Man Of God Fitsum Abel

Man Of God Fitsum Abel Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Man Of God Fitsum Abel, Religious organisation, Addis Ababa.

22/08/2020

"፤ ነገር ግን መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና።"
(ወደ ዕብራውያን 13: 16)
"But do not forget to do good and to share, for with such sacrifices God is well pleased."
(Hebrews 13:16)

"፤ በሚመጣው ዘመን ነገር ሁሉ የተረሳ ይሆናልና ለዘላለም የሚሆን የጠቢብና የሰነፍ መታሰቢያ አይገኝም። አዬ ጉድ! ጠቢብ ከሰነፍ ጋር እንዴት ይሞታል!" (መጽሐፈ መክብብ 2: 16)
18/08/2020

"፤ በሚመጣው ዘመን ነገር ሁሉ የተረሳ ይሆናልና ለዘላለም የሚሆን የጠቢብና የሰነፍ መታሰቢያ አይገኝም። አዬ ጉድ! ጠቢብ ከሰነፍ ጋር እንዴት ይሞታል!"
(መጽሐፈ መክብብ 2: 16)

19/04/2020

ስለ በደላችን ሞተ... እኛንም ለማፅደቅ ከሙታን በትንሳኤው ኃይል ተነሳ ...በኢየሱስ ሞት ሞት ተሸነፈ፣ጨለማ፣ኃጢአት፣ሰይጣን ተሸነፈ...አንተ(ቺ) የትንሳዔ ልጅ ነህ(ሸ)
Melkam beal

18/04/2020

4. ቃሎቻቹን አትጣሉ
እግዛአብሄር እንደ ግል፣ቤተሠብ፣ቤ/ክ ፣ሀገር የተናገረንን መያዝ ተገቢ ነዉ ፡፡ የእግዛአብሄር ቃል በሰዎች ጊዜ ብቻ ሳይሆን ምቹ በማይመስል ጊዜም ይሠራልና ነው፡፡
" ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።"
(የሐዋርያት ሥራ 27:25)
5. ደስታችሁን አትጣሉ
በሁኔታዎች የማይወሠድ ደስታን ለሠጠን ምስጋና ይሁን፡፡ አንዳንዴ በሀዘን ብናልፍም ሀዘን በኛ ቤት እንዳይሰራ መጠንቀቅ አለብን፡፡
" ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ።"
(ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4:4)
6. መቆረሳችሁን አትጣሉ
ለመቆረስ እና ለሌሎች ለማሠብ ባለጠጋ መሆን ብቻ በቂ አይደለም ።ለመስጠት ሰጪ ልብም ያስፍልጋልና
ከድህነታቸው ጥልቀት የሠጡ እንዳሉ መፀሀፍ " በብዙ መከራ ተፈትነው ሳሉ የደስታቸው ብዛትና የድህነታቸው ጥልቅነት የልግስናቸውን ባለ ጠግነት አብዝቶአል፤"
(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 8:2) ያስተምረናል ፡፡

17/04/2020

አትጣሉ (ክፍል 2)
በዚ ታሪክ ዉስጥ እንደምንማረው በመርከብ ሲጓዙ ከባድ ነዉጥ ሲፈጠር ያላቸውን ሁሉ ቢጥሉም ለዉጥ እንዳላመጡ እና መጣል ያለባቸዉን ሲጥሉ ደግሞ ለውጥ እንዳገኙ እናያለን ፡፡ መጣል የሌለብንን ስንጥል ወደ ኪሳራ ሲያራምድ መጣል ያለብንን መጣል ግን ወደ መረጋጋት እና ወደ መፍትሄ ያመራናል፡፡ በሚከተሉት ቁጥሮች ላይ መጣል የሌለብንን ወይም መያዝ ስላለብን ነገሮች አብረን እንመለከታለን፡፡ ተባረኩ ፡፡
1.እምነታችሁን አትጣሉ
-- ባአምላካችሁ ላይ መታመን መወሠድ የለበትም
-- እምነታቹ እንዲጨምር እዲጎለብት የምትሠሙትን ነገር መምረጥ እና የእግዛአብሄርን ቃል ከወትሮ በተለየ ማንበብና መኖር ያስፈልጋል ይገባናል፡፡
" ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።"
(የሐዋርያት ሥራ 27:25)
2. ፀሎታችሁን አትጣሉ
ለራሳችሁ እና ለሌሎች ፀልዩ
እግዛብሄር ለ ሰው ልጅ የሰጠው ትልቁ ጉልበት እና አቅም ፀሎት ነው፡፡ፀሎት የኛን አለመቻል አሳይተን የሱን አቅም ይዘን የምንነሳበት ቦታም ነው፡፡
ስንፀልይ ጥያቄዎቻችን ባይመለሡ እንኳን ልባችንና አምሮአችን ላይ ከወትሮ የተለየ የደስታ ስሜት ይሰማናል ፡፡
" እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።"
(የያዕቆብ መልእክት 5:16)
3. ማመስገን አትጣሉ
በርግጥም ያለንበትን ዙሪያ ካየን የማመስገን አቅም አንዳዴ አናኝም ነገር ግን ትክክለኛ ምስጋና ተመስጋኙን በማወቅ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
" እንዲህም አለ። ራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን ወጥቻለሁ፥ ራቁቴንም ወደዚያ እመለሳለሁ፤ እግዚአብሔር ሰጠ፥ እግዚአብሔርም ነሣ፤ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን። (መጽሐፈ ኢዮብ 1:21)
ይቀጥላል ተባርኩ

10/04/2020

4. ያለንበትን ሁኔታ እግዛአብሄር እንደሚያዉቅ ማወቅ
" እግዚአብሔርም የእስራኤልን ልጆች አየ፥ እግዚአብሔርም በእነርሱ ያለውን ነገር አወቀ። "
(ኦሪት ዘጸአት 2:25)
5. ነገር ሁሉ ለበጎ እንደሚሆን ማውቅ
" እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 8:28)
6.እግዛአብሄር መልካም እንደሆነ ማወቅ
" እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል። "
(ትንቢተ ናሆም 1:7)

አትጣሉ (ክፍል 1) ከፍጥረት ጅማሬ ጀምሮ እቺ ምድር ብዙ ተግዳሮቶች አሳልፋለች ፡፡ ነገር ግን ለተግዳሮቶች የሚሠጠዉ ምላሽ የተለያየ ሆኖ እናየዋለን ፡፡ አንዳንዶች እንዴት እንደሆነ ሌሎች ...
08/04/2020

አትጣሉ (ክፍል 1)
ከፍጥረት ጅማሬ ጀምሮ እቺ ምድር ብዙ ተግዳሮቶች አሳልፋለች ፡፡ ነገር ግን ለተግዳሮቶች የሚሠጠዉ ምላሽ የተለያየ ሆኖ እናየዋለን ፡፡ አንዳንዶች እንዴት እንደሆነ ሌሎች ደግሞ ማን እንዳደረገዉ ዉጥረት ዉስጥ ይገባሉ፡፡
በመከራ ጊዜ ማወቅ ያለብን ነገሮች
1.የእግዛአብሄር መለወጥ አይደለም
" እኔ እግዚአብሔር አልለወጥም፤ እናንተ የያዕቆብ ልጆች ሆይ፥ ስለዚህ የጠፋችሁ አይደላችሁም። "(ትንቢተ ሚልክያስ 3:6)
2.በ እግዛአብሄር መረሳትም አይደለም
" ያዕቆብ ሆይ፥ እስራኤልም ሆይ። መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች ፍርዴም ከአምላኬ አልፋለች ለምን ትላለህ? ለምንስ እንዲህ ትናገራለህ? "
(ትንቢተ ኢሳይያስ 40:27)
3. መከራ የሰውነታችን መገለጫ ነዉ
" ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10:13)
ሼር በማድረግ ለእርሶም ወዳጅ ይድረስ ተባረኩ

07/04/2020

" እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል። "
(ትንቢተ ናሆም 1:7)

06/04/2020

" ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም።"
(የዮሐንስ ወንጌል 1:5)

05/04/2020

አለመስማት በሽታ ሲሆን የሚሰሙትን አለመምረጥ ደሞ የከፉውን ህመም ያስከትላል ። ከምሰሙት ተጠበቁ bless u

" እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።"1ኛ የጴጥሮስ መልእክት...
29/03/2020

" እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።"1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 5:7)

10/02/2020

Address

Addis Ababa

Telephone

+251921512147

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Man Of God Fitsum Abel posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share