ቅዱስ ሕዝቅያስ ጻድቅ (ንጉሠ ይሁዳ)

ነሐሴ አራት በዚህች ቀን ከዳዊት ዘር የሆነ የአካዝ ልጅ ሕዝቅያስ ንጉሥ አረፈ። ከጻድቁ ንጉሥ ከዳዊት በኋላ እንደ ሕዝቅያስ ያለ በእስራኤል ውስጥ አልተሾመም ከዚህ ጻድቅ ንጉሥ በቀር ሁሉም ጣዖትን አምልከዋልና መሠዊያም ሠርተዋልና።

እርሱም በነገሠ ጊዜ ጣዖታትን ሰበረ መሠዊያቸውንም አፈረሰ ከነሐስ የተሠራውንም እባብ ቆራረጠ የእስራኤል ልጆች አምልከውት ነበርና እግዚአብሔርም ዘመነ መንግሥቱን እጅግ አሳመረለት በጎ ነገርንም ሁሉ ሰጠው ።

ሕዝቅያስም በነገሠ በዐሥራ አራተኛው ዘመን የፋርስ ንጉሥ ሰናክሬም መጥቶ ኢየሩሳሌምን ከበባት ይህም ሰናክሬም በዘመኑ እንደርሱ ያለ የሌለ ኃይለኛ ብርቱ የምድር ነገሥታት ሁሉ የፈሩትና የታዘዙለት ነው ። ሕዝቅያስም ከእርሱ ግርማ የተነሣ ፈርቶ አገሩን እንዳያጠፋ ብዙ ወርቅና ብር እጅ መንሻ ላከለት ሰናክሬምም ደስ ብሎት ምንም ምን አልተቀበለም በእርሱ ላይና በልዑል እግዚአብሔር ላይ ተቆጥቶ እግዚአብሔር ከእኔ እጅ ሊያድናችሁ አይችልም በማለት የስድብን ቃል ላከ እንጂ ።

ሁለተኛም በልዑል ስም ላይ ስድብና ቍጣ የተጻፈበትን ደብዳቤ ላከ ሕዝቅያስም በሰማ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት ገብቶ አለቀሰ ልብሱንም ቀዶ ማቅ ለበሰ እንዲህም ብሎ ጸለየ ። አቤቱ የእስራኤል አምላክ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ አንተም ብቻህን በዓለም መንግሥታት ላይ ንጉሥ የሆንክ አንተም ሰማይና ምድርን የፈጠርህ ልመናዬን አድምጥ ። ዐይኖችህን ገልጠህ ተመልከት ሕያው እግዚአብሔር አንተን እያቃለለ ሰናክሬም የላከውን ቃሉን ስማ ።

ከዚህም በኋላ ንጉሥ ሕዝቅያስ የፋርስ ንጉሥ ሰናክሬም የተናገውን እንዲነግሩትና ስለርሱና ስለ ሕዝቡ ይጸልይ ዘንድ ወደ ኢሳይያስ መልእክተኞችን ላከ ። ኢሳይያስም ከእግዚአብሔር ቃልን ተቀብሎ እንዲህ ብሎ መለሰለት ልብህን አጽና አትፍራ በዓለሙ ሁሉ እንደርሱ ያለ ያልተሰማ ዕፁብ ድንቅ የሆነ ሥራ በሰናክሬም ላይ ሊሠራ እግዚአብሔር አለውና ።

ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር የላከው መልአክ መጥቶ ከፋርስ ሠራዊት መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ሰዎችን ገደለ የለኪሶም ሰዎች ሲነጋ በተነሡ ጊዜ የሞቱትን ሰዎች ሬሳ ሁሉ አገኙ የተረፉትም ከንጉሣቸው ጋራ ሸሽተው ነነዌ አገር ገቡ ። ሰናክሬምም ሊጸልይ ወደጣዖቱ ቤት በገባ ጊዜ ልጆቹ አድራማሌክና ሶርሶር በሰይፍ መትተው ገደሉት ። ሕዝቅያስምከሰናክሬም እጅ ድኖ የተመሰገነ እግዚአብሔርን አመሰገነ ።

በዚያም ወራት ሕዝቅያስ ታመመ ለሞትም ደረሰ የአሞፅ ልጅ ኢሳይያስም ወደረሱ መጥቶ እግዚአብሔር እንዲህ አለ ትሞታለህ እንጂ አትድንምና ቤትህን ሥራ አለው። ሕዝቅያስም ፊቱን ወደግድግዳው መልሶ ወደ እግዚአብሔር ለመነ እያመሰገነውም እንዲህ አለ አቤቱ በቀና ልቡና በዕውነት ሥራ በፊትህ ጸንቼ እንደኖርኩ ፈቃድህንም እንደፈጸምሁ አስብ ብሎ ሕዝቅያስ ፈጽሞ ጽኑዕ ልቅሶን አለቀሰ ።

ኢሳይያስም ወደ መካከለኛው ዐፀድ ደረሰ እግዚአብሔርም እንዲህ ብሎ ተናገረው ሒደህ ለወገኖቼ ንጉሥ ለሕዝቅያስ ያባትህ የዳዊት ፈጣሪ እግዚአብሔር እንዲህ አለ በለው ። ጸሎትህን ሰማሁ ዕንባህንም አየሁ እነሆ እኔ አድንሃለሁ እስከ ሦስት ቀንም ወደ እግዚአብሔር ቤት ትወጣለህ ።

በዘመኖችህም ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት ጨምሬልሃለሁ ከፋርስ ንጉሥ እጅም አድንሃለሁ ይቺንም አገር ስለ እኔና ስለ ባለሟሌ ዳዊት አጽንቼ እጠብቃታለሁ ። ሕዝቅያስም ኢሳይያስን እንዲህ አለው እግዚአብሔር እንደሚያድነኝና እስከ ሦስት ቀን ወደ እግዚአብሔር ቤት ለመውጣቴ ምልክቱ ምንድ ነው ።

ኢሳይያስም እንዲህ አለው የተናገረውን ቃል ያደርግ ዘንድ ከእግዚአብሔር የተገኘ ምልክቱ ይህ ነው እነሆ ጥላው ወደ ዐሥረኛው እርከን ቢመለስ ምልክቱ ይህ ነው ። ሕዝቅያስም እንዲህ አይደለም የጥላው ወደ ዐሥረኛ እርከን መመለስ ቀላል ነው ። መመለስስ ከሆነ ፀሐይ ወደ ዐሥረኛው እርከን ይመለስ አለ ። ኢሳይያስም ወደ እግዚአብሔር ጮኸ ፀሐይም ዐሥሩን እርከን ተመለሰ ።

ሕዝቅያስንም የምድር ነገሥታት ሁሉ ፈሩት እጅ መንሻም አገቡለት የእግዚአብሔር ኃይል ከእርሱ ጋራ እንዳለ አውቀዋልና ። በመንበረ መንግሥቱም ሃያ ዘጠኝ ዓመት ነግሦ ኖረ ። እግዚአብሔርን አገልግሎ በሰላም አረፈ ።

አርኬ
ሰላም ለሕዝቅያስ ዘጸለየ በሕቱ። ዘተወሰከ ዘመኑ ወፈድፈደ እምኁልቁ እመኒ ሶቢሃ ተዐየርዋ ለጽድቁ ። በእደ መልአክ ሠራዊተ ፋርስ ኅልቁ ወለመልአኮሙ ቀተልዎ ደቁ።

አባ ማቴዎስ ገዳማዊ

በዚችም ቀን እንደ በግ የጸጒር ልብስ ለብሶ በበረሃ የሚኖር አባ ማቴዎስ አረፈ። ይኸውም አባ ማቴዎስ የአቶሩን ንጉሥ በተአምሩ ከነቤተሰቡ ያሳመነው ነው፡፡ በእርሱም ትምህርት በሀገሪቱ ብዙ ሰማዕታት ተገኝተዋል፡፡ ቅድስት ሣራና ወንድሟ መርምህናም አባታቸው የአቶር ንጉሥ ሲሆን እርሱም የተቀረጹ ጣዖታን ያመልክ ነበር፡፡ እናታቸው ግን አማኝ ክርስቲያን ነበረች፡፡ አባቱን ለምኖና አስፈቅዶ ወደ ዱር ሄዶ አራዊትን ለማደን በወጣ ጊዜ እናቱ የሰማይና የምድር አምላክ እግዚአብሔር በላዩ በረከትን ያሳድርበት ዘንድ ከጸለየችለት በኋላ ሸኘችው፡፡

መርምህናም ከአርባ ፈረሰኛ አገልጋዮቹ ጋር ወጥቶ ሄደ፡፡ ወደ አንድ ተራራም ወጥቶ በዚያ አደረ፡፡ በሌሊትም የታዘዘ መልአክ ጠራውና ‹‹መርምህናም ሆይ ተነሥተህ ወደዚህ ተራራ ጫፍ ላይ ውጣ፣ ስሙ ማቴዎስ የሚባል ቅዱስ ሰው ታገኛለህ፡፡ እርሱም የሕይወትን ነገር ይነግርሃል›› አለው፡፡

ሲነጋም ወደ ተራራው ጫፍ ላይ ወጣና የበግ ጠጉር ለብሶ አባ ማቴዎስን ባገኘው ጊዜ እጅግ ፈራ፡፡ አባ ማቴዎስም ‹‹አይዞህ አትራ እኔም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነኝና አትፍራ›› ብለው አበረቱት፡፡ መርምህናም የእግዚአብሔርን ስም ሲጠሩ ሲሰማ ‹‹አባቴ ከአማልክቶች በቀር አምላክ አለን?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ አባታችንም የሃይማኖትን ነገር ሁሉንም አስተማሩት፡፡ መርምህናም ‹‹ከራስ ጠጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ ድረስ በለምጽ የተመታች እኅት አለችኝና እርሷን የአምላክህን ስም ጠርተህ ካዳንክልኝ በእውነት በአምላክህ አምናለሁ›› አላቸው፡፡ ተያይዘውም ከተራራው ወርደው ወደ ንጉሡ ቤት ሄደው መርምህናም ለእናቱ ያጋጠመውን ነገር ነገራትና በለምጽ የተመታችውን እኅቱን ሣራን በሥውር ወደ አቡነ ማቴዎስ ዘንድ ወሰዳት፡፡ አቡነ ማቴዎስም መሬቱን ባርከው ውኃ አፍልቀው አጠመቋትና ከለምጹዋ ፈወሷት፡፡ አርባው ጭፍራዎችም አምነው በአባታችን እጅ ተጠመቁ፡፡

አባታችንም ሰማዕትነትን እንደሚቀበሉ ትንቢት ነግረዋቸው ባርከው መርቀው አሰናበቷቸው፡፡ የአቶሩም ንጉሥ ልጆቹንና ያመኑትን አርባውን ጭፍራዎቹን በሰይፍ ገደላቸው፡፡ ሰይጣንም በአቶሩ ንጉሥ አድሮ አሳበደው፡፡ እንደ እሪያም መጮህ ጀመረ፡፡

ክርስቲያን የሆነችው የቅዱስ መርምህናምና የቅደስት ሣራ እናታቸው ወደ አባ ማቴዎስ ሄዳ ንጉሡ በልጆቹ ላይ ያደረገውንና በእርሱም ላይ የተፈጸመበትን ነገር ነገረቻቸው፡፡ አባ ማቴዎስም ንጉሡን ዘይት ቀብተው ጸልየው ፈወሱት፡፡ በውስጡ አድሮበት የነበረውንም ሰይጣን በእሪያ መልክ ከንጉሡ ውስጥ አስወጡት፡፡

ንጉሡም ወደ ልቡ ሲመለስ በአቡነ ማቴዎስ ትምህርት በጌታችን አመነ፡፡ በሚገዛቸው አገሮች ሁሉ ያሉትን ሰዎች ይዞ ከነቤተሰቡ ተጠመቀ፡፡ አቡነ ማቴዎስም እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ ኖረው በዚህች ዕለት በሰላም ዐረፉ፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ 4)


🗓 የነሐሴ 4 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1. ቅዱስ ሕዝቅያስ ጻድቅ (ንጉሠ ይሁዳ)
2. አባ ማቴዎስ ገዳማዊ
3. ቅዱስ ዳዊት ሰማዕት

🗓ወርሐዊ በዓላት

1. ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ወንጌላዊው)
2. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
3. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
4. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ (ሰማዕት)

የነሐሴ 4 ቀን የእለቱ ግጻዌ

መልእታት
👇

ሮሜ 12÷16-ፍጻ

1ጴጥ 5 ÷6-12

ሐዋርያት 17፥ 23-28

ምስባክ 👇

"እግዚኦ በኃይልከ ይትፌሣሕ ንጉሥ። ወብዙኀ ይትኀሠይ በአድኅኖትከ። ፍትወተ ነፍሱ ወሀብኮ"። መዝ 20፥1-2

ትርጉም➣"አቤቱ፥ በኃይልህ ንጉሥ ደስ ይለዋል፤ በማዳንህ እጅግ ሐሤትን ያደርጋል። የልቡን ፈቃድ ሰጠኽው፥ የከንፈሩንም ልመና አልከለከልኸውም"። መዝ 20፥1-2።

የእለቱ ወንጌል📖
👇
ሉቃስ 14÷31-ፍጻ

የሚቀደሰው ቅዳሴ
👇
ቅዳሴ ዘእግዝእትነ አወ ዘቄርሎስ ነው።

የነሐሴ 4 ቀን ወንጌል ሙሉ ንባብ📖

ሉቃስ 14

31 ወይም ሌላውን ንጉሥ በጦርነት ሊጋጠም የሚሄድ፥ ከሁለት እልፍ ጋር የሚመጣበትን በአንድ እልፍ ሊገናኝ የሚችል እንደ ሆነ አስቀድሞ ተቀምጦ የማያስብ ንጉሥ ማን ነው?
32 ባይሆንስ ሌላው ገና ሩቅ ሳለ መልክተኞች ልኮ ዕርቅ ይለምናል።
33 እንግዲህ እንደዚሁ ማንም ከእናንተ ያለውን ሁሉ የማይተው ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም።
34 ጨው መልካም ነው፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፈጣል?
35 ለምድር ቢሆን ለፍግ መቈለያም ቢሆን አይረባም፤ ወደ ውጭ ይጥሉታል። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።

ከለሩን ይንኩትቀድማችሁ ያገኛችሁትን ኮሜንት ላይ ጻፉ።     ሶስቱም ጸንተው የሚኖሩ ናቸው።
09/08/2026

ከለሩን ይንኩት
ቀድማችሁ ያገኛችሁትን ኮሜንት ላይ ጻፉ።
ሶስቱም ጸንተው የሚኖሩ ናቸው።

💒✨✞  መ ል  ክ  አ     ፍ  ል  ሰ  ታ    ለ ማ ር ያ ም  ✞✨💒                                       ▬▬▬▬▬       ▬▬       ▬▬▬▬▬        ...
09/08/2026

💒✨✞ መ ል ክ አ ፍ ል ሰ ታ ለ ማ ር ያ ም ✞✨💒

▬▬▬▬▬ ▬▬ ▬▬▬▬▬

፩:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ምስለ ነፍስኪ ኢመዋቲ
በተሰናዕዎ አሐቲ።
ድንግል በ፪ኤ ማርያም ወለተ ማቲ
ሐመረ ተርሴስ ዘሰሎሞን አንቲ
እንተ አእተውዋ ጠቢባን ወርቀ አፌር (አፌዝ)ባቲ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
ሕያዊት ከምትሆን ነፍስሽ ጋር በፍጹም ተዋህዶ ለተከናወነው ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
አንቺ ወለተ ማቲ የተባልሽ በነፍስ በስጋ በውስጥ በአፍአ አማናዊት ድንግል ነሽ እኮን ብልሆችና አዋቂዎች የአፌዝን ወርቅ አሳፍረው የሚጓዙብሽ ሰሎሜናዊት የተርሴስ መርከብ አንቺ ነሽ፡፡

፪:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ መካነ ፍሥሓ ወኑዛዜ።
ኀበ ይረስእዎ ለላኅ ወኢይሔይልዎ ለትካዜ።
ማርያም ህሉት ውስተ ልበ አምላክ እምቅድመ ጊዜ
ትፍሥሕትሰ ተእሣሕኩ በፍልሰትኪ ይእዜ።
ገጸ ዚአኪ እሬኢ ማዕዜ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
ኅዘንን ወደሚረሱበት ትካዜን ወደማያስቡበት የተረጋጋ ፍጹም ደስታ ወዳለበት ለተጓዘው ፍልሰተ ስጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ቅድመ ዓለም በአምላክ ልቡና ታስበሽ ያለሽ ነሽ እኮን፡፡ እንግዲህ በፍልሰትሽ በፍጹም ደስታ ዛሬ ደስ ተሰኝቻለሁ ነገር ግን ፊትሽን የማየው መቼ ይሆን፡፡

፫ :- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ውስተ ልበ ስብእ ዘኢተሐለየ
እንዘ ትትዓጸፊ ጸጋ ወትለብሲ ዕበየ።
ማርያም ሥጋኪ ዘተመሰለ ባሕርየ
ተሀውከ ሞት አኮኑ ሶበ ነጸረ ወርእየ
እንዘ በደመና ብሩህ የአርግ ሰማየ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
በሰው ልብ የማይታሰበውን ግርማ ሞገስን የተላበሰ ጸጋ ክብርን ለተጎናጸፈ ፍልሰተ ስጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ሥጋሽ ዕንቈ ባሕርይ ነው፡፡ ስለዚህም በደመና ሲያርግ በተመለከተ ጊዜ ሞት በፍጹም ኃፍረት አፈረ፡፡

፬:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ እግዚአብሔር ዘባረካ
ወዓልአለ ክብራ እምፍልሰተ ኄኖክ ወልደ ባረካ።
ማርያም ፍሥሕት ወብርህት ዕለተ ዋካ
በእንቲአኪ ይገብሩ ውስተ ሰማያዊት ታዕካ
ነገደ መላእክት አእላፍ ሱባዔ ፋሲካ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
ከባረካ ልጅ ከኄኖክ ፍልሰት ከፍ ከፍ አድርጎ እግዚአብሔር አክብሮ ለባረካት ፍልሰተ ስጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ከብርሃናት ሁሉ የምትበልጭ ብርህትና አስደሳችነሽ እኮን ስለዚህም የብዙ ብዙ የሚሆኑ የሰማይ መላእክት በአንቺ ምክንያት በሰማያዊት አዳራሽ ታላቅ ደስታን ያደርጋሉ፡፡

፭:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ዘኢይቀበል ሞገሱ
ወዘኢይነጽፍ ባሕረ ተውዳሱ።
ማርያም ታዕካ ለእግዚአብሔር ጽርሓ መቅደሱ
ተበሃሉ በሰማያት እለ ኪያኪ አፍለሱ
ማርያምሰ እንተ በምድር ታንሶሱ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
ክብሩ ባለሟልነቱ ለማይገሰስ የምስጋናው ባሕር (ባሕርይ)ለማይጎድል ፍልሰተ ስጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
የእግዚአብሔር የልዩ ምስጋናው አዳራሽ ነሽ እኮን ስለዚህ በፍልሰትሽ ጊዜ አንቺን የተቀበሉ መላእክት ማርያምስ በሰማይም በምድርም የከበረች ነች ተባባሉ፡፡

፮:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ዘአፈድፈደ ስባሔ
እምፍልሰተ ያዕቆብ ዓርከ ኤሎሄ።
ማርያም ቀንሞስ ማርያም አፈወ ርኄ
እንዘ ብርሃነ ይለብሱ ወይትአጸፉ ሡራኄ
ሞገሰ ፍልሰትኪ መላእክት ሰበኩ ኵለሄ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ❗
ከጌታ ወዳጅ ከያዕቆብ ፍልሰት ይልቅ ክብር ምስጋና ለተገባው ፍልሰተ ስጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ቀናንሞ የተባለ ሽቱ ነሽ የልዩ ሽቱ አይነትም መገኛ ነሽ፡፡ ስለዚህም ብርሀን ለብሰው በብርሃን ነፀብራቅ ተጎናጽፈው የፍልሰትሽን በዓል መላእክት ያከብራሉ፡፡

፯:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ስቡሐ ዘተሰብሐ።
እንበሌኪ ድንግል ወእንበለ ወልድኪ በኵረ ፍሥሓ
እምፀዳለ ፀሐይ ወወርኅ
ስነ ስብሐቲሁ አብርሀ አልቦ ለሞት ማዕሠሪሁ ዘፈትሐ
ወሙታነ በሲኦል አንቅሐ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
ከፀሐይና ከጨረቃ ሥነ ጸዳል ይልቅ ፈጽሞ ለሚያበራውና ፍጹም ምስጋና ለተገባው ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ሁሉን ከሚያስደስትና የደስታ መገኛ ከሚሆን ልጅሽና ያለ አንቺ የሞትን ማሰሪያ በጣጥሶ የሲኦልን ደጃፍ ሰባብሮ ነፍሳትን ከዲያብሎስ የባርነት አገዛዝ ነጻ ያወጣ ማንም የለም፡፡

፰:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ እምዓለመ መትሕት ኃላፊ።
ዉስተ አውደ ኪሩብ ተሃሉ እንዘ የዓቅባ ሱራፊ።
ማርያም ምዕዝት እምስነ ጽጌያት ዘወርኃ ተውፊ።
ናሁ ተሰጠምኩ ውስተ ባሕረ ስሕተት ጸናፊ።
በሐመረ ንጽሕኪ ወትረ ኪያየ ሐድፊ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
ሱራፊ መልአክ እየጠበቃት በኪሩቤል ከተማ ትኖር ዘንድ ከዚህ ከአላፊውና ከጨለማው ዓለም ለተዛወረችው ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ከጥቅምት ወር የጽጌ የአበባ ሽታ ይልቅ የመዓዛሽ ጣዕም እጅግ የጣፈጠ ነው፡፡ እነሆ በስህተት ባሕር ልሰጥም ተቃርቤአለሁና በንጽሕናሽ በቅድስናሽ መርከብ አሳፍረሽ እኔን አገልጋይሽን አሻግሪኝ፡፡

፱:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ለሊቀ ካህናት ዘአደሞ።
መሥዋዕተ መድኃኒት ያዕርግ ቅድስተ ቅዱሳን ቀዊሞ።
ለመላከ ሞት ጸዋግ መልአከ በቀል ወተቀይሞ።
ሚመጠነ አድወዮ ወሚመጠነ አሕመሞ።
ሞገሰ ፍልሰትኪ ማርያም ዘአምላክ ሐተሞ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ❗
በቅድስተ ቅዱሰን ቆሞ የነግሁን መስዋዕት ሲያሳርግ የካህናቱን አለቃ ለአስደነቀው ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
አምላክ ያተመው የፍልሰትሽ ግርማ ሞገስ ያን የቂም በቀል መልአክና የክፉ መጨረሻ የሆነ መልዐከ ሞት ምንኛ አሰቃየው ምንኛ መከራውን አሳየው እሰይ እሰይ

፲:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ዘአጥናን ኃይሉ።
ወአኤናዎን መዝራዕተ ሣህሉ።
ማርያም ሣህልኪ ለትውልደ ትውልድ ዘይሄሉ።
አምጻኢተ ምሕረት ማርያም ለኃጥአነ ምድር ኵሉ።
ወቡርክት ማርያም ለክርስቶስ አባሉ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ❗
የይቅርታው ክናድ ለዘላለሙ ጸንቶ ለሚኖረውና የኃይለኞች ኃይለኛ ለሚሆን ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል።
ድንግል እመቤቴ ሆይ
መታሰቢያሽ ከትውልድ ወደ ትውልድ ለዘላለም ሲታሰብ ይኖራል በምድር ላይ ለሚኖሩ ኃጥአን ሁሉ አማልደሽ ምህረት የምታስገኝ ነሽና እመቤቴ ሆይ የተባረክሽ የክርስቶስ አካሉን ነሽ ፡፡

፲፩:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ደባትረ ብርሃን ኀበ ተተክሉ።
ለገነተ ጽባሕ በማዕከሉ፡፡
ውድስት አንቲ ወስብሐት በአፈ ኲሉ።
እምነ ጻድቃን ዘታሕቱ ወእምትጉሃን ዘላዕሉ።
ማርያም ለኪ ስብሐተ አደሉ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ❗
ለተመረጡት ልጆች እናት ትሆኛቸው ዘንድ ምጡቅ በሆነ በብርሀን ሰረገላ ለመጠቀ ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል።
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ብዙዎች ወገኖች በሁለት ድሪም በአስፈላጊው ጊዜ በትጋትና በመፋጠን ወገንን እንደሚዋጁ እኔን አገልጋይሽን በይቅርታሽ ወርቅ ዋጅተሽ ገንዘብ አድርጊኝ፡፡

፲፪:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ እግዚአብሔር ዘተዋሐዳ
ወተካፈለ ክበዳ።
ለፍልሰትኪ ድንግል እምኢየሩሳሌም ምድረ ይሁዳ
አፈወ ስኂን ወተዝካረ ዕጣን ፀዓዳ።
ነገሥተ ተርሴስ ወደስያት ያበውዑ ጋዳ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
እግዚአብሔር ለተዋሐዳትና ስነ ሥርአቷንም ለተካፈላት ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል።
ድንግል እመቤቴ ሆይ
በፍልሰትሽ ጊዜ በምድረ ይሁዳና በኢየሩሳሌም አደባባይ የተርሴስና የደስያት ነገስታት ለመታሰቢያሽ መዓዛቸው የጣፈጠ ሽቶና ልዩ ልዩ እጅ መንሻዎች ይዘው ቀረቡ፡፡

፲፫:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ እግዚአብሔር ዘዓልዓሎ
እምፍልሰተ ኤልያስ ነቢየ ሴሎ፡፡
ማርያም ሰድኒ ውስተ ብሔረ ትፍሥሕት በክነፈ አውሎ
ለምንት ሊተ በነዝሕላል ውስተ ብሔረ ስሕተት እዴሎ
እንዘ ይዴግነኒ ሞት ዘይእኅዝ ኲሎ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ❗
ከሴሎ ነቢይ ከኤልያስ ፍልሰት ይልቅ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ላደረገው ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
ሁሉን እንዳውሬ የሚያድን ሞት ተከትሎኝ የኔ በተድላ ደስታ መኖር ምኔም ስለአይደለ በአውሎ ነፋስ ክንፍ ጠልፈሽ ጻድቅ ካለበት ቦታ ወስደሽ ከዚያ አድርሽኝ።

፲፬:- ለፍልሰተ ሥጋኪ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ውስተ ብሔር።
ሥዑር እንተ ኬንያሃ ወገባሪሃ እግዚአብሔር፡፡
ማርያም ኅብእኒ እምግብርናተ ሞት መሪር
ሶበሰ ትፈቅዲ ንግሥተ ሰማያት ወምድር።

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ❗
ተጠባቢዋና መጋቢዋ እግዚአብሔር የሆነ ወደ አማረችውና ወደ ተደላደለችው ሀገር ለፈለሰው ፍልሰተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
መሪር ከሆነ የሞት አገዛዝ ነፃ አውጪኝ የሰማይና የምድር ንግሥት ሆይ አንቺ እኮ ከፈቀድሽ ኃጥኡን ባሪያ ነፃ ማውጣት አይሳንሽም ፡፡

፲፭:- ለትንሣኤ ሥጋኪ

ሰላም ለትንሣኤ ሥጋኪ ዘትንሣኤ ክርስቶስ መንታ
ርእሶ ሕያወ ድኅረ ኀብአ ውስቴታ
በጽላሎትኪ ኅብእኒ ማርያም ርግበ ኤፍራታ
ወሰውርኒ በአጽፍኪ አመ ይከውን ሐተታ
ወአመ ታገብእ ምድር ዘነሥአት ማኃፀንታ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ❗
ሕያው ባሕርዩን በውስጧ ሰውሮ ለተነሳባት የክርስቶስ ትንሳኤ መንትያ ለሆነች ትንሣኤ ስጋሽ ሰላምታ ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
በዚያች በቁርጥ ቀን የፍርድ ምርመራ በተደረገ ጊዜ ምድርም አደራዋን በመለሰች ጊዜ አንቺ የኤፍራታ ርግብ ሆይ በክንፈ ረድኤትሽ ሠውሪኝ በጥላሽም ሥር ሸሽገሽ አድኚኝ፡፡

፲፮:- ለዕርገተ ሥጋኪ

ሰላም ለዕርገተ ሥጋኪ ዘተወጥነ ቦቱ
ዕርገተ ቅዱሳን ሰብእ ዘበኀቤኪ ተአኲቱ፡፡
ለሊቃ ካህናት አሮን ማርያም ሠርጐ ትርሢቱ
ሠዑለ ይኩን በልብስኪ እንተ ላዕሉ ወታሕቱ
ፍሬ ከናፍር ወአፍ ውዳሴኪ ዝንቱ፡፡

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
አንቺን ለሚያመሰግኑ ቅዱሳን ሰዎች ሁሉ የዕርገታቸው መመሪያ ለሆነ ዕርገተ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል።
ድንግል እመቤቴ ሆይ
የሊቀ ካህናቱ የካህኑ የአሮን የሽልማቱ ጌጥ ነሽ እኮን በአንደበታችን የሚነገረው የምስጋናሽ ፍሬ ሁሉ በውስጥም በውጭም ላለው ልብስሽ ላይ በስዕል መልክ ተቀርጾ ይኑር ፡፡

፲፯:- ስብሐት ለኪ

➥ እመቤቴ ማርያም ሆይ ❗
በሥጋዊ በደማዊ አንደበት ሁሉ ለአንቺ ምስጋና ይገባል፡፡
በመላእክትም አንደበት ያለማቋረጥ ለአንቺ ምስጋና ይገባል፡፡
ድንግል እመቤቴ ሆይ
የደብተራ ኦሪት ቃል ኪዳን የተጻፈብሽ የሕግ ታቦት ላንቺ ሰላምታ ይገባል፡፡ እንደዚሁም ለኔ ለአገልጋይሽ የክብር ጌጥ ወይም ሽልማት ሆኖኝ ይኖር ዘንድ የልዩ ችሮታሽን የነጭ ሐር ልብስ አጎናጽፊኝ ፡፡
ይልቁንም በሥጋ በነፍስ ጥበቃሽ አይለየኝ፡፡

ሰላም ለጊዮርጊስ ተውላጠ ፃማሁ ወሕማሙ።
እንተ ተለዓለ ሞገሰ ስሙ፡፡
በፍልሰትኪ ድንግል(ዮም) ተቶስሐ ፍልሰተ ዓጽሙ።
እንዘ ይብል ሶበ ጸለየ አሜሃ ቀዲሙ።
ምስለ ፍልሰትኪ ደምርኒ እሙ፡፡

ስብሐት ለኪ ማርያም ለአብ መርዓቱ፡
ስብሐት ለኪ ማርያም ለወልድ ወላዲቱ፡፡
ስብሐት ለኪ ማርያም ለመንፈስ ቅዱስ ታቦቱ፡፡
ወርቅሰ ወብሩር ኃላፊ ውእቱ
እምወርቅ ወእብሩር ኪያኪ እፈቱ፡፡

አሜን ‼

ነሐሴ ሦስት ስድሳ ክንድ የሆነ የድንጋይ ምሰሶ ላይ ወጥተው በዚያም ሳይቀመጡ ቆመው እያስተማሩና እየጸለዩ 42 ዓመት የኖሩት ሶርያዊው አቡነ ስምዖን ዘዓምድ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ዳግመኛም በዚኽ...
08/08/2026

ነሐሴ ሦስት ስድሳ ክንድ የሆነ የድንጋይ ምሰሶ ላይ ወጥተው በዚያም ሳይቀመጡ ቆመው እያስተማሩና እየጸለዩ 42 ዓመት የኖሩት ሶርያዊው አቡነ ስምዖን ዘዓምድ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ወደ ሮም በመሄድ በከሃዲው ንጉሥ በእንድርያኖስ ፊት የጌታችንን አምላክነት መስክረው የሰማዕትነት አክሊልን የተቀዳጁት ቅድስት ሶፍያና ሦስቱ ሴት ደናግል ልጆቿ ዕረፍታቸው ነው።

ቅድስት ሶፍያ ቡርክት

ይህች ቅድስት እናት ኢጣሊያዊት (የአሁኗ ጣልያን አካባቢ) ስትሆን የነበረችው በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ ነው።

ትውልዷ የነገሥታቱ ዘር ውስጥ እንደ መቆጠሩ እጅግ የተከበረች ሴት ነበረች፤ ምንም ሥጋዊ ክብሯ እንዲህ ከፍ ያለ ቢሆንም መንፈሳዊነቷ የሚደነቅ ነበር።

ከነገሥታቱ ዘር ካገባችው ባሏም ሦስት ሴቶች ልጆችን አፍርታለች፤ በሃይማኖት ምክንያት መከራ ሲመጣ ስለ ልጆቿ ስትል ሃገሯን ጥላ ተሰደደች፤ ስለ ክርስትናም በባዕድ ሃገር መጻተኛ ሆነች። ያም ሆኖ ክፉዎቹ እግር በእግር ተከትለው ደረሱባት።

ቅድስት ሶፍያ ከዚህ በላይ መሸሸትን አልፈለገችም፤ ከልጅነታቸው ለተባረኩ ልጆቿ ገድላተ ሰማዕታትን ታስጠናቸው ነበርና አሁን የነገር መከናወኛ ደርሷል፤ ልጆቿን ቁጭ አድርጋ አዋየቻቸው።

"ልጆቼ ክርስቶስን የወደደ ክብሩ በሰማይ እንጂ በምድር አይደለም፤ ገድላቸውን ያነበባችሁትን ቅዱሳት አንስትን አስቡ" አለቻቸው፤ ሦስቱ ሕፃናትም "እናታችን አትጨነቂ።

እኛ ለአምላክ ፍቅር ተገዝተናል፤ ስለ ስሙም ደምን ልንከፍል ቆርጠናል፤ ብቻ የእርሱ ቸርነት ያንቺም ምርቃን አይለየን እንጂ" አሏት።

ቅድስት ሶፍያ በሰማችው ነገር እጅግ ደስ አላት፤ ከዚያ ጉዞ ወደ ምስክርነት አደባባይ አደረጉ፤ ቅድስቷ እናት ሦስቱንም ሕፃናት በመኮንኑ ፊት አቀረበች።

አንድ በአንድ ጠየቃቸው፤ ሁሉም ግን መልሳቸው የተጠናና ተመሳሳይ ሆነበት፤ "እኛ የክርስቶስ ነን" ነበር ያሉት፤ መኮንኑ በቁጣ ሦስቱንም እያከታተለ አስገደላቸው።

ቅድስት እናት ሶፍያ በእንባ እየታጠበች ልጆቿን በየተራ ቀበረች፤ ስለ ሃይማኖቷ ክብሯን ሃገሯን ሃብቷን መንግስቷን ሰጠች፤ ከምንም በላይ ግን ልጆቿን ሰጠች።

ከዚህ በኋላ ግን በመጨረሻው ወደ ልጆቿ መቃብር ሒዳ በእንባ ለመነች፤ "ልጆቼን አይ ዘንድ ናፍቄአለሁና ጌታ ሆይ ውሰደኝ" አለች።

ከደቂቃዎች በኋላም እዚያው ላይ ዐረፈች፤ የአካባቢው ሰዎች ደርሰው እርሷንም ከልጆቿ ጋር ቀበሯት።
መድኃኔዓለም ከታላቁ አባ ስምዖንና ከቅዱሳት አንስት በረከትን ረድኤት ያድለን፤ ትዕግስታቸውንም ያሳድርብን

አርኬ
ሰላም ለሶፍያ እንተ አንደየት ርእሳ ።መንግሥተ ሰማያት አብዲራ እምነ ምድራዊት ንግሣ። ተዝካረ ደቂቃ ሠላስ ወአኮ ሠላሳ። ከመ ገብረት ዮም ከመ ትፈጽም ማኀሠሣ። እግዚአብሔር ተመጠወ ነፍሳ።

አቡነ ስምዖን ዘዓምድ ሶርያዊ

ስምዖን ዘዓምድ የሚባሉ ሌላኛው የአንጾኪያው ታላቅ አባት አሉ፤ እኚህ ግን የሶርያው ስምዖን ዘዓምድ ናቸው።

በልጅነታቸው በግ ሲጠብቁ ቢያድጉም ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ወደ ቤተ እግዚአብሔር እየሄዱ መጻሕፍትን ይሰሙ ነበር፤ በሚሰሙት ቃልም ገዳማዊ ሕይወትን በልባቸው አሰቡና ወደ አንዲት ገዳም ገብተው ከበሩ ወደቁ፡፡

መነኮሳቱም ይህን ብላቴና ወደ ውስጥ እናስገባው ብለው አስገብተው ተላላኪ አገልጋይ አደረጓቸው፤ በታላቅ ተጋድሎ ሆነው መነኮሳቱንም እያገለገሉ ኖሩ፤ እህል የሚቀምሱት ሰንበትን ብቻ እየጠበቁ ነበር፡፡

ሰውነታቸውን እጅግ ከመጉዳታቸው የተነሣ ሊጎበኟቸው የሚመጡት ቅዱሳን የሞቱ ይመስላቸው ነበር፡፡

የክርስቶስን መታሰርና መቸንከር አስበው ሰውነታቸውን በቀጭን ገመድ አጠላልፈው በኃይል አጥብቀው ስላሰሩት ገመዱ የሰውነታቸውን ሥጋ እየቆራረጠ ጣለው፡፡

ከቁስሉ የሚወጣው ደምና መግልም እየሸተተ ቢያስቸግራቸው የገዳሙ መነኮሳት ‹‹ሸተተን ከረፋን›› ብለው ለአበምኔቱ ከሰሷቸውና ከገዳሙ እንዲባረሩ አደረጓቸው፡፡

አባታችን ስምዖን ዘዓምድም በዚህ በመነኮሳቱ ድርጊት ሳይከፉና ሳያዝኑ እግዚአብሔር ያዘጋጀላቸውን ቦታ በጸሎት ጠይቀው እባቦችና ጊንጦች ያሉበት ጉድጓድ ውስጥ ሄደው ገቡ፤ እባቦችና ጊንጦችም ምንም ሳይነኳቸው ከእነርሱ ጋር አብረው እየኖሩ በምስጋና ሕይወታቸው መኖር ጀመሩ፡፡

እግዚአብሔርም ለገዳሙ አበምኔት በራእይ ተገልጦ ስምዖን ወዳጄን ወዴት አደረስከው፤ በፍርድ ቀን እርሱ ከአንተ ይሻላል ስላለው አበምኔቱ እጅግ ደንግጦ ለመነኮሳቱ ነገራቸውና ተጨነቁ አዘኑ፤ ከብዙ ፍለጋ በኋላ በጉድጓዱ ውስጥ እባቦችና ጊንጦች ከበዋቸው አገኟቸው፡፡

በድለንሃል ይቅር በለን ብለው ከእግራቸው ሥር ቢወድቁ እርሳቸው ግን በፍጹም ትሕትና ሆነው ‹‹እኔ ነኝ ያሳዘንኳችሁ እናንተ ይቅር በሉኝ›› አሏቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ይዘዋቸው ወደ ገዳም ተመለሱ፤ መልአክ ተገልጦላቸው ተልእኮአቸውን ቢነግራቸው ቁመቱ ስልሳ ክንድ የሆነ የድንጋይ ምሰሶ ላይ ወጥተው በዚያ ሆነው ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረጉ፣ ሕሙማንን እየፈወሱ፣ ወንጌልን ሳይቀመጡ ቆመው እያስተማሩ 12 ዓመት ኖሩ፡፡

ስምዖን ዘዓምድ የተባሉትም በዚህ ምክንያት ነው፤ ዝናቸውን የሰሙ ሕዝቦች ሁሉ ወደ እርሳቸው እየሄዱ በትምህርታቸውና በተአምራታቸው እየተገረሙ ይመጡ ነበር፤ ብዙ ኢአማንያንን እያስተማሩ ያጠምቋቸው ነበር፡፡

ከዚህም በኋላ ወደ አንድ ሌላ ምሰሶ ተዛውረው 30 ዓመት እንደ ቀድሞው እያገለገሉ ኖረው ነሐሴ 3 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡

ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፤ በጸሎታቸው ይማረን

አርኬ
ሰላም ለስምዖን እንተ ለሐቌሁ አጽንዖ። በኀብለ በቀልት ይቡስ ዘይገምዶ ወይብልዖ። በእንተ ዝንቱ እምደብር ሶበ አበ ምኔት አውጽኦ። በቃለ ተግሣጽ እግዚአብሔር አውሥኦ። ለገብርየ ስምዖን እንዘ ይብል አግብኦ።

(ስንክሳር ዘወረኀ ነሐሴ 3)

🗓 የነሐሴ 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1.ታላቁ አባ ስምዖን ዘዓምድ
2.ቅድስት ሶፍያ ቡርክትና ደናግል ልጆቿ

🗓ወርሐዊ በዓላት

1.በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው (ዘካርያስና ስምዖን)
4.አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
5.አቡነ ዜና ማርቆስ
6.አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል
7.ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ (ዓምደ ሃይማኖት)

የነሐሴ 3 ቀን የእለቱ ግጻዌ

መልእታት
👇

1ቆሮ 8÷1-ፍጻ

1ጴጥ 4 ÷1-6

ሐዋርያት 26፥ 1-29

ምስባክ 👇

"እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ። ውብእሲ ተወልደ በውስቴታ።ወዉእቱ ልዑል ሣረራ። መዝ 86÷5

ትርጉም➣"ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።"መዝ 86÷5

የእለቱ ወንጌል📖
👇
ማቴዎስ 12÷38-ፍጻ

የሚቀደሰው ቅዳሴ
👇
ቅዳሴ ዘእግዝእትነ ነው።

የነሐሴ 3 ቀን ወንጌል ሙሉ ንባብ📖

ማቴዎስ 12

38 በዚያን ጊዜ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን አንዳንዶቹ መለሱና። መምህር ሆይ፥ ከአንተ ምልክት እንድናይ እንወዳለን አሉ።
39 እርሱ ግን መልሶ እንዲህ አላቸው። ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም።
40 ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል።
41 የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፥ እነሆም፥ ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።
42 ንግሥተ ዓዜብ በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና፥ እነሆም፥ ከሰሎሞን የሚበልጥ ከዚህ አለ።
43 ርኩስ መንፈስ ግን ከሰው በወጣ ጊዜ፥ ዕረፍት እየፈለገ ውኃ በሌለበት ቦታ ያልፋል፥ አያገኝምም።
44 በዚያን ጊዜም። ወደ ወጣሁበት ቤቴ እመለሳለሁ ይላል፤ ቢመጣም ባዶ ሆኖ ተጠርጎና አጊጦ ያገኘዋል።
45 ከዚያ ወዲያ ይሄድና ከእርሱ የከፉትን ሰባት ሌሎችን አጋንንት ከእርሱ ጋር ይወስዳል፥ ገብተውም በዚያ ይኖራሉ፤ ለዚያም ሰው ከፊተኛው ይልቅ የኋለኛው ይብስበታል። ለዚህ ክፉ ትውልድ ደግሞ እንዲሁ ይሆንበታል።
46 ገናም ለሕዝቡ ሲናገር፥ እነሆ፥ እናቱና ወንድሞቹ ሊነጋገሩት ፈልገው በውጭ ቆመው ነበር።
47 አንዱም። እነሆ፥ እናትህና ወንድሞችህ ሊነጋገሩህ ፈልገው በውጭ ቆመዋል አለው።
48 እርሱ ግን ለነገረው መልሶ። እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነማን ናቸው? አለው።
49 እጁንም ወደ ደቀ መዛሙርቱ ዘርግቶ። እነሆ እናቴና ወንድሞቼ፤
50 በሰማያት ያለውን የአባቴን ነውና ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነውና አለ።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ 2 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share