Kolfe Kal Heywet Church Offical page

Kolfe Kal Heywet Church Offical page Welcome to where impossible is possible !

ዛሬ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም በነበረን የእሁድ አምልኮ፣ መጋቢ ፍጹም ንጉሴ የዕለቱን የወንጌል ቃል ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ🔥 መንፈስ ቅዱስና ተፅዕኖ አምጭ ሰው!🔥 በሚል ርዕስ አካፍለዋል ።...
07/06/2026

ዛሬ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም በነበረን የእሁድ አምልኮ፣ መጋቢ ፍጹም ንጉሴ የዕለቱን የወንጌል ቃል ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ
🔥 መንፈስ ቅዱስና ተፅዕኖ አምጭ ሰው!🔥 በሚል ርዕስ አካፍለዋል ።
📌 መንፈስ ቅዱስ ሲመጣ ትምህርት፣ ሀብት ወይም ሥልጣን ሳይወስነው ተራ ሰዎችን ቀይሮ ታሪክ ለዋጭና ተፅዕኖ ፈጣሪ ያደርጋል (ሐዋ 4:13፣ 1:8)።
📌 የእግዚአብሔር መንፈስ አብሮን ካለ ትውልድ ያዳምጠናል። መንፈስ ቅዱስ የሌለበት ማንኛውም እንቅስቃሴ ትውልድን መቀየር አይችልም።
🎯 በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ተፅዕኖ አምጪ የሆኑ ሰዎች :-
1.የጸሎት ሰዎች ናቸው (ሐዋ 1:14)
2.በእግዚአብሔር ቃል የጸኑ ናቸው (ሐዋ 2:42)
3.ሌሎችን የሚያገለግሉ ና የሚያካፍሉ ናቸው(ሐዋ 4:32-35)
4.በቅድስና የሚመላለሱ ናቸው (ሐዋ 5:1)
5.ለእግዚአብሔር መንግሥት የሚኖሩ ናቸው (ሐዋ 28:31)
የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት አንድ ሰው ለራሱ ለቤተሰቡ ለሀገሩ ይተርፋል!
ጌታ ዘመናችንን በቅዱስ መንፈሱ ይሙላው!

06/06/2026
ዛሬ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በነበረን  የመጨረሻው የ21 ቀን የጾም ፀሎት ማጠቃለያ ላይ መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ  የዕለቱን የወንጌል ቃል ከዘፍ 24  አስተምረዋል።ለትውልዱና ለምድሪቱ ፀሎት...
31/05/2026

ዛሬ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በነበረን የመጨረሻው የ21 ቀን የጾም ፀሎት ማጠቃለያ ላይ መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ የዕለቱን የወንጌል ቃል ከዘፍ 24 አስተምረዋል።
ለትውልዱና ለምድሪቱ ፀሎት ተደርጓል። በስተመጨረሻም የቤተክርስቲያኗ አገልጋዮች በቃሉ መሰረት ራሳቸውን ዝቅ አድርገው በታማኝነት ሕዝቡን ለማገልገል በጉባኤው ፊት ቃል በመግባት የጾም ፀሎት መርዓ ግብሩ ተጠናቋል።
ራዕ19:5 ድምፅም፡— ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ፥ አምላካችንን አመስግኑ።

ዛሬ ግንቦት 16/2018 ዓመተ ምህረት በነበረን የአምልኮ ፕሮግራም መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ በማቴዎስ 16 በመንተራስ ኢየሱስ ክርስቶስ በግል ማወቅ በሚል ርዕስ የዕለቱን ቃል አስተምረዋል ።ኢየ...
24/05/2026

ዛሬ ግንቦት 16/2018 ዓመተ ምህረት በነበረን የአምልኮ ፕሮግራም መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ በማቴዎስ 16 በመንተራስ ኢየሱስ ክርስቶስ በግል ማወቅ በሚል ርዕስ የዕለቱን ቃል አስተምረዋል ።
ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።እነርሱም፡ አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው፥ ይላሉ፡ አሉት።(ማቴ 16፥13-14)
ዛሬስ ኢየሱስ ለእናንተ/ለአንተ/ለአንቺ ማን ነው?
ጴጥሮስ መንፈስ ቅዱስ ሲገልጥለት፦ «አንተ ክርስቶስ የህያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ» ብሎ መለሰ። የቆላስያስ መጽሐፍ (ቆላ 1፥13-29) የኢየሱስን ማንነት ፍንትው አድርጎ ያሳየናል፤ እርሱ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ነው!
💡 በቆላስያስ መጽሐፍ የተገለጠው የኢየሱስ ማንነት፦
1. መሲህ
2. የሁሉ ፈጣሪ
3. ከሁሉ በፊት የነበረ
4. የቤተ ክርስቲያን ራስ
5. አማላጅ
ዛሬም ይህንን ያወቅነውን፣ የተገለጠልንንና በግል ያገኘነውን ክርስቶስን ዝም አንበል! እንኑረው፣ እንመስክረው፣ ለአለምም እናውጅው! ✨

ግንቦት 2/2018 ዓመተ ምህረት በነበረን የአምልኮ ፕሮግራም መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ መዝሙር 23 ተንተርሶ የእግዚአብሔር  ቃል   ያካፈሉን ሲሆን፣በዚሁ ዕለት  የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን...
12/05/2026

ግንቦት 2/2018 ዓመተ ምህረት በነበረን የአምልኮ ፕሮግራም መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ መዝሙር 23 ተንተርሶ የእግዚአብሔር ቃል ያካፈሉን ሲሆን፣በዚሁ ዕለት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ስጋና ክቡር ደም መታሰቢያ በህብረት ተወስዷል።
በዕለቱም የውሃ ጥምቀት የወሰዱ 48 ወንድሞችና እህቶች እጅ በመጫን ተፀልዮላቸዋል።
እንዲሁም ሚያዚያ 11 2018 ዓ/ም በተከናወነው ቡራኬ ዕውቅናና አቀባበል የተደረገላቸው የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አባቶችና እናቶች ለቤተክርስቲያኗ ምስጋና አቅርበዋል ።
📢 በመጨረሻም በኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ ግንቦት የወንጌል ወር በመሆኑ፣ እያንዳንዱ አማኝ የምስራቹን ቃል ለሌሎች እንዲያደርስ ጥሪ ተላልፏል።
"ወንጌልን ባልሰብክ ወየውልኝ!" (1ኛ ቆሮ. 9:16)

"ዕዳችሁን ክፈሉ!" የሚሽን ወር ማጠቃለያ ፕሮግራምበኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የሚሽን ወር ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠናቋል።በዕለቱ ሚሽነሪ...
04/05/2026

"ዕዳችሁን ክፈሉ!" የሚሽን ወር ማጠቃለያ ፕሮግራም
በኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የሚሽን ወር ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ተጠናቋል።
በዕለቱ ሚሽነሪ ለገሰ ኃ/ማርያም ከሐዋርያት ሥራ 13:1-3 በመነሳት "ዕዳችሁን ክፈሉ" በሚል ርዕስ ጥልቅ የሆነ የእግዚአብሔርን ቃል አካፍለዋል። ሚሽነሪው በናይጄሪያና በባንግላድሽ የነበራቸውን አገልግሎት፣ ያጋጠሟቸውን ተግዳሮቶችና የእግዚአብሔርን አስደናቂ ጥበቃ በምስል በማስደገፍ ለጉባኤው አቅርበዋል።
የመልዕክቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
መንፈስ ቅዱስ የሚሰራባት ቤተ ክርስቲያን መገለጫዎች፡
* መሪዎች የመንፈስ ቅዱስን ድምጽ የሚሰሙና አገልጋዮችን ለወንጌል ስርጭት የሚልኩ ናቸው።
* አገልጋዮች ለእግዚአብሔር ጥሪ የሚታዘዙና ለመላክ ዝግጁ የሆኑ ናቸው።
* አባላት አገልግሎቱን በጸሎት፣ በጾምና በምስጋና የሚደግፉ ናቸው።

ዛሬም እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንን ለታላቁ ተልዕኮ ይፈልጋታል። ሁላችንም፦
በጸሎት በመደገፍ፣
በገንዘባችን በማገዝ፣
የእግዚአብሔርን ድምጽ በመስማት ለመላክና ለመላክ እንድንዘጋጅ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም ቤተክርስቲያን እየተከናወኑ ያሉ የሚሽን ስራዎች ሪፖርት ቀርቧል
በዕለቱ 7 አዳዲስ ነፍሳት ጌታ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸው አድርገው ተቀብለዋል።
ወንጌላችን ገና ድል ያደርጋል!
የእግዚአብሔር ቃል ገና ዓለምን ይዘራል!

“ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ!” (1ኛ ቆሮንቶስ 9፡16)የኮልፌ ቃለ-ሕይወት ቤተክርስቲያን በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የምታከብረው "የሚሽን ወር" ትላንት ሚያዚያ 18 ዓመተ ምህረት በይፋ ተጀ...
27/04/2026

“ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ!” (1ኛ ቆሮንቶስ 9፡16)
የኮልፌ ቃለ-ሕይወት ቤተክርስቲያን በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የምታከብረው "የሚሽን ወር" ትላንት ሚያዚያ 18 ዓመተ ምህረት በይፋ ተጀምሯል!
በዚህ ልዩ የበረከት ወር የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፦
* እያንዳንዱ ምእመን በዕውቀቱ፣ በገንዘቡና በጸሎቱ በወንጌል ስራ ውስጥ የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ይተላለፋል።
* ቤተክርስቲያናችን በኢትዮጵያ 15 አካባቢዎች ያሰማራቻቸውን ሚሽነሪዎች በጸሎት እያሰብን፣ በእነርሱ በኩል ለተሰራው ታላቅ ስራ ለእግዚአብሔር ምስጋና ለማቅረብ።
የዕለቱ መልዕክት፦
በመጀመሪያው ቀን መርሃ-ግብር አገልጋይ መጋቢ ዶ/ር ቀለሜ ቃና ባስተላለፉት ወቅታዊ መልዕክት፦
" አፍሪካ ተነሺ! ቤተክርስቲያን ወደ ተለያዩ ዓለማት ወንጌልን ይዛ የምትወጣበት የአፍሪካ ጊዜ አሁን ነው" በማለት አውጀዋል።"
አገልጋዩ በሐዋርያት ሥራ 20፡7-37 ላይ በመመስረት “እኔስ? አንተስ? አንቺስ?” በሚል ጥያቄ ለወንጌል አገልግሎት ያለንን ትጋት እንድንመረምር አሳስበዋል። ወንጌል የእግዚአብሔር የልብ ምት እንደመሆኑ፣ ይህ ዘመን ወንጌልን የምንሰብክበት የመጨረሻው ሰዓት መሆኑንም አስተምረዋል።
በስተመጨረሻም የዋና መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ፣ መልዕክት ተላልፏል በመልዕክቱም መላው ምእመናን በዚህ ቅዱስ የወንጌል አገልግሎት ውስጥ በጸሎትና በድጋፍ እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በየአካባቢው ለተሰማሩት ሚሽነሪዎች፣ ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሁሉ እግዚአብሔር ከፀባኦት በነገር ሁሉ ስኬትንና መከናወንን ይስጣቸው ።
ወንጌል ለሁሉ!

በኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን በሚያዚያ 11/ 2018 ዓመተ ምህረት  የጌታ ራት መርዓ ግብር ላይ በኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አባቶችና እናቶች ቡራኬ ተካሂዷል።ስለ ቡራኬ ምንነትና አስፈላጊነ...
21/04/2026

በኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን በሚያዚያ 11/ 2018 ዓመተ ምህረት የጌታ ራት መርዓ ግብር ላይ በኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አባቶችና እናቶች ቡራኬ ተካሂዷል።
ስለ ቡራኬ ምንነትና አስፈላጊነት በዘፍጥረት 49፡26 በመንተራስ በመጋቢ አመሉ ጌታ የእግዚአብሔርን ቃል አካፍለዋል። ቡራኬ ማለት ሰውን ወደ ሌላ ምዕራፍ የሚያስገባ፣ ቀደምትነትንና ፊተኝነትን ለትውልድ የሚያስተላልፍ ኪዳናዊ ቃል መሆኑን እና ቡራኬ የሚሰጠውም የሚቀበለው ሰው ቡራኬው የህይወት ለውጥ እንደሚያመጣ ማመን አስፈላጊ መሆኑን በአፅንኦት ያስተማሩን ሲሆን እንዲሁም ፀሎትና ቡራኬ የተለያዩ መሆናቸውን፣ ቡራኬ ውድና ልዩ ቃል መሆኑን አና “ይሁን” ማለት እንደሆነና ቃሉ ያለውን ኃይል በግልፅ አብራርተዋል።
በመቀጠልም የቤተክርስቲያኒቱ ዋና መጋቢን ጨምሮ ለ14 አባቶችና ለ2 እናቶች በሕይወታቸውና በአገልግሎታቸው በኢትዮጵያ ወንጌላዊያን ታሪክ ውስጥ ላሳረፉት አሻራ ቤተክርስቲያን እውቅና ሰጥታለች፤ የእግር ማጠብ ሥርዓትም ተከናውኗል።
ከዚያም ለልጆች፣ ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች፣ ለቤተክርስቲያን መሪዎች፣ ለሴቶች፣ ለፀሎት አገልጋዮች፣ ለነጋዴዎችና ለመንግሥት ሰራተኞች ቡራኬ ተሰጥቷል። በቤተክርስቲያኗ የተጀመረው ሥራ እንዲቀጥል አባቶች ባርከዋል።
በመጨረሻም የጌታ ራት በመውሰድ መንፈሳዊ መርዓ ግብር ተጠናቋል፤ በመገኘቱ የባረከን የአባቶቻችን አምላክና አባት እግዚአብሔር የተባረከ ይሁን!!!

የ 2018ዓ/ም የጌታችንና የመድኃኒታችንን የልደት በዓል  መታሰቢያ  ምክንንያት በማድረግ የኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ ለ100 አቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት አድርጋለች።  በዚህም ስነስርዓት ላ...
05/01/2026

የ 2018ዓ/ም የጌታችንና የመድኃኒታችንን የልደት በዓል መታሰቢያ ምክንንያት በማድረግ የኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ ለ100 አቅመ ደካሞች የማዕድ ማጋራት አድርጋለች። በዚህም ስነስርዓት ላይ የነፍስ ምግብ የሆነው የክርስቶስ ወንጌል ተሰብኳል። በማዕድ መጋራት የተሳተፉ ወገኖች የሰላም አለቃውን ኢየሱስን ማመስገን ችለዋል። ክብር ሁሉ ለገናናው ኢየሱስ ይሁን!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kolfe Kal Heywet Church Offical page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Kolfe Kal Heywet Church Offical page:

Share

Category