29/05/2026
♥ስድስቱ አስደናቂ የድንግል ማርያም ፀጋዎች
1 በሀሳቧም በሥጋዋም ድንግል መሆኗ
ሴቶች ሁሉ በሀሳብም በሥጋም ድንግል መሆን አይቻላቸውም
በሥጋ ድንግል ቢሆኑ ሀሳባዊ ድንግልና ፈጽሞ የላቸውም ወይም ድንጋሌ ሥጋ ቢኖራቸው ከሄዋን ስህተት እስከ ክርስቶስ መምጣት ያሉት ሴቶች ድንጋሌ ነፍስ አልነበራቸውም
እመቤታችን ግን በሐሳብ በሥጋ ድንግል መሂኗ ከሄዋን ልጆች ሁሉ ልዩ መሆኗን ያስረዳል ድንጋሌ ነፍስ ማለት ሲኦል አለመውረድ ነው
በሄዋን ምክንያት 5500 ዘመን ሙሉ ሴቶች ወደሲኦል ይወርዱ ነበር እመቤታችን ግን ወደሲኦል የሚወርዱ ሴቶች የሚመኩባት ገነትን የከፈተች የገነት በር ናት
በሄዋን ምክንያት ገነት ቢዘጋ በድንግል ማርያም ተከፍቷልና
2 የእግዚአብሔር እናት መሂኗ
ሄዋን ምክንያተ ሞት ቃኤልን ስትወልድ ድንግል ማርያም ግን የሕይወት ራስ ክርስቶስን ወለደች
ሴቶች የወለዷቸው ልጆች ራሳቸውን ማዳን የማይችሉ ናቸው እመቤታችን ግን ዓለምን በመሀል እጁ ይዞ የሚገዘውን እግዚአብሔር ወልድን እንበለ አብ ወእንበለ ዘርዕ ወዘእንበለ ሩካቤ ወለደችው
በአባቱ ፈቃድ ወረደ በድንግል ማርያም ዘንድ እንግዳ ሆነ በንጹህ ድንግልናዋ እግዚአብሔር ተወለደ ብሎ ሊቁ እንተናገረው እመቤታችን የእግዚአብሔር እናት ሆነች እመ እግዚአብሔር ጸባኦት ብሎ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እንደመሰከረው
ሴቶች ሟች ሰው ወለዱ
እመቤታችን ግን ሕያው እግዚአብሔር ወልድን ወለደችው
ሰው ስትሆን ደግሞ የእግዚአብሔር እናት መሆኗ ለእመቤታችን ብቻ የተሰጠ ልዩ ጸጋ ነው
3 የተባረከች መሇኗ
ሴቶች ሁሉ በሄዋን ምክንያት ተረግመው በነበረበት ወራት ከሴቶች ተለይታ የተባረከች ናት ቡርክት አንቲ እምአንስት ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ብሎ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እንደተናገረው
ከሄዋን እስከ ክርስቶስ ድረስ የነበሩ ሴቶች ሁሉ የተረገሙ ነበሩ
እመቤታችን ግን ከተረገሙ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ከሞላባቸው ሴቶች መካከል በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ ተገናጽፋ የተወለደች ናትና ቡርክት አንቲ ይላታል
4 ደስተኛ መሆኗ
5500 ዓመት የነበሩ ሴቶች በሙሉ ኀዘንተኛ ነበሩ
ደስታ አልነበራቸውም
በወንዶች ጭቆና ስር ነበሩ
በእናንተ ምክንያት ሞት መጣብን
በእናንተ ምክንያት ርስት አጣን እያሉ ወንዶች ርስት አያካፍሏቸውም ነበር በዚህ ምክንያት ያዝኑ ነበር እመቤታችን ግን ተፈስሒ ፍስህት ደስተኛይቱ ደስ ይበልሽ ብሎ መልአኩ እንደተናገረው ባዘኑት ሴቶች መካከል ደስተኛ ስለሆነች የደስተ መፍሰሻ ሙሐዘ ፍስሐ ይላታል ፊቷ እንደ ፀሐይ ያበራ ነበር
ያዘነ ሰው ፊቱ ይጠቁራል የተደሰተ ሰው ፊቱ ያበራልና
እመቤታችን ግን ውሎ አዳሯ ከፍሱሐን መላእክት ጋር በቤተ መቅደስ ነበርና የደስታ መፍሰሻ ናትና ተፈሥሒ ፍሥሕት ይላታል
ለአዘነው ዓለም ደስታ ናትና
ለተከዘው ዓለም ሰላም ናትና
5 ጸጋ የተመላች መሆኗ
ሴቶች ሁሉ ጸጋቸውን ተገፈው እርቃነ ሥጋ እርቃነ ነፍስ በነበሩበት ጊዜ ክብር ጸጋ ከሱቶች በጎደለበት ወቅት ጸጋን የተሞላች ምልእተ ጸጋ ሁና ከእናቷ ከሀና ተወልዳለችና መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ኦ ምልዕተ ጸጋ ይላታል
6 እግዚአብሔር ከእርሷ ጋራ መሆኑ
የሰው ልጅ በፈቃዱ የዲያብሎስ ባሪያ ነኝ ብሎ ፈርሞ ገብረ ዲያብሎስ ዓመተ ዲያብሎስ አዳም ገብሩ ለዲያብሎስ ሄዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ በተባለበት ወራት ዓመተ እግዚአብሔር ሁና እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው ይላታል 5500 ዘመን ሰው ሁሉ የሰይጣን ማደሪያ በነበረበት ጊዜ የእግዚአብሔር ማደሪያ ሁናለችና መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው አላት ሉቃ 1/26 ጀምሮ
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ