Glorious Life Church

Glorious Life Church The gospel of Jesus Christ is the only solution for man kind, so keep following us as we follow Jesus Christ. You are blessed.
(259)

“እርሱም፣ “እናንተስ እኔን ማን ትሉኛላችሁ?” አላቸው። ስምዖን ጴጥሮስም፣ “አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ” በማለት መለሰ።” ማቴ‬ ‭16‬:‭15‬-‭16‬ ‭

“ he asked. “Who do you say I am?” Simon Peter answered, “You are the Messiah, the Son of the living God.”” Matt‬ ‭16‬:‭15‬-‭16‬ ‭NIV‬‬

ቸርች እንዴት ነበር(How was Church?)"እምነት መለኪያ ነው!"ዕብራውያን 3:12 NASV[12] ወንድሞች ሆይ፤ ከእናንተ ማንም ከሕያው እግዚአብሔር የሚያስኰበልል፣ ኀጢአተኛና የማያምን...
23/08/2026

ቸርች እንዴት ነበር
(How was Church?)

"እምነት መለኪያ ነው!"

ዕብራውያን 3:12 NASV
[12] ወንድሞች ሆይ፤ ከእናንተ ማንም ከሕያው እግዚአብሔር የሚያስኰበልል፣ ኀጢአተኛና የማያምን ልብ እንዳይኖረው ተጠንቀቁ።

✍️ የልብ ክፋት እና እልከኝነት የእምነት ትልቅ ጠላት ሲሆን በአለማመን ውስጥ ሆነን እንድንቀር ያደርጋል።
አለማመን ተስፋውን ከመውረስ መከልከል፣ እግዚአብሔር ታማኝ እንዳልሆነ ማስመሰል፣ የእምነት እርምጃን ማስቆም፣ ፍርሃትን ማሳደግ እና ልብን ማደንደን ትልቁ በሕይወታችን የሚያመጣው ውድቀት ነው።

የእስራኤላውያን ሕይወት የአለማመን ምሳሌ የሆነበት ምክንያት ግብፃውያንን ሲቀሰፉ አይተው፣ መና ሲዘንብ አይተው፣ ባህርም እንደ ግርግዳ ሆኖ ሲከፈል አይተው እና በእሳትና በደመና አምድ ተመርተው ላሉ ይህን ሁሉ ዘንግተው ወደ አለማመን መግባታቸው ነው።

ኢያሱና ካሌብ የተለዩበት ምክንያት ችግሩን አልካዱም ግዙፎች ሰዎች እንዳሉ አውቀው ነበር። ነገር ግን "እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነዉ" ብለዉ በእምነት ጸኑ።
እንዲሁም አብርሃም የአለማመን ተቃራኒ ሲሆን፤ አለማመን ሁኔታውን ተመልከት ሲለው እርሱ ግን በእምነት ሁኔታውን አይቻለሁ ነገር ግን ተስፋውን የሰጠውን አውቃለሁ ብሎ አመነ።

በመጨረሻም ክርስትና ማስረጃ ይቃወማል ማለታችን ሳይሆን እምነት የሚታየውን ብቻ የመጨረሻው መለኪያ አያደርገውም ማለታችን ነው። ስለዚህ ከማመን ጠላት ከሆኑት በመራቅ በእምነት እንበርታ።

ዮሐንስ 20:29 NASV
[29] ኢየሱስም፣ “አንተ ስላየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ግን ብፁዓን ናቸው” አለው።

ሬቨ ዶ/ር ተዘራ ያሬድ
ቀን እሁድ 17/12/2018
⛪️ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን
አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ
መልካም የመነሳትና የማብራት ምሽት

22/08/2026

በሕይወትዎ የእግዚአብሔርን ድንቅና ተአምራት ማየት ይፈልጋሉ? በቃሉ ታንጸው የእግዚአብሔርን ክብር የሚያዩበትና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሕይወትዎ የሚለወጥበት ታላቅ የጸሎትና የትምህርት ጊዜ ተዘጋጅቷል።
⭐️ በዕለቱ 📖 የእግዚአብሔርን ቃል ከተወደደው መንፈሣዊ አባታችን ሬቨረንድ ዶ/ር ተዘራ ያሬድ ጋር ይኖረናል።
🗓️ ዕለት፦ ነገ እሁድ
⏰ ሰዓት፦ ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ
📍 ቦታ፦ የክብር ሕይወት ቤተ ክርስቲያን (ኤክሰለንስ አዳራሽ)(https://maps.app.goo.gl/w2fjD73tgkdtetMj8)
✨ እርስዎም በክብር ተጋብዘዋል!
የተዘጋጀውን ሰማያዊ በረከትና ተአምራት ለመቀበል በጸሎትና በመጠባበቅ ይምጡ። ይህንን መልእክት ለወዳጅ ዘመድዎ Share በማድረግ የጌታ ሥራ ተካፋይ ይሁኑ!
📲

WE ARE LIVE NOW
22/08/2026

WE ARE LIVE NOW

Join this channel to get access to perks: / የ...

✨ በብርሃን ውስጥ የመኖር ምስጢር እና የተትረፈረፈ ሕይወት! ✨እግዚአብሔር ብርሃን ነው፤ በእርሱ ዘንድ ምንም ጨለማ የለም። እኛም በእርሱ ብርሃን ውስጥ ስንመላለስና ትእዛዙን ስንጠብቅ እውነ...
21/08/2026

✨ በብርሃን ውስጥ የመኖር ምስጢር እና የተትረፈረፈ ሕይወት! ✨

እግዚአብሔር ብርሃን ነው፤ በእርሱ ዘንድ ምንም ጨለማ የለም። እኛም በእርሱ ብርሃን ውስጥ ስንመላለስና ትእዛዙን ስንጠብቅ እውነተኛውን የእግዚአብሔር እውቀት እናገኛለን።

ጠላት ሊሰርቅ፣ ሊያርድና ሊያጠፋ ብቻ ይመጣል፤ ኢየሱስ ግን የተትረፈረፈ ሕይወት እንዲኖረን መጥቷል። ፍቅርና እውነት በውስጣችን ሲበሩ ጨለማው ያልፋል፤ በወንድሙ ላይ ፍቅር ያለውም በብርሃን ይኖራል።

በእግዚአብሔር ቃል የታጠቀና እግዚአብሔርን የሚያውቅ ትውልድ ክፉውን አሸንፏል። በእርሱ ጥበቃ ሥር ላለን ለእናንተ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ አይከናወንም!

📌 የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፦

"እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም..." — 1ኛ ዮሐንስ 1:5

"ትእዛዛቱንም ብንጠብቅ በእርሱ እንደተማመንነ በዚህ እናውቃለን..." — 1ኛ ዮሐንስ 2:3,8,9,14

"እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።" — ዮሐንስ 10:10

"በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ አይከናወንም..." — ኢሳይያስ 54:17

💡 ዛሬ በብርሃን ተመላለስ፤ ጠላት ድል ተመቷል፣ ሕይወትህም በእግዚአብሔር እጅ የተጠበቀ ነው!

#የእግዚአብሔርቃል #ብርሃን #የተትረፈረፈሕይወት #ጥበቃ #እምነት #ኢየሱስጌታነው

🌟 « . . . አምላካችሁን እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችሁና በፍጹም ነፍሳችሁ ብትፈልጉት ታገኙታላችሁ። »— ዘዳግም 4:29🙌 ሁላችሁም በክብር ተጋብዛችኋል! 🙌የማለዳውን በረከት አብረን ለመቀ...
21/08/2026

🌟 « . . . አምላካችሁን እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችሁና በፍጹም ነፍሳችሁ ብትፈልጉት ታገኙታላችሁ። »
— ዘዳግም 4:29
🙌 ሁላችሁም በክብር ተጋብዛችኋል! 🙌
የማለዳውን በረከት አብረን ለመቀበል፣ በጋራ የምንጸልይበትና የምንበረታበት ልዩ ሰዓት ተዘጋጅቶላችኋል።
📅 ቀን፦ ነገ ቅዳሜ፣ ነሃሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ሰዓት፦ ከጠዋቱ 12:00 - 2:00
📍 ቦታ፦ በኤክሰለንስ ዶም አዳራሽ
⚡️ >>>>>>>>>

20/08/2026

🔥 ነገ ልዩ ቀን ነው! 🔥 🔥 ነገ ልዩ ቀን ነው! 🔥

በ A.R.M.Y Winter Camp 5ኛ ቀን ፕሮግራማችን ላይ አብረውን እንዲሆኑ ተጋብዘዋል!

ነገ ቀኑን ሙሉ ከመንፈስ አባታችን ሬቨረንድ ዶ/ር ተዘራ ያሬድ ጋር እጅግ ድንቅና የሚያስገርም ጊዜ ይኖረናል።

👉 ገና አልረፈደም! እርስዎም መጥተው የእግዚአብሔርን ቃል፣ ነፃነትና በረከት ይካፈሉ።

📍 ቦታ፦ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን (Glorious Life Church)

🙌 ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!

1ኛ ዮሐንስ 5፡10 የእምነትንና የአለማመንን ማንነትና የሚያስከትሉትን ውጤት በግልጽ ያብራራል። በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ሰው እግዚአብሔር ሰማያዊውን እውነት በልቡ ስለ...
20/08/2026

1ኛ ዮሐንስ 5፡10 የእምነትንና የአለማመንን ማንነትና የሚያስከትሉትን ውጤት በግልጽ ያብራራል። በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ የሚያምን ሰው እግዚአብሔር ሰማያዊውን እውነት በልቡ ስለጻፈለትና መንፈስ ቅዱስም በውስጡ ስለሚመሰክርለት ውስጣዊ የእምነት እርግጠኝነትና ምስክርነት አለው። በአንጻሩ ደግሞ በእግዚአብሔር የማያምን ሰው እግዚአብሔር ስለ ልጁ የሰጠውን ምስክርነት ባለመቀበሉ ምክንያት በቀጥታ እግዚአብሔርን "ሐሰተኛ" አድርጎ እንደመቁጠር ይቆጠራል። በመሆኑም አለማመን እንዲሁ ተራ ጥርጣሬ ወይም የሃሳብ አለመስማማት ሳይሆን፣ የእግዚአብሔርን ታማኝነት፣ ኃያልነትና እውነተኛነት ጥያቄ ውስጥ የሚከት፣ እንዲሁም እግዚአብሔር ያዘጋጀውን ተስፋና ርስት እንዳንወርስ የሚያግድ ታላቅ የልብ እምቢተኝነት ነው።

🌟 ልዩ የትምህርት የተአምራት እና የድንቅ ፕሮግራም 🌟የጌታን ድንቅና ተአምራት የምንለማመድበት፣ በቃሉ የምንታነፅበት እና የእግዚአብሔርን ክብር የምናይበት ታላቅ የጸሎትና የትምህርት ጊዜ ተዘ...
18/08/2026

🌟 ልዩ የትምህርት የተአምራት እና የድንቅ ፕሮግራም 🌟

የጌታን ድንቅና ተአምራት የምንለማመድበት፣ በቃሉ የምንታነፅበት እና የእግዚአብሔርን ክብር የምናይበት ታላቅ የጸሎትና የትምህርት ጊዜ ተዘጋጅቷል!

📅 ቀን፦ ማክሰኞ፣ ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም

⏰ ሰዓት፦ ከምሽቱ 11፡45 ጀምሮ

📍 ቦታ፦ የክብር ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ኤክሰለንስ አዳራሽ (https://maps.app.goo.gl/w2fjD73tgkdtetMj8)

የተዘጋጀውን ሰማያዊ በረከት ለመቀበል !

ከወዲሁ ሕይወትዎን ለዚህ ፕሮግራም ያዘጋጁ፤ ለወዳጅ ዘመድዎም ይህን ጥሪ በማጋራት (Share) የጌታ ሥራ ተካፋይ ያድርጓቸው!

ቸርች እንዴት ነበር?(How was Church?)"...አለማመን..."ይሁዳ 1:5 NASV[5] ምንም እንኳ አስቀድማችሁ ይህን ሁሉ የምታውቁ ቢሆንም፣ ጌታ ሕዝቡን ከግብጽ ምድር እንዴት እንዳወ...
16/08/2026

ቸርች እንዴት ነበር?
(How was Church?)

"...አለማመን..."
ይሁዳ 1:5 NASV
[5] ምንም እንኳ አስቀድማችሁ ይህን ሁሉ የምታውቁ ቢሆንም፣ ጌታ ሕዝቡን ከግብጽ ምድር እንዴት እንዳወጣ፣ በኋላ ግን ያላመኑትን እንዳጠፋ ላስታውሳችሁ እወድዳለሁ።

✍️ በምድራዊ የሕይወት ስርዓት ውስጥ ርስት የሚወረሰው ሰው ሲሞት ቢሆንም፤ ያ ሰዉ መውረሳችንን የማየት እድል አይደርሰውም ነገር ግን ኢየሱስ ሞተ ርስቱን መውረሳችንን ለማረጋገጥ ከሞት ተነሳ። ታዲያ ርስትን ለመውረስ አስፈላጊው ነገር እምነት ነው።

የእግዚአብሔር ተስፋ ጠላቶች እና ጠንቅ ከሆነው ነገር መካከል አለማመን ሲሆን እስራኤላውያንን ወደ ተስፋቸው እንዳይገቡ ያደረጋቸው ብቸኛ ነገር አለማመን ነበር። አለማመን የሚያጠፋን የሕይወት ስርዓት በመሆኑ አለማመንን በማስወገድ በእምነት መጠንከር እንችላለን።

1 የዮሐንስ መልእክት 5:10 አማ05
[10] በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን ይህ ምስክርነት በልቡ ውስጥ አለ፤ እግዚአብሔርን የማያምን ግን እግዚአብሔር ስለ ልጁ የሰጠውን ምስክርነት ባለማመኑ ሐሰተኛ አድርጎታል።

የአለማመን ትልቁ አደጋ እግዚአብሔር ሐሰተኛ እና ዉሽተኛ እንደሆነ መስካሪ መሆኑ ነው፡፡ እንዲሁም የእግዚአብሔርን ባህርይ ጥያቄ ውስጥ ማስገባት ሲሆን፤ ማለትም የእግዚአብሔርን ታማኝነት፣ ኃይል፣ ጥበብ እና የገባውን ቃል የሚፈጽም መሆኑን ይጠራጠራል።

አንድ ሰው አላመነም ማለት የእግዚአብሔር ተስፋ ኀይሉን አጥቷል ማለት ሳይሆን፤ ሰውየው ግን በእግዚአብሔር ቃል እንዳይታመን፣ እንዳይታዘዝ እና በእምነት እርምጃ እንዳይወስድ የሚያደርገው የልብ አቋም ነው።

የአለማመን ሌላኛው ችግር ተስፋ አለመኖሩ፣ ቃሉ አለመኖሩ እና እግዚአብሔር ኀይል ማጣቱ አልነበረም ነገር ግን ችግሩ የተስፋ ሰጪውን አለማመን እና በቃሉ ላይ ያለን መታመንን መቃወም ነው።
በግሪክ አለማመን " Apistia" ሲሆን ትርጓሜው እምነት ማጣት፣ አለመታመን እና የታማኝነት ጉድለት ሲኖረን ማለት ነው።

በመጨረሻም አለማመን ችግሩን ከእግዚአብሔር በላይ በማየት፣ ካለፈዉ ውድቀት እና የሚታየውን ከማይታየው በላይ በማድረግ ሲመጣ፤ እምነት ደግሞ ቃሉ ሳያጥር በሕይወታችን ሲገባና እኛም ብንሰማ ነው።

"እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።" ሮሜ 10:17

ሬቨ ዶ/ር ተዘራ ያሬድ
ቀን እሁድ 10/12/2018
⛪️ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን
አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ
መልካም የመነሳትና የማብራት ምሽት

Address

Haile G/Selasie Street
Addis Ababa
GLC

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Glorious Life Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Glorious Life Church:

Shortcuts

Share