07/06/2026
ዛሬ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም በነበረን የእሁድ አምልኮ፣ መጋቢ ፍጹም ንጉሴ የዕለቱን የወንጌል ቃል ከሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ
🔥 መንፈስ ቅዱስና ተፅዕኖ አምጭ ሰው!🔥 በሚል ርዕስ አካፍለዋል ።
📌 መንፈስ ቅዱስ ሲመጣ ትምህርት፣ ሀብት ወይም ሥልጣን ሳይወስነው ተራ ሰዎችን ቀይሮ ታሪክ ለዋጭና ተፅዕኖ ፈጣሪ ያደርጋል (ሐዋ 4:13፣ 1:8)።
📌 የእግዚአብሔር መንፈስ አብሮን ካለ ትውልድ ያዳምጠናል። መንፈስ ቅዱስ የሌለበት ማንኛውም እንቅስቃሴ ትውልድን መቀየር አይችልም።
🎯 በመንፈስ ቅዱስ ተሞልተው ተፅዕኖ አምጪ የሆኑ ሰዎች :-
1.የጸሎት ሰዎች ናቸው (ሐዋ 1:14)
2.በእግዚአብሔር ቃል የጸኑ ናቸው (ሐዋ 2:42)
3.ሌሎችን የሚያገለግሉ ና የሚያካፍሉ ናቸው(ሐዋ 4:32-35)
4.በቅድስና የሚመላለሱ ናቸው (ሐዋ 5:1)
5.ለእግዚአብሔር መንግሥት የሚኖሩ ናቸው (ሐዋ 28:31)
የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት አንድ ሰው ለራሱ ለቤተሰቡ ለሀገሩ ይተርፋል!
ጌታ ዘመናችንን በቅዱስ መንፈሱ ይሙላው!