የተዋህዶ ልጅ ነኝ Orthodox

የተዋህዶ ልጅ ነኝ Orthodox Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የተዋህዶ ልጅ ነኝ Orthodox, Religious organisation, Agona, Addis Ababa.

11/03/2026

ለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምንም ነገር ሳይሰስት ያለውን ሁሉ ሰጠ።በመንፈሳዊ ቅናት የጀመረውን አገልግሎት በመንፈሳዊ ጽናት ፈጸመ።በቃልም በሕይወትም ሰበከ።በተሰጠውም መክሊት ብዙ አተረፈ።በመጨረሻም ወደ አባቶቹ ከተማ በክብር ተጠራ።ዘላለም ወደ ዘለዓለም ሄደ።ሕይወቱና ስብከቱም አሁን ላለውና ለመጪው ትውልድ እንዳበራ ይኖራል።
እግዚአብሔር አምላክ የሁላችንንም ፍጻሜ እንደ አንተ ያሳምርልን።

18/10/2023
እግዚአብሔር ይመስገን በሰላም በጤና ስለተመለሱልን።
12/10/2023

እግዚአብሔር ይመስገን በሰላም በጤና ስለተመለሱልን።

አቤት ግርማ ሞገስ ጠላት ይሄን ሲያይ ይሸበራል ተሸብሮ ሊያሸብረን ይሞክራል ነገር ግን እንደነሱ ፍቃድ ሳይሆን እንደእግዝያብሄር ፍቃድ እንኖራል...
04/03/2023

አቤት ግርማ ሞገስ ጠላት ይሄን ሲያይ ይሸበራል ተሸብሮ ሊያሸብረን ይሞክራል ነገር ግን እንደነሱ ፍቃድ ሳይሆን እንደእግዝያብሄር ፍቃድ እንኖራል...

21/02/2023

ቤተክርስቲያን ለምን ተፈተነች ?

#1, እውቀት አልባ ሰዎች አስቀድመው ቦታውን ስለያዙት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ክብሯን እንድታጣ እያደረጓት ነው።

ሁላችን እንደምናውቀው ዝቅ ብለው ከታች ቤተክርስቲያንን የሚያገለግሉ ሰዎች
የድጓ መምህራን
የቅኔ መምህራን
የአቋቋም መምህራን
የመጻሕፍት መምህራን
የቅዳሴ መምህራን
የዝማሬ መዋስዕት መምህራን
የቀመር መምህራን (የአቡሻኽር) ሌሎችም በብዛት አሉ
በአለቅነት በአሰተዳድር ላይ ሆነው እሊህን ሊቃውንት የሚመሩት ግን መምህርነቱ ይቅርና አብዛኛዎቹ

- ቅኔ አያውቁ
- አቋቋም አያውቁ
- ድጓ አያውቁ
- የመጽሐፍት ትርጓሜ አያውቁ
- ዝማሬ መዋስዕት አያውቁ
- ቀመር አያውቁ
ስለዚህ = የዓሳ ግማቱ ከአናቱ ሆነና እንዲህ ሆነ
አሁንም የቤተ ክርስቲያን ልዕልናዋ ይመለስ ከተባለ ?

ከላይ እስከታች ይስተካከል

ያልተማረው አስተዳዳሪ ይማር
የተማረው ሊቅ ወደወንበር ይምጣ

ያልተማረው አለቃ ይማር
የተማረው ሊቅ ወደወንበር ይምጣ

ያልተማረው መነኩሴ ይማር
የተማረው መነኩሴ ይጰጵስ

ያንጊዜ የቤተክርስቲያን ልዕልና ይመለሳል

# 2, የመነኮሳት ወደከተማ መፍለስ

በሥርዐተ ምንኩስና መነኩሴ ወደበረሃ ወደገዳም ሲመንን እንጂ ወደከተማ ሲመንን አናውቅም
አሁን ግን ሁሉም ነገር ተገለባበጠና ሥርዐቱ ጠፋ

መጽሐፍም እንዲህ ይላል
ከባህር የወጣ ዓሳና በዐቱን የለቀቀ መነኩሴ አንድ ናቸው ይላል።ይህም ማለት ዓሳ ከባህር ከወጣ በሕይወት እንደማይኖር መነኩሴም ከበዐቱ ከወጣ ሕይወተ ምናኔ ጣዕመ ምናኔ የለውም መንፈስ ቅዱስ ይለየዋል ማለት ነው።

አሁንም በየከተማው የተሰገሰጋችሁ አባቶች መነኮሳት እባካችሁ ወደበዐታችሁ (ገዳማችሁ)
ግቡና ጸልዩ የከተማው ዋሻነት ይቅርባችሁ ያንጊዜ መፍትሔ ይመጣል እግዚአብሔርም ይቅር ይለናል።

# 3, የመነኮሳት ደሞዝ
አንድ በሕግ የሚኖር መምህር፣ካህን፣ ሰባኪ ፣ዲያቆን ሚስት ልጅ ያለው 4000 እና 5000 ብር ይበላል ።
በአንጻሩ አንድ መናኝ ነኝ የሚል ብቸኛ መነኩሴ 40,000 (አርባ ሺ ) 50,000(ሃምሳ ሺ) ብር ይበላል ይህን ያህል ደሞዝ የሚበላ መነኩሴ ቢሰስን ሕግ ቀኖና ዶግማ ቢሽር በሕገወጥነት ጵጵስናን ገንዘብ ቢያደርግ ምን ይደንቃል ?
በግብፅ ሥርዐት አንድ ሰው ከመነኮሰ ከመነኮሰበት ቀን ጀምሮ ደሞዙ ይቋረጣል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ደግሞ ከመነኮሰበት ቀን ጀምሮ የደሞዝ ጭማሬ ይደረግለታል ።
ይህ ሥርዐት ከስሩ ካልተ ቆረጠ ነገም
ኢ ሕጋዊ ፓትርያርክ
ኢ ሕጋዊ ጳጳስ
ኢ ሕጋዊ ኤጲስቆጶስ
ኢ ሕጋዊ መነኩሴ
መፈብረኩ አይቀርም

ወደ ትናንቱ ልዕልናችን
ወደ ትናንቱ ማንነታችን
ወደ ትናንቱ ክብራችን ።እንመለስ

የቤተክርስቲያኒቱ የፈተና ምንጮች እሊህንና እሊህን ይመስላሉ።

ለሌሎችም አጋሩት

09/02/2023

ያልተቋረጠው የእስከንድሪያው መንበረ ማርቆስ ስልጣነ ክህነት (apostolic succession) ቅብብሎሽ ይሄ ነው ።

1. ማርቆስ
2. አንያኖስ
3. ሜልያስ
4. ክርዳኑ
5. አምብርዮስ
6. ዮስጦስ
7. አውማንዮስ
8. መርክያኖስ
9. ክላውያኖስ
10. አክርጵያኖስ
11. ዮልዮስ
12. ድሜጥሮስ
13. ያሮክላ (ሔራክልስ)
14. ዲዮናስዮስ
15. መክሲሞስ
16. ቴዎናስ
17. ጴጥሮስ (ተፍጻሜተ ሰማዕት)
18. አኪላስ
19. እለእስክንድሮስ
20. አትናቴዎስ
21. ጴጥሮስ 2ኛ
22. ጢሞቴዎስ
23. ቴዎፍሎስ
24. ቄርሎስ
25. ዲዮስቆሮስ
26. ጢሞቴዎስ 2ኛ
27. ጴጥሮስ 3ኛ
28. አትናቴዎስ 2ኛ
29. ዮሐንስ
30. ዮሐንስ 2ኛ
31. ዲዮስቆሮስ 2ኛ
32. ጢሞቴዎስ 3ኛ
33. ቴዎዶስዮስ (ቴውዳስስ)
34. ጴጥሮስ 4ኛ
35. ድምያኖስ
36. አንስጣስዮስ
37. አንድራኒቆስ
38. ብንያሚን
39. ያቃቱ (አጋቶን)
40. ዮሐንስ 3ኛ
41. ይስሐቅ
42. ስምዖን
43. እለእስክንድሮስ 2ኛ
44. ቆዝሞስ
45. ቴዎድሮስ
46. ካኤል (ሚካኤል)
47. ሚናስ
48. ዮሐንስ 4ኛ
49. ማርቆስ 2ኛ
50. ያዕቆብ 1ኛ
51. ስምዖን 2ኛ
52. ዮሳብ 1ኛ (ዮሴፍ)
53. ካኤል (ሚካኤል) 2ኛ
54. ቆዝሞስ 2ኛ
55. ስንትዮ 1ኛ
56. ሚካኤል 1ኛ
57. ገብርኤል 1ኛ
58. ቆዝሞስ 3ኛ
59. መቃርዮስ 1ኛ
60. ታውፋኔዎስ
61. ሚናስ 2ኛ
62. አብርሃም
63. ፊላታዎስ
64. ዘካርያስ
65. ስንትዩ 2ኛ
66. ክርስቶዶሉ (ገብረ ክርስቶስ)
67. ቄርሎስ 2ኛ (ጌርሎስ)
68. ሚካኤል 2ኛ
69. መቃርዮስ 2ኛ (መቃርስ)
70. ገብርኤል 2ኛ
71. ሚካኤል 3ኛ
72. ዮሐንስ 5ኛ
73. ማርቆስ 3ኛ
74. ዮሐንስ 6ኛ
75. ቄርሎስ 3ኛ
76. አትናቴዎስ 3ኛ
77. ገብርኤል 3ኛ
78. ዮሐንስ 7ኛ
79. ታውዳስዮስ 2ኛ
80. ዮሐንስ 8ኛ
81. ዮሐንስ 9ኛ
82. ብንያሚን 2ኛ
83. ጴጥሮስ 5ኛ
84. ማርቆስ 4ኛ
85. ዮሐንስ
86. ገብርኤል 4ኛ
87. ማቴዎስ 1ኛ
88. ዮሐንስ 5ኛ
89. ዮሐንስ 11ኛ
90. ማቴዎስ 2ኛ
91. ገብርኤል 6ኛ
92. ሚካኤል 4ኛ
93. ዮሐንስ 12ኛ
94. ዮሐንስ 13ኛ
95. ገብርኤል 7ኛ
96. ዮሐንስ 14ኛ
97. ገብርኤል 8ኛ
98. ማርቆስ 5ኛ
99. ዮሐንስ 15ኛ
100. ማቴዎስ 3ኛ
101. ማርቆስ 6ኛ
102. ማቴዎስ 4ኛ
103. ዮሐንስ 16ኛ
104. ጴጥሮስ 6ኛ
105. ዮሐንስ 17ኛ
106. ማርቆስ 7ኛ
107. ዮሐንስ 18ኛ
108. ማርቆስ 8ኛ
109. ጴጥሮስ 7ኛ
110. ቄርሎስ 4ኛ
111. ጴጥሮስ 8ኛ
112. ቄርሎስ 5ኛ
113. ዮሐንስ 19ኛ
114. መቃርዮስ 3ኝእ
115. ዮሳብ (ዮሴፍ) 2ኛ
116. ቄርሎስ 6ኛ
117. ባሲልዮስ
118. ቴዎፍሎስ
119. ተክለሃይማኖት
120. መርቆሬዎስ
121. ጳውሎስ
122. ማትያስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሐዋሪያዊት ናት የምንለው በምክንያት ነው ።

ሀዋሪያቶች በሰበሰቧት በአንዲት ቤተክርስቲያን እናምናለን !






👉 የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትሪያርክ ብፁወ ቅዱስ አቡነ ባሲልዮስ ሰኔ 21/1956 ዓ.ም በግብፁ ፓትርያርክ አቡነ ዩሳብ ካልዕ እና በፓትርያርክ ቄርሎስ ሳድሳዊ አማካኝነት በካይሮ ተቀብተው ሲሾሙ

👉 ሁለተኛው የኢኦተቤ ፓትሪያርክ ሰማዕተ ቤተክርስቲያን ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ በግራ በኩል የአይን ምስክር ሆነው ይታያሉ

06/02/2023

ድርድር የሚባለውን ነገር መሸሽ ግትርነት ሊሆን ይችላል?

ኦርቶዶክሳዊ ያልሆኑት ሁሉ ነገራችን በውል እንዲረዱት የቀረበ ትሑት ማብራሪያ።

(ብርሃኑ አድማስ አንለይ)

ብዙዎች በቅንነት ድርድር ምን ችግር አለው? መንፈሳዊ ሰዎች እንዴት ይህን እንቢ ሊል ይችላል? መነጋገር ምንድን ነው ችግሩ? እነዚህ እና ተመሳሳይ አሳቦችን አለመቀበል እንዴት እነካለሁ የሚል የአለመደፈር ስሜት የሚመስላቸው ሰዎች እንዳሉ ከአንዳንድ አስተያየቶች መረዳት ችያለሁ። ስለዚህ ድርድርን መቀበል ለምን አስቸጋሪ እንደሆነ ለመረዳት ጉዳዩ ምን እንደሆነ ማስረዳት እፈልጋለሁ።

ቤተ ክርስቲያናችን ተጥሷል ብላ ውግዘት ለመፈጸም ምክንያት የሆናት የትኞቹም ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት የሚጠቀሙበት መንፈሳዊ ሕግ መጣሱ ነው። ይህ ሕግ አማኞች በልቡናቸው የሚያምኑትን ረቂቅ እምነት በተግባር በሥርዓተ አምልኮት የሚፈጽሙበት መንፈሳዊ ሥርዓት ማለት ነው። ይህ ሕግ ምን ምን እንደሚያካትት በዝርዝር ማስረዳት ባይቻልም ምን እንደሆነ ለመረዳት እንዲያግዘን ትንሽ ልዘርዝርለት ። ለምሳሌ የጾም ወቅቶችን ፣ ቀኖቹን እና ሰዓቱን የሚመለከተው፣ ቅዳሴ መቼ እንዴት በእነማን እንደሚቀደስ ፤ የክርስቶስ ዐበይት በዓላት እነማን እንደሆኑና እንዴት እንደሚከበሩ፣ ሥርዓተ አምልኮት የሚመሩ እና ቤተ ክርስቲያንን በማስተማርም ሆነ በማስተዳደር የሚያገልግሉ ካህናት እንዴት እንደሚሾሙ እና እንዴት እንደሚሻሩ፣ በስሐተት እና በኃጢአት የወደቁ ሰዎች እንዴት እንደሚመለሱ፤ ይህንን የመሳሰሉትን ብዙ የሥርዓተ አምልኮት ነገሮች በዝርዝር የያዘ መንፈሳዊ ሕግ ነው።

ሰሞኑን የገጠመን ኤጲስቆጶሳትን መሾም እና በሀገረ ስብክት መመደብ የተመለከተውን ዋና የሥርዓተ አምልኮታችን ምሰሶ የሆነውን አስተምህሮ እና ቀኖና የተመለከተ ጥሰት ነው። ይህ ሲያጋጥም ምን እንደሚደረግ እና እንዴት እንደሚፈታ ሁሉ ደግሞ አሁንም ሥርዓቱ አስቀድሞ ደንግጎ እና አስቀድሞም አውግዞ ተቀምጧል። በየዘመኑ የሚደረገው ያንን መፈጸም እና ማስፈጸም ብቻ ነው።

ታዲይ ይህ ነገር ለድርድር እንደማይገባ በዚሁ የቀኖና መጻሕፍት ከተደነገጉት ውስጥ አንድ ሁለቱን ምሳሌ አድርጌ ላስረዳ። ለምሳሌ ያህል አጽዋማትን የተመለከተውን ላንሳ። ለምሳሌ አንድ ሊቀ ጳጳስ ብድግ ብሎ ዐርብ እና ረቡዕን መጾም አይገባም። ዐቢይ ጾምንም ለሃምሳ አምስት ቀናት ሳይሆን ለዐሥራ አምስት ቀናት ይበቃናል። ትንሣኤንም እሑድን ጠብቀን ማድረግ አይጠበቅብንም። ወቅቱንም ብንፈልግ በመስከረም ካልሆነም በጥር እንዳመችነቱ ማድረግ እንችላለን። ዋናው ዐቢይ ጾምን መጾማችን ብቻ ነው የሚበቃው። ይህን ቢያደርግ ይህን ያለው ሊቀ ጳጳስ በአጭሩ ሌላ እምነት መሥርቷል ማለት ይቻላል። ይህን ያደረገ ጊዜ በራሱ ፈቃድ ከነባሩ ኦርቶዶክስ ራሱን ለይቷል። የቀኖና መጽሐፋችን ደግሞ ይህን የሚያደርገውን ገና ቀድሞ አውግዞታል። የአሁኑ ሲኖዶስ ደግሞ ይሰበሰብና ይህን ለማስጠበቅ የተሾመው ጳጳስ ራሱ ስለሻረው ያን የቀደሙ አባቶች የፈጸሙት ውግዘት በተግባር ይፈጸምብሃል ይልና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኅብረት ይለየዋል፣ ሥልጣኑን እና መዓርጉንም ይቀማዋል።

ይህ ከሆነ በኋላ አሁን እንደሚባለው መንግሥት መጥቶ ይህ ምን ችግር አለው፣ በንግግር ይፈታል ቢል አባቶች እና አማኞች የምንለው ይህ ለድርድር አይቀርብም ነው። ምክንያቱም ዐርብ እና ረቡዕን የመሻር ወይም እንዲሻሩም ሆነ እንዲቀጥሉ የመደራደር ሥልጣን ያለው አካል የለም። ዐቢይ ጾምን በ55 ቀናት እና በ15 ቀናት መካከል ተደራድሮ 30 ወይም 45 ቀናት ብቻ የማድረግ ሥልጣን ያለው የለም። ትንሣኤን ከእሑድ ውጭ በሌላ ቀናት ቀርቶ የሚያዚያ ጨረቃ ሙሉ ከመሆኗ በፊት ባለው ሌላ እሑድ ውስጥ እንኳ ያደረገ ቢኖር ከሥልጣኑ ይሻር ነው የሚለው ቀኖናው። የመሰላችሁን ፍረዱበት እንኳን አይልም። ይህም ማለት ፍርዱ ያለቀ የደቀቀ ሆኖ በየዘመኑ የሚኖረው ሲኖዶስ ሥልጣኑ ያንን ተገባራዊ ማድረግ ብቻ ነው።

ለሌሎቻቸሁ ድርድር አይቻልም የሚለው ያልገባቸሁ ክህነት መሾም ልክ እንደ መንግሥት ሥልጣን ስለመሰላችሁ በድርድር የሚያልቅ መስሏችሁ ሊሆን ይችላል። ነገሩ ልክ እላይ የገለጽኩት ዓይነት ብቻ ነው። ልክ ይህ ገብቷቸው ወይም በብዙዎች ዘንድ ይህ መሆኑ አለመታወቁን ጥላ አድርገው መሒዳቸውን ትተው አጥፈተናል ሲሉ ጥለውት ከወጡት ኦርቶዶክስነት ይመለሳሉ። ያኔ ነው መነጋገር የሚቻለው። ሀሳቡን ግልጽ አድርጌው ከሆነ ጉዳዩ ይህ መሆኑን እንድትረዱት እፈልጋለሁ። ልክ እንደሌላ መዋቅር አይደለም ያልነው ለዚህ ነው። ይህ የግትርነት ሳይሆን የእምነት ሕግን የመፈጸም እና ያለመፈጸም ጉዳይ ነው ማለት ነው።

በአጭር ቋንቋ ኦርቶዶክስ እና ሄትሮዶክስ የመሆን ጉዳይ ነው። በእነዚህ መካከል ድርድር መደረግ ይችላል ማለት በፕሮቴስታንት እና በእስልምና መካከልም ይቻላል እንደማለት ያለ መሆኑን በውል መረዳት ተገቢ ነው።

መንግሥት ለምን አስከፋን ካላችሁ? በዚህ ውስጥ ገብቶ ላደራድር፣ እኔ የምሰጠውን ምክርም ስሙ ማለት ቅዱሳን በሠሩት ቀኖና ላይ እኔ የምሰጠው ሀሳብ ሥልጣን ይኑረው ማለት ስለሆነ ይህ ፍጹም ክህደት ነው። ሁለተኛ እነዚህ ሰዎች በቀኖናው መሠረት ተወገዙ እንጂ ሌላ እምነት እንዳይመሥርቱ የከለከላቸው የለም። የጎሣ ኦርቶዶክስ መመሥረትም መብታቸው ነው። ይህን ወደ ኦርቶዶክስ ለማስገባት መሞከር ግን ክህደት ነው፣ የተወገዘ ነው። ሦስተኛ አሁን መንግሥታዊ አካላት እያደረጉት ያሉት ከኦርቶዶክስ ወጥተው አዲስ ለተቋቋሙት ሌላው ቀርቶ ሕጋዊ ሰውነት እንኳ ለሌላቸው የኦርቶዶክስ የሆኑትን መቅደሶች፣ መንበረ ጵጵስናዎች እና ቢሮዎች በጉልበት እየቀሙ እየሰጡ ነው። ይሄ የእኛ የኦርቶዶክሶች ነው፤ እነርሱ እምነታቸውን ሰብከው ካፈሩት ምእመን ልክ እንደ ፕሮቴስታንት የራሳቸውን ይሥሩ ሲል እየገደለ፣ እያሠረ ፣ እየቀማ እየሰጠ ነው። የተጠየቀው ቀላል ጥያቄ ነው። የኦርቶዶክሶችን ለሄትሮዶክሶች ለምን በጉልበት ትሰጣለህ የሚል ቀላል ጥያቄ ነው።

እነዚህን ሰዎች እንደሆኑት ሆነው ተቀብላችሁ አብራችሁ አገልግሉ ማለትም በኦርቶዶክስ መቅደስ ፓስተሩ፣ በመስጊድም ቄሱ ይባርክ ከሚለው ምንም ልዩነት የለውም። ልብሱን ስለለበሱ አሁን ኦርቶዶክስ አድርጋችሁ እንዳትቆጥሩ። ይህን የምንለው እነርሱን በመጥላት እና በመናቅ አይደለም። ይህ እንዳልሆነ የምናመልከው አምላክ እርሱ ልዑል እግዚአብሔር ያውቃል። ይህን የምንለው ጉዳዩ መሠርታዊ የሥርዓተ አምልኮት ጥሰት መሆኑን በገላጭ ምሳሌ እንድትረዱት ብቻ ነው።

እግዚአብሔር ያሳያችሁ!! እንዲህ ያለ በደል በየት ሀገር በማን ላይ ተፈጽሞ ያውቃል? ታዲያ እምነቴን አትንካ፣ የሃይማኖት ተቋሜንም ለማያምኑበት አሳልፈህ አትስጥብኝ። ይልቁንም ሕግ አስከብረህ ከብጥብጥ አድነኝ ስለው በሁሉም በኩል እውነት አለ ማለት ምን ማለት ነው? ግትርነትስ የሚሆነው እንዴት ሆኖ ነው። ጉዳዩ ይሄው ነው። በሕያው እግዚአብሔር ስም እመሰክራለሁ ሌላ ምንም ነገር የለውም። ሀገር ወዳድ፣ እውነት ወዳድ የሆናችሁ ሁሉ ከመተቸታችሁ እና አስተያየት ከመስጠታችሁ በፊት ይህን ነገር በውል ተረድታችሁ እንድታስረዱ በታላቅ ትሕትና እጠይቃለሁ። አስተዋይ ኅሊና ያለው ሁሉ አይቶ ይፍረድ።

አትርፎዬ  #ጊዮርጊስ ጉራጌ ኢትዮጵያ
26/01/2023

አትርፎዬ #ጊዮርጊስ ጉራጌ ኢትዮጵያ

Address

Agona
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የተዋህዶ ልጅ ነኝ Orthodox posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የተዋህዶ ልጅ ነኝ Orthodox:

Share