የዳግም ምጽአት ዝግጅት በ ባሕታዊ ገ/ሚካኤል /ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የዳግም ምጽአት ዝግጅት በ ባሕታዊ ገ/ሚካኤል /ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻

የዳግም ምጽአት ዝግጅት በ ባሕታዊ ገ/ሚካኤል /ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻ የምጽአት ዝግጅት ! ማቴ ፳፬ ፥ ፵፬።
/የምጽአት ገዳም ማስፈፊያ እና የበዓሉ ማስከበሪያ ዓለም አቀፍ ተቋም:: ማኅበሪቱ በቴሌግራም

ስለ ጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን መንፈሳዊ ጉዞ እና ስለሚያስፈጽሙት የዳግም ምጽአት ዝግጅት ሂደት ለጠየቃችሁ እና ወደፊትም ለምትጠይቁ ምእመናን ከአክብሮት ጋር የቀረበ የማብራሪያ...
19/09/2020

ስለ ጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን
መንፈሳዊ ጉዞ እና ስለሚያስፈጽሙት
የዳግም ምጽአት ዝግጅት ሂደት ለጠየቃችሁ እና ወደፊትም ለምትጠይቁ ምእመናን
ከአክብሮት ጋር የቀረበ የማብራሪያ መልስ :-

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ።

ጌታችን ና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት በተናገረው መልእክት "ተዘጋጅታችኹ ኑሩ (ጠብቁ) ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።" (ማቴ ፳፬÷፵፬) ብሏልና፣ የ አባታችን አገልግሎት ይህን መልእክት መሰረት ያደረገ ነው።

በማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻ አባላት ተሳትፎ እና በጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገ/ሚካኤል ሰብሳቢነት እየተካሄደ ያለው የዳግም ምጽአት ዝግጅት " በጥምቀት በንስሐ እና በቅዱስ ቁርባን ተቀድሰን እንዲሁም የምጽአት በዓልን በድምቀት እያከበርን እንጠብቀው ቀኑን አናውቅምና፣ እንዲሁም ለበዓሉ ማስከበሪያና መታሰቢያ ታላቅ ደብር እንሥራለት " የሚል ነው ።

የዝግጅቱ አስፈጻሚ ጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገ/ሚካኤል ተገን እምነቴን በገንዘብ አልቀይርም በማለት ና ተልእኮዬን ሳላውቀው ሀብት አይምጣብኝ ብለው በመጸለይ እና ለዘመናት በእውነተኛዋ መንገድ ጸንቶ በመቆየትና ለመንፈሳዊው ተልእኳቸው የሚያስፈልጉ ሥራዎችን በመሥራት እና በመዘጋጀት ለዘመናት ሲደክሙና ሲወጡ ሲወርዱ የቆዩና እግዚአብሔር የፈቀደው ጊዜ ሲደርስ ታላቅ መንፈሳዊ ተልእኳቸውን ይዘው ብቅ ያሉ አባት ናቸው ።

የተሰጣቸው ተልእኮ እና ዓላማ :-
፩) እንደ ጌታችን ልደት ጥምቀትና ትንሣኤው እንዲሁም እንደ መስቀል በዓሉ ታላቅ በዓል ፤ የጌታ መገለጥ የሆነ ነውና እንዲሁም ታላቅ ሥራ የሚሠራበት ፣ ስንዴውን ከገለባው የሚለይበት ፣ እንክርዳዱን የሚያበጥርበት፤ ዕለት የሆነውን ዳግም ምጽአትን ከላይ እንደተጠቀሱት ዐቢይ በዓላት በድምቀት ማስከበር ነው ።
ይህም ሲባል መጋቢት ፳፱ የሚከበረውን ደብረ ዘይትን የዳግም ምጽአት በዓል
በዓዋጅ በዓለም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ
በበለጠ ድምቀት እናክብረው ለማለት ነው እንጂ ሌላ አዲስ በዓል እየፈጠሩ እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል ።

፪) ለበዓሉ ማስከበሪያና መታሰቢያ የሚሆን እና እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ታላቅና ታሪካዊ የሚሆን በከበረ ድንጋይ የሚሠራ በአንድ ዙሪያ ባለ ዓሥራ ሦስት ቤተ መቅደስ ያለው ቤተክርስቲያን ለማሠራት የታዘዙና የተነሡ አባት ናቸው ።
(አንዱ ና ዋናው መሐል ላይ የሚሆነው ለጌታችንና ለእመቤታችን ሲሆን በዙሪያው የሚሠሩት ዓሥራ ሁለቱ ደግሞ ለዓሥራ ሁለቱ ሐዋርያት የሚሆኑ ናቸው።)

ማሳሰቢያ :-
የጌታችን የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መምጫን ቀን አውቃለሁ አላሉም "ቀኑን አናውቅምና ተዘጋጅተን እንጠብቅ" ነው የሚለው መልእክታቸው ።

፪) የኢየሱስ መንገድ ጠራጊ ነኝ አላሉም ይልቁንም " የዳግም ምጽአት መንገድ ጠራጊ ነኝ ነው ያሉት" ምክንያቱም የተጠሩበት አገልግሎት ምጽአት የለም / አይደርስብንም በሚል ስሜት የተዘናጋውን ወገን በዳግም ምጽአት ላይ ይበልጥ ትኩረት በማድረግ መጽሐፍ ቅዱስንና የቅዱሳን አበውን ትምህርት መሠረት በማድረግ ማስተማርና ማዘጋጀት ነው ።
በእውነቱ የዚህን ታላቅ ሥራ መልእክት ላልደረሰው በማዳረስ ታሪካዊና መንፈሳዊ አስተዋፅኦ ልናደርግና የበረከቱ ተካፋይም ልንሆን ይገባል !

ባሕታዊ ገ/ሚካኤል ትሑትና ቡሩክ በሄዱበት ቦታ ሁሉ ማለት ይቻላል ቤተ ክርስቲያን የሚተክሉ አባት ሲሆኑ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ እንዲሁም በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገሮችሁሉ በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ተክለዋል አስተክለዋል ። ጠበል በማጥመቅና እየሰየሙ በማንገሥም ታላላቅ አገልግሎትና አስተዋጽዖ በመስጠት ላይ የሚገኙ ናቸው ።

አባታችንን ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ ይህን ዓላማ ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበረ ሲሆን፣ በ 1974 ዓ / ም ጀምረው በልጅነት እድሜአቸው የፈውስ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት እሳቸውን የሚያውቁ ወላጆቻችን እና አንዳንድ አባቶች እንደ ነገሩን ከዚያን ዘመን ጀምሮ የምጽአቱን ዝግጅት እንዲያስፈጽሙ በበቁ ስውራን አባቶች አማካኝነት እንደተነገራቸውና ይህን በምንም የግል ጥቅም ሳይለውጡ ጸንተው እንደኖሩ ተገንዝበናል። እናም ሙሉ ሕይወታቸውን ለዚህ ዓላማ የሰጡ እንደሆኑና ትክክለኛ ታላቅ ቁም ነገሮች የያዙ ፣ ጊዜና ፈቃደ አምላክ የሚጠብቁ በትእግሥት ያሉ እንዲሁም በዓላማ ጽናት ተስፋ ሳይቆርጡ እመቤታችንን በሱባኤና በጸሎት እየተማፀኑ ፈቃደ እግዚአብሔርን የሚጠይቁ መሆናቸውንና ጊዜውም ገና መሆኑን አውቀው ለሠላሳ አምስት ዓመታት ገደማ ይህንኑ ዓላማ ይዘው በጸሎትና በዝግጅት ጸንተው ኖረዋል ።

ቀጥሎም ፈቃደ እግዚአብሔር መድረሱን የሚናገሩ መልእክቶች ና ምልክቶች ሲደርሳቸው በ ፪ሺ፯ /2007 አ.ም መልእክቱን ና ዝግጅቱን ለ ምእመናን ይፋ አድርገዋል። በአሁን ወቅት በርካታ የዝግጅቱ ሂደቶች እየተካሄዱ ነው።

ይህ ሁሉ ውዳሴ ከንቱ ሳይሆን የዓላማውን ምንነትና የአስፈጻሚውን አገልግሎት ና ተልእኮ በተመለከተ የተሰጠ መረጃና ምሥክርነት ነው።

(ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻)

ከ ጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገ/ሚካኤል ተገን:-       በዘመኑ በተገኘው የጥበብ መሣሪያ አግልግሎቶች ፦ ዓለም አቀፍ መንፈሳዊ መልእክት እና ሰማያዊ ዝግጅት !!!በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅ...
12/08/2020

ከ ጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገ/ሚካኤል ተገን:-

በዘመኑ በተገኘው የጥበብ መሣሪያ አግልግሎቶች ፦ ዓለም አቀፍ መንፈሳዊ መልእክት እና ሰማያዊ ዝግጅት !!!

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ከሐዱ አምላክ አሜን
የተከበራችሁ የሰው ነገድ በሙሉ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን እያልኩ ፦ መጀመሪያ ለሁላችን ፈጣሪ ምስጋና እናቅርብ ፦ ዓለማትን የፈጠረ አምላክ እንኳን ኖረ !!! አሜን ። እኛንም እንኳን ፈጠረን አሜን ።

መግለጫ:- በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተገለጸው መጀመሪያ ሕያው እግዚአብሔር ዓለማትን ሁሉ ፈጥሮ ሰውን ግን በአርአያውና በመልኩ ከፈጠረው በኋላ ብዙ ተባዙ ፣ ውለዱ ተዋለዱ ፣ጨምድርን ምሏት ፣ ከሰማይ በታች ፣ ከምድር በላይ ያለውን ሁሉ ግዙ ንዱ ፣ ብሉ ጠጡ ፣ ቢልም ፦ የሚበሉ እና የማይበሉትን ፣ ለዪቶ አስተምሯል ። ዘፍ ፪ ÷ ፲፮ - ፲፯ ። ዘሌዋ ፲፩ እና ፲፪ን እንመልከት ። ስለ ሕግጋቶቹም ዘጸ ፳ ፥ ፩ -፲፯ ማቴ ፭ ፥ ፩ - ፍጻሜ ። ተጽፈው ይገኛሉ ። ስለ ሁለቱ ዓለማትና ሕገ እግዚአብሔር የሕይወታችን መመሪያ በሙሉ ደግሞ በሕገ ልቡና ፣ በሕገ ኦሪት ፣ በሕገ ወንጌል ፣ በሥርዓተ ሊቃውንት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተጽፎ ! ተተርጉሞ ፣ ተዘጋጅቶ እና ታትሞ ይገኛል ።

ማብራሪያ ፦ ስለዚህ በሕጉና በሥርዓቱ ፣ በፈቃዱ እና በትእዛዙ ጸንተን እንገኝ እንላለን ። መንፈሳዊ ዓዋጅ ፦ ዘመኑ የዝግጅት ነውና ወደ ሰማያዊ ዝግጅታችን እንቀጥላለን ፦ በማቴ ፳፬ ፥ ፵፪ - ፵፬ ። ተብራርቶ እንደምናገኘው እንግዲህ ጌታችሁ በምን ሰዓት እንደ ሚመጣ አታውቁም እና ተዘጋጅታችሁ ኑሩ ጠብቁ የተባልነውን ለማስፈጸም በቸርነቱ ብዛት በዚህች መጨረሻ ዘመን ተደለዉ ወተጋብኡ እያልን በዳግም ምጽአቱ ስም ከነ ዓላማችን እነሆኝ እያልን ቆመን እንገኛለንና በዚህ መልእክት ማስተላለፊያ አግልግሎት እየገባችሁ ከበረከቱ ትካፈሉና ከሥራው ትሣተፉ ዘንድ የተለያዩ የማኅበራዊ ገጽ አድራሻዎችን እነሆ በክብርና በማመን ማኅበሪቱ ትገልጽላችሗለች።

ዋናው መልእክት የዳግም ምጽአቱን መታሰቢያ በዓል እንደ ጥምቀትና መስቀል በመላው ዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወገዳማት " በዓለ መርዓ " በሚል ስያሜና ርእስ በከፍተኛ ድምቀት ለማስከበር ነው ። ከእመቤታችንም የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለችባትን በየካቲት ፲፮ ቀን ሁሉ ጊዜ በየዓመቱ እንዲሁ በዓለም ከቀፍ ፣ በነፍስ ወከፍ በዓዋጅ በዓልነት አሳውጆ ለማስከበር ነው ። በመቀጠልም የበዓሉ ማስከበሪያ ባለ ፲፫ ቤተ መቅደስ የሆነ ታሪካዊ ሥነ ሕንጻ በከበረ ድንጋይ ደብሩን ለማሠራት ነው ።

የዚህ ፍጹም ሀብተ ጸጋ ባለቤት የታደለችው ባለ ቃል ኪዳን አገራችን ብሔረ አግአዚት ኢትዮጵያ ናትና በአንዲቱ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት እምነት ያላችሁና የጸናችሁ ወገኖቻችንና ወዳጆቻችን ሁሉ በቋሚ አባልነትና በተለያዬ የአግልግሎት ድጋፍ ለምትሰጡ ሁሉ የሥራው ሁሉ አስፈጻሚና የአባላቶቹ ሁሉ ዋና ሰብሳቢ እና መሪ የሆነች ዘለዓለማዊት ማኅበር " ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻ " በተሰኘችው ማኅበራዊችን እየገባሁ በራሳችሁ ፈቃድና በግል ፍላጎታችሁ በነፃነት ዓላማውን በመውደድ ሊንክ እያላችሁ ትመዘገቡ ዘንድ ዝግጅታችንን እና ሙሉ አድራሻችንን ስንገልጽ የተጠራችሁትንና የተመረጣችሁትን እንዲሁም የተፈቀደላችሁን አሰባስቦ አብረን እናበርክት ዘንድ የዘወትር ጸሎታችን ነው ። ለቁም ነገር ብቻ ጻፉልን ደውሉልን ለበለጠ መተማመኛ በሱባኤ ጸሎት በመታገዝ አረጋግጦ መረዳት ነው ።

ታዛዥ አገልጋያችሁ የምጽአት መንገድ ጠራጊ ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን እባላለሁ ። ባለችኝ ዕውቀትና በተሰጠኝ ሀብተ ጸጋ ወደፊትም በሚሰጠኝ ሀብተ ጸጋ ሁሉ ከተዋሕዶ ሃይማኖት ጋር ይህን ዝግጅትና ዓላማ በመላው ዓለም ለማስፋፋት ከአምላኬና እመቤቴ ጋር ቃል ገብቻለሁ።

ከልጅነት ዘመኔ ጀምሮ "ካሁን በፊት ያልተፈጸመ ፣ ወደፊት እንደ ነቢያት ትንቢት የሚፈጸም ፣ ይህን የመጨረሻ ዘመን ትውልድ ወደ አንተ የሚመልስ ፣ የጽድቅ አሸናፊነት የሚያሰጥ ሀብተ ጸጋ ስጠኝ ፣ ሚሥጢር ግለጽልኝ ፣ በእኔና በዓላማዬ ላይ አድረህ አንተ ሥራ ! አንተ ምራ ! እመቤቴ ማርያም አንቺ ምሪኝ አንቺ አስፈጽሚኝ ዓለም አቀፍ ፣ ነፍስ ወከፍ የሆነ ሥራ ስጡኝ" እያልኩ እናትና ልጇን እየተማፀንኩ በማደግ እና የተሰጠኝ ምላሽ እና ተልእኮ ነው።
_____________________________________________
___________________________________
_________________________

ከማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻ :-

የዚሕ ታላቅ ዝግጅት ና ማኅበር አባል መሆን ለምትፈልጉ ምእመናን በሙሉ!

የምጽአት ዝግጅቱ አስፈፃሚ ፣ የታላቁ ና ታሪካዊ የሚሆነው የምጽአት መታሰቢያ ቤተመቅደሱ አሠሪ እና እንዲሁም የምፅአት በአል አስከባሪ ማኅበር ና ዋና ተቋም የሆነችው " ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻" አባል መሆን የምትፈልጉ ምእመናን ከታች በተቀመጠላችሁ የቴሌግራም ገፅ አድራሻዎች ተጠቅማችሁ በቀላሉ ወደ ማኅበሪቱ በመግባት የታላቁ ዝግጅት አባል በመሆንና በመሳተፍ ለዝግጅቱ አስተዋፅኦ ማድረግ ና የበረከቱ ተካፋይ መሆን የምትችሉ መሆኑን በ ትህትናና በደስታ እንገልፃለን።

የአባታችን መልእክት የሚተላለፍበት የማኅበሪቱ ቻናል ወይም ጣቢያ በቴሌግራም



የባሕታዊ ገብረ ሚካኤል የስልክ ቁጥር:-
+251 9 11 74 35 83

የ ዩትዩብ ቻናል:-
https://m.youtube.com/channel/UCTwCHSH1sTdLzwhZLLGk3HA?view_as=subscriber

የ ፌስቡክ ገፅ
page:
Page-https://www.facebook.com/698917243558437

Telegram group: t.me/dagimmisatgroup Telegram channel: t.me/dagimmisatchannel page: Page-https://www.facebook.com/698917243558437 የምጽአት መታሰቢያ ገዳም ማስ...

ተዘጋጅተን እንጠብቅ ቁጥር ፫ የዚሕ ታላቅ ዝግጅት ና ማኅበር አባል መሆን ለምትፈልጉ ምእመናን በሙሉ! የምጽአት ዝግጅቱ አስፈፃሚ ፣ የታላቁ ና ታሪካዊ የሚሆነው የምጽአት መታሰቢያ ቤተመቅደሱ...
07/08/2020

ተዘጋጅተን እንጠብቅ ቁጥር ፫
የዚሕ ታላቅ ዝግጅት ና ማኅበር አባል መሆን ለምትፈልጉ ምእመናን በሙሉ!

የምጽአት ዝግጅቱ አስፈፃሚ ፣ የታላቁ ና ታሪካዊ የሚሆነው የምጽአት መታሰቢያ ቤተመቅደሱ አሠሪ እና እንዲሁም የምፅአት በአል አስከባሪ ማኅበር ና ዋና ተቋም የሆነችው " ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻" አባል መሆን የምትፈልጉ ምእመናን ከታች በተቀመጠላችሁ የቴሌግራም ገፅ አድራሻዎች ተጠቅማችሁ
በቀላሉ ወደ ማኅበሪቱ በመግባት የታላቁ ዝግጅት አባል መሆንና በ አገልግሎት መሳተፍ ና በልዩ ልዩ መልኩ ለዝግጅቱ አስተዋፅኦ ማድረግ ና የበረከቱ ተካፋይ መሆን የምትችሉ መሆኑን በ ትህትና ና በደስታ እንገልፃለን። በ ቴሌግራም የማያመቻችሁ ምእመናን በአባታችን የቀጥታ ስልክ ቁጥራቸው በመደወል ማነጋገር የሚቻል መሆኑንም ልንገልፅ እንወዳለን።

የአባታችን መልእክት የሚተላለፍበት የማኅበሪቱ ቻናል ወይም ጣቢያ በቴሌግራም



የጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል
የ ስልክ ቁጥር +251 9 11 74 35 83

የ ዩትዩብ ቻናል
https://m.youtube.com/channel/UCTwCHSH1sTdLzwhZLLGk3HA?view_as=subscriber

የ ፌስቡክ ገፅ
page:
Page-https://www.facebook.com/698917243558437

ከ ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻።

(መስራች ና ዋና ሰብሳቢ:- ጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን)

06/08/2020

ተዘጋጅተን እንጠብቅ! ክፍል ፪

" ኢትዮጵያ የገነት በርና የመንግሥተ ሰማያት መሸጋገሪያ ናት " ምክንያቱና ምልክቱም ከነማስረጃው የአበው ኪዳን ፣ የብሉይ ኪዳን ፣ የአዲስ ኪዳን ፣ የሊቃውንት ሥርዓት ፣ የዳግም ምጽአት ሰማያዊ ዝግጅት በክብር ይዛ ትገኛለች ። የኤዶም ገነት ማየ ግዮን ዓባይና ጣና ወንዝ አፍላገ ገነት ፣ የኖኅ ቀስተ ደመና የምሕረት ቃል ኪዳን ምልክት ፣ / ሰንደቅ ዓላማችን ፣ የሙሴ ጽላት ታቦተ ጽዮን ፣ የቅዱስ ያሬድ ማኅሌታይ ሰማያዊ ዜማ ፣ የሃይማኖት አግልግሎት መስጫ ግእዝ ልሳን ፣ የመንግሥት እና የሥራ ማስተዳደሪያ ፦ የዓለም ሕዝብ መግባቢያ ብሔራዊ ቋንቋ አማርኛ ፣ ጌታችን ዕፀ ቅዱስ መስቀል ፣ የእኛም የደኅናው ዘመን ማብሠሪያና የዳግም ምጽአት በዓል ማወጃ በተፈጥሮ አበባ የቀስተ ደመና ዕንቁጣጣሽ ዓርማ ከትእምርተ ምጽአት ጋር ። በቃል ኪዳን ባለሟልነት ይዛ የምትገኝ ሀገረ እግዚአብሔር ፣ ርስተ ማርያም ፣ የቅዱሳን መናኻሪያ ፣ የነገሥታት መዲና ፣ የክርስቲያን ደሴት ፣ ከዓለም ተለዪታ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ሁልጊዜ ዘርግታ ፣ ከሥነ ፍጥረት እስከ ዳግም ምጽአት ባለሟልነቷን አጽንታ የምትገኝ ታላቅ አገር ናት ። ስለዚህ የሀገር ፍቅር ፣ የወገን ክብር ፣ የሃይማኖት ጽንዓት ፣ የታሪካዊ ሥራ ፍላጎት ያላችሁ ሁሉ መሰሎቼ !!! ወደ ፍሬ ጉዳዩ እናምራና ስለ ኢትዮጵያ ትንሣኤ ፣ ስለ ዓለም ሰላም ፣ ስለ አንዲት እምነት ስምምነትና የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት መስፋፋት ፣ ስለ ፍጡራን ሁሉ ስምምነት ፣ ስለ ዘውድ ክብር ፣ ስለ ሰንደቅ ዓላማ ቀስተ ደመና ቃልኪዳን ፣ ስለ ሰማያዊ ቋንቋ ግእዝ ልሳን ፣ መንፈሳዊ ብቃት ዕድገት ፣ ስለ ሰማያዊ ዝግጅት ማስፈጸሚያ ዘለዓለማዊት ማኅበር አመራርና የጽድቅ ሰብሳቢነት ፍላጎት ያላችሁ ከጎናችን ቁሙ !!! የበረከቱ ተካፋይ ፣ የሥራው ተሣታፊ ሁኑ ። ማስገንዘቢያ የግል አትራፊ ድርጅት ያልሆነ የዓለም አቀፍ ዓላማ ፣ የተዋሕዶ ሃይማኖታዊ አቋም ፣ የደኅናው ዘመነ ፍስሐ ወኃሤት ማብሠሪያ ፣ የሰማያዊ ዝግጅት ማስፈጸሚያ ፣ ነው ። በማንኛውም ምክንያት የማገኘው ገቢ የልማት ምንጭ ሁሉ ለዚሁ የተቀደሰ ዓላማ የሚውል ነው ።

" የዳግም ምጽአት ዝግጅት " የሰማያዊ ዝግጅት ጥሪና መንፈሳዊ ዓዋጅ ዓለም አቀፍ መልእክት ፦ በጥያቄና መልስ እናቀርበዋለን ። ሰማያዊ ዝግጅት ማለት ምንድን ነው ? " መልስ ፦ ሰማያዊ ዝግጅት ማለት መጀመሪያ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በአንድ አምላክ ወልድ ዋሕድ ብሎ አምኖ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት እምነት መመሪያ ፣ በሊቃውንት ሥርዓት መጠመቅ ነው ። ስለዚህ ያልተጠመቁ አሕዛብን እናስጠምቅ ። ሁለተኛ ሕጉንና ሥርዐቱን ጠብቆ መቁረብ ሥጋወደሙን መቀበል ነው ። ያልቆረብን እንቁረብ ። ሦስተኛ ንስሐ መግባት ነው ። ኃጢአት የሌለበት አይገደድም ። በንስሐ ከፀዱ በኋላ ተመልሶ ኃጢአት መሥራት መሳሳት አይገባም ። መጨረሻም ቀና ሃይማኖት መማር ፣ በጎ ምግባር መሥራት ፣ ልዩ ልዩ ትሩፋተ ጽድቅ ማብዛት ነው ። እንዲሁም የዳግም ምጽአቱን መታሰቢያ በዓል ማክበርና ደብሩን መሥራትና ማሠራት ፣ የእመቤታችንን ቃል ኪዳን መዘከርና ማዘከር የመሳሰሉ እምነትና ምግባርን አስተባብሮ ይዞ መገኘት ፤ በተግባርም መግለጽ የመልካም ነገር አርአያ መሆን ነው ። ታላቋ አገራችን ኢትዮጵያ የቃል ኪዳን ቅርሳቅርሶችንና ንዋየ ቅድሳቶችን ፣ ታሪካዊ ቦታዎችን ፣ አስደናቂ ሥፍራዎችንና ሕንጻዎችን ይዛ ስትገኝ ፦ ፍጽምት የሆነች ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖትም የጽድቅ አስተማሪ እና መሪ በመሆን እበየዘመኑ የሚፈጸመውን ክሥተት ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት እየተነበየችና እየሰበከች ፣ በማወጅ ቀና ሃይማኖት ተማሩ ፣ በጎ ምግባር ሥሩ ፣ ትሩፋት ጨምሩ ፣ በማለት ሁልጊዜ ታስተምራለችና በመመሪያዋ እንመራ ። ሌሎቹንም ከክሕደትና ከኃጢአት ወደ እምነትና ወደ ጽድቅ እንመልሳቸው ። ከሐሰትም ወደ እውነት ፣ እንሳባቸው ። ከመበተን ወደ አንድነት ፣ በዘለዓለማዊቷ ማኅበራችን እንሰብስባቸው ። ዓላማችን ፣ አቋማችን ፣ ዝግጅታችን ፣ መርኋችን ፣ ሀብተ ጸጋችን ሁሉ የጽድቅ መሪዎች ናቸው ። ላመነባቸውና ለሚጠቀሞባቸው ሁሉ ለሰው ነገድ በሙሉ የተሰጡ ናቸው ። ስለዚህ ዓለሙንና ዘመኑን እንዋጅ ትውልዱን እናድን ። የሀብተ ጸጋችንን ክብር እንጠብቅ ። ነፃ ወጥተን ዓለምን ነፃ እናውጣ ። እንጅ ብሉ ጠጡ ስለተባልን ያገኘነውን ሁሉና የተከለከለውን ሁሉ አንብላ አንጠጣ ። ብዙ ተባዙ ስለ ተባልንም አንድ ወንድ ባንዲት ሴት ፣ ከንዲት ሴት በአንድ ወንድ ባለው የጋብቻ ሕግ እንጅ በአመንዝራነት ፣ በሕገ ወጥነት አይደለም ። እንደ ዳንስ ፣ እንደ ዘፈን ፣ በተለያዬ ሱስ እንደተያዝን አለል ዘለል ማለት እስከ መቼ ድረስ ??? !!! ይልቅስ ዘመኑ የዝግጅት ነውና እንዘጋጅ!!!

(ከ ጸያሔ ፍኖት ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን)

ማሳሰቢያበ ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን በ Youtube የ ቃለመጠይቅ ቪዲዮ ላይ ለተለጠፈው የተሳሳተ ርእስ እና ሽፋን ምስል (Cover Picture/ Tumbnail) ግራ መጋባት እንዳይኖር ...
17/05/2020

ማሳሰቢያ

በ ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን በ Youtube የ ቃለመጠይቅ ቪዲዮ ላይ ለተለጠፈው የተሳሳተ ርእስ እና ሽፋን ምስል (Cover Picture/ Tumbnail) ግራ መጋባት እንዳይኖር የተሰጠ መግለጫ እና ማሳሰቢያ

1) ባሕታዊ ገ/ሚካኤል የ ጌታን መምጫ ቀን አውቃለሁ አላሉም ብለውም አያውቁም "ቀኑን አናውቅም ተዘጋጅተን እንጠብቅ ነው ያሉት"
2) የ ኢየሱስ መንገድ ጠራጊ ነኝም አላሉም
" የዳግም ምፅኣት መንገድ ጠራጊ ነኝ ነው ያሉት" ምክንያቱም፣ የተጠሩበት አገልግሎት እና አላማቸው እያየናቸው ያሉትን በርካታ የዳግም ምፅኣት ደውሎች ለተዘናጋው ወገን በማስገንዘብ ስለ ዳግም ምፅኣት የ መፅሐፍ ቅዱስን ና የ ቅዱሳን አበውን አስተምሕሮ መሰረት በማድረግ እያስተማሩ ብዙዎችን ለ ንስሐ ና ለ ቅዱስ ቁርባን ማብቃት ነውና!
ዳግም ምፅኣት እንደ ጌታችን ልደት፣ እንደ ጥምቀቱ ና እንደ ትንሳኤው ታላቅ አምላካዊ ክስተት ነዉና እንደ ሌሎቹ በአላት በድምቀት እንዲከበር ና ታላቅ ና እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናት ታሪካዊ የሆነ ና በ መጠኑም በአለም ትልቁ የሚሆን ቤተ መቅደስ እንዲሰራለት ለማድረግ ነው አላማቸው።
በድምቀት እንዲከበር ሲባል መጋቢት ፳፱ (29) የሚከበረውን ደብረ ዘይት የ ዳግም ምፅኣት በኣል በበለጠ ድምቀት እናክብረው ለማለት ነው እንጂ ሌላ አዲስ በአል እየፈጠሩ እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል።
ባሕታዊ ገ/ሚካኤል ትሁት ና ብሩክ በገቡበት ና በደረሱበት ሁሉ ቤተ ክርስትያን የሚሰሩ አባት ሲሆኑ በ አዲስ አበባ ና በዙሪያዋ እንዲሁም በ ሰሜናዊ የኢትዮጵያ ክፍሎች በርካታ ቤተ ክርስትያናትን ሰርተዋል።
ዋና መልእክታቸውም
" ኑ ታላቁን ደብር እንስራ
ከተመረጠችው ተራራ"
ይሕ በሽታም በቅርብ ይጠፋል ሁላችን በ አንድነት ምሕላውን ከቀጠልን። በፀሎት ያፅናን።
መልእክቶቻቸውን ሌሎችም በማስተላለፍ መንፈሳዊና ታሪካዊ አስተዋፆ እንድታደርጉ ጥሪአችንን እናስተላልፋለን።

በ Youtube
UCTwCHSH1sTdLzwhZLLGk3HA

በ Facbook Page-https://www.facebook.com/698917243558437

15/05/2020

የባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ቃለ መጠይቅ
በ Youtube ቪዲዮው ላይ ለተለጠፈው የተሳሳተ ርእስ እና ሽፋን ምስል (Cover Picture/ Tumbnail) እንዲስተካከል እንጠይቃለን።

ማሳሰቢያ
1) ባሕታዊ ገ/ሚካኤል የ ጌታን መምጫ ቀን አውቃለሁ አላሉም ብለውም አያውቁም "ቀኑን አናውቅም ተዘጋጅተን እንጠብቅ ነው ያሉት"
2) የ ኢየሱስ መንገድ ጠራጊ ነኝም አላሉም
" የዳግም ምፅኣት መንገድ ጠራጊ ነኝ ነው ያሉት" ምክንያቱም፣ የተጠሩበት አገልግሎት እና አላማቸው እያየናቸው ያሉትን በርካታ የዳግም ምፅኣት ደውሎች ለተዘናጋው ወገን በማስገንዘብ ስለ ዳግም ምፅኣት የ መፅሐፍ ቅዱስን ና የ ቅዱሳን አበውን አስተምሕሮ መሰረት በማድረግ እያስተማሩ ብዙዎችን ለ ንስሐ ና ለ ቅዱስ ቁርባን ማብቃት ነውና!
ዳግም ምፅኣት እንደ ጌታችን ልደት፣ እንደ ጥምቀቱ ና እንደ ትንሳኤው ታላቅ አምላካዊ ክስተት ነዉና እንደ ሌሎቹ በአላት በድምቀት እንዲከበር ና ታላቅ ና እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናት ታሪካዊ የሆነ ና በ መጠኑም በአለም ትልቁ የሚሆን ቤተ መቅደስ እንዲሰራለት ለማድረግ ነው አላማቸው።
በድምቀት እንዲከበር ሲባል መጋቢት ፳፱ (29) የሚከበረውን ደብረ ዘይት የ ዳግም ምፅኣት በኣል በበለጠ ድምቀት እናክብረው ለማለት ነው እንጂ ሌላ አዲስ በአል እየፈጠሩ እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል።
ባሕታዊ ገ/ሚካኤል ትሁት ና ብሩክ በገቡበት ና በደረሱበት ሁሉ ቤተ ክርስትያን የሚሰሩ አባት ሲሆኑ በ አዲስ አበባ ና በዙሪያዋ እንዲሁም በ ሰሜናዊ የኢትዮጵያ ክፍሎች በርካታ ቤተ ክርስትያናትን ሰርተዋል።
ዋና መልእክታቸውም
" ኑ ታላቁን ደብር እንስራ
ከተመረጠችው ተራራ"
ይሕ በሽታም በቅርብ ይጠፋል ሁላችን በ አንድነት ምሕላውን ከቀጠልን። በፀሎት ያፅናን።
ይሕ የ ማሕበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ምእት" ዋና ሰብሳቢ የሆኑት የ ባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ተገን ሙሉ ዝርዝር መልእክቶች የሚተላለፉበት ቻናል/ገፅ ሲሆን መልእክቶቻቸውን ሌሎችም በማስተላለፍ መንፈሳዊና ታሪካዊ አስተዋፆ እንድታደርጉ ጥሪአችንን እናስተላልፋለን።

በ Youtube
UCTwCHSH1sTdLzwhZLLGk3HA

በ Facbook Page-https://www.facebook.com/698917243558437
የባሕታዊ ገብረ ሚካኤል ስልክ ቁጥር ቁም ነገር አዘል ና ተገቢ ጥያቄ ላላቸው ምእመናን
+251 9 11 61 45 59

02/05/2020

መልእክት ለመላው ኢትዮጵያዊያን

በየ ሀገራቱ በተለይም በ ቤሩት ያሉ ኢትዮጵያውያን በስራዎች መቆም ምክንያት በተፈጠረዉ ችግር በሚያሳዝን ና በሚያስጨንቅ ሁኔታ በየመንገዱ እየወደቁ ነው። ሁላችንም በ ፀሎት እንድናስባቸው እንዲሁም በየ ማሕበራዊ ድሕረ ገፆች ላይ ድምፃችንን እንድናሠማላቸው ና በምታውቁት መንገድ ሁሉ እርዳታው እንዲደርሳቸው እንድታደርጉ በ እግዚአብሔር ስም ጥሪአችንን እናስተላልፋለን። ሁላችን በምንችለው መንገድ ሁሉ ልንደርስላቸው ይገባል።

21/04/2020

የ ባህታዊ ገብረ ሚካኤል መንፈሳዊ ጥሪ የወቅቱን ጉዳዮች በተመለከተ

ማሳሰቢያ:
በዚህ Video ና በሌሎችም Video ና Post ውስጥ ያሉ ከዚህ በፊት የትም ቦታ ይፋ ያልሆኑ የወደፊት ተስፋ ና ትንቢትን የያዙ በሚገነባው ታላቅ ታሪካዊ ቤተ ክርስትያን ውስጥ የሚቀመጡ ቅዱስ ስእላቶችን አውርዶ በየቦታው መጠቀም የተወገዘ ሲሆን በ ህግ ና በ እግዚአብሄር ዘንድ ያስጠይቃል። በ ባህታዊ ገብረ ሚካኤል በ ሱባኤ የተገኙ፣ በሳቸው የተሳሉ ና በሳቸው ባለቤትነት የተመዘገቡ ናቸው።

በነፃ የተበረከተ የ አዲሡ ወረርሺኝ በሽታ መድሐኒትይሕ ፅሑፍ ባለ ቃልኪዳን የንሥሐ ፀሎት ነዉ፣ አምኖ ለፀለየበት፤ በሀጥያት ብዛት ከከመጣው ወረርሺኝ የሚከላከል ና የሚያድን ነው።
15/04/2020

በነፃ የተበረከተ የ አዲሡ ወረርሺኝ በሽታ መድሐኒት

ይሕ ፅሑፍ ባለ ቃልኪዳን የንሥሐ ፀሎት ነዉ፣ አምኖ ለፀለየበት፤ በሀጥያት ብዛት ከከመጣው ወረርሺኝ የሚከላከል ና የሚያድን ነው።

Address

እንጦጦ
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዳግም ምጽአት ዝግጅት በ ባሕታዊ ገ/ሚካኤል /ማኅበረ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዘነገደ ፻ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share