22/06/2026
በክርስቶስ ተልዕኮ ቤተክርስቲያን የእሁድ ሁለተኛው አገልግሎት
ርዕሰ :- ፍቅር ለእግዚአብሔር ራዕይ ለአለም
- ለእግዚአብሔር ደስታ፣ ለእግዚአብሔር ክብር ተፈጥረናል ትክክለኛ ህይወት መኖር የምንችለው ለክብሩ እና ለደስታው መኖር ስንችል ነው።
- ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር መለኪያው ቃላቶቻችን ስሜቶቻችን ሀይማኖታዊ እንቅስቃሴዎቻችን አይደለም።
- የፍቅር እውነተኛ ፈተና መልሱ የምንናገረው ሳይሆን የምንኖርበት ህይወት ነው። ዩሀ 14:21
- ታላቁ ትዕዛዝ : - ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን መውደድ ነው።
- እግዘብሔርን መውደድ የህይወት አላማ ነው።
- የተፈጠርነው የእርሱ ልንሆን ነው።
- ለእግዚአብሔር ያለን ፍቅር ለሰዎች የሚሆን ራዕይ እና ርህራሄ ይወልዳል
ታላቁ ተልዕኮ - ፍቅር በተግባር ማለት ነው።
-ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ፍቅር ይንቀሳቀሳል ፣ይዘረጋል ፣ይሰዋል፣ ያገለግላል።
- ትልቁ የፍቅር ተግባር ክርስቶስን ለሰዎች ማስተዋወቅ ነው ማቴ 28:19
- ታላቁ መሰጠት መስዋትነት ነው ፍቅር ደግሞ ሁልጊዜ ወደ መስዋዕትነት ያመራል ዩሀ 3:16
-እግዚአብሔር ፍቅሩን ከሰማይ ሆኖ በቃል ብቻ አላወጀም ልጁን ሰደደ።
- እውነተኛ ፍቅር እውነተኛ ቁርጠኝነት መሰጠትን ይወልዳል።
- ታላቁ ቸልተኝነት ማድረግ የሚገባንን አለማድረግ ነው።
-ታላቁ ቸልተኝነት አማኞች የእግዚአብሔር በረከት ተቀብለው ነገር ግን ለሌሎች ሳያገለግሉበት ሲቀሩ ነው።