Semayawi Thought

Semayawi Thought Equipping Ethiopian Christians to renew their minds through this media, serve the church and create culture to the glory of God

Semayawi Thought is a nonprofit online magazine published in Amharic and English both, a platform for Ethiopian Evangelical Christians Professionals and for those who are attracted in Semayawi (heavenly) thoughts. Our online magazine is much more than a blog, which is simply a chronological list of posts focused on publishing different types of spiritual contents and devoted to personal and spirit

ual growth. Together as a community, we will experience the fullness of life, grow spiritually and personally. For those of you who have been wishing to read and write your deepest reflections and ideas for Ethiopian Churches, Semayawi Thought will provide you opportunities. On Semayawi Thought, we issue a spiritual perspective on world events as well as tools for your spiritual practice, all based on Bible. Filled with convenient as well as inspirational content, hoping it will change your life. And don't miss our ever-expanding line of bringing quality contents to Ethiopian Christians!

‹ አጥብቆ ጠያቂ የእናቱን ሞት ቢረዳም›› እውነቱን አውቆ እርሙን ማውጣት፣ ማድረግ ያለበትንም አስተውሎ ማድረግ ይሻለዋል፡፡የእኛ አገር ነገር አደናጋሪ፣ አሳሳቢ፣ አስጨናቂ፣ አጠያያቂ ከሆነ ...
31/07/2026

‹ አጥብቆ ጠያቂ የእናቱን ሞት ቢረዳም›› እውነቱን አውቆ እርሙን ማውጣት፣ ማድረግ ያለበትንም አስተውሎ ማድረግ ይሻለዋል፡፡
የእኛ አገር ነገር አደናጋሪ፣ አሳሳቢ፣ አስጨናቂ፣ አጠያያቂ ከሆነ ሰነበተ፡፡ በአንድ ወገን ሲቃና በሌላ ወገን ይደረመሳል፣ ዛሬ በሰለ ሲባል አድሮ ቃሪያ ይሆናል፡፡ እፎይታ የሩቅ ህልም እየመሰለ ሄደ፡፡ ውጥረትና ሁካታ የወትሮ ልብስ ሆኑ፤ ጣርና ሲቃ አየሩን ሞሉት፡፡ ለምንድነው ይህ የሚሆነው? ምን ቢሆን ነው የሚስተካከለው? መቼ ነው ይህ አገር አደብ የሚገዛው? ብርቱ ጥያቄ ልቦናችንን ይገዘግዛል፡፡ እንደ አገር ሁሉ ቤተክርስቲያንም እንደታመመች እንዳቃሰተች አለች፡፡ የብርሃን ማማ እንድትሆን የተጠራች፣ የተስፋ ቋት እንድትሆን የምንጠብቃት ይህች የክርስቶስ አካል ኩራዟ እየተስለመለመ፣ ጎተራዋ እየተመናመነ የሚሄድ ይመስላል፡፡

ለምን ይህ ሁሉ ሆነ?

የዚህ መጣጥፍ ርዕስ ከመጽሐፈ መሳፍንት ምዕራፍ 6 የተቀዳ ነው፡፡ ጌዴዎን ብርቱ ገበሬ እንደነበር ከትጋቱ እናስተውላለን፤ በጠላት በተዋከበ አገር ውስጥ ተደብቆም ቢሆን፣ ጉድጓድ ገብቶም ቢሆን ስንዴውን ይወቃል፣ አላረፈም፣ እጅ አልሰጠም፡፡ በሥራ ቦታው የተገለጠለት መልአክ ከጌዴዎን አስተሳሰብ ጋር የማይገጥም ከፍ ያለ ነገር ይናገራል፡፡ ‹‹ አንተ ጽኑዕ፣ ኃያል ሰው ፣ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነው፡፡››
የመልአኩ ዐዋጅ እና የመሬቱ እውነታ አልገጣጠም ያለው ጌዴዎን ብርቱ ጥያቄ ጠየቀ፡፡‹‹ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ይህ ነገር ሁሉ ለምን ደረሰብን? ለምን የምድያም መጫወቻ ሆንን? ለምን ዘወትር በፍርሀት እና በሰቀቀን እንኖራለን? ለምን መቅኖ ቢስ ተንከራታቾች፣ የዋሻ እና የጉድጓድ ነዋሪዎች ሆንን? ስንት ታሪክ እየተተረከልን፣ ስንት ታምራት እየተነገረን አሁን ያለንበት ሰቆቃ ውስጥ ለምን ወደቅን?
የጌዴዎንን ታሪክ ዙሪያ ገባ ስናጤን መልሱ አጅግም ውስብስብ አይደለም፡፡ ሕዝበ እስራኤል ከባርነት ያወጣቸውን አምላክ በሌሎች አማልክት ተክተውታል፡፡ ‹‹ባዕዳን አማልክትን አታምልኩ›› ያላቸውን የታዳጊያቸውን ቃል አልሰሙም፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ በመከራም ውስጥ ሆነው ትዕቢታቸው እና ‹‹ ከእኛ በላይ ላሣር›› የሚለው መፈክራቸው አልተለወጠም፡፡ ‹‹ እስራኤል እጄ አዳነኝ ብሎ እንዳይታበይብኝ የሰራዊቱን ቁጥር ቀንስ›› ብሎ እግዚአብሔር ጌዴዎንን ያዘዘው የልባቸውን ዐውቆ ነው፡፡ ከድል በኋላ እንኳ አንዳንዶቹ የታሪክ ሽሚያ ውስጥ ገብተው ‹‹ እኛን ሳትጠሩን ለምን ዘመታችሁ?›› እስኪሉ ድረስ ጉረኞች ነበሩ፡፡

በኢሳይያስ መጽሐፍ ውስጥ ደግሞ ሌሎች ጥያቄዎች አሉ፡፡ ‹‹ ፀሎት የማትመልስ ከሆነ ለምን ጾምን? ለምንስ ጸለይን? የሚሉ፡፡ ‹‹ አንተን ፈልገን እራሳችንን ያዋረድነው ፋይዳው ምንድነው? የሚሉ፡፡ ለእነዚህም መልሱ ሩቅ አይደለም፡፡ አስመሳይ ሀይማኖተኞች፣ ጸሎት አሳማሪ፣ ክፉ ሥራ ሠሪ ሆነው የተገኙ ናቸው፡፡ ግብዝ ሃይማኖተኝነት ከባዕድ አምልኮ አይተናነስም፡፡ ይጾማሉ፣ እንደ እንግጫ እራሳቸውን መሬት ላይ ያነጥፋሉ፤ ግን ከጸሎት ሲነሡ ያው የራሳቸውን ፍቃድ ይፈጽማሉ፡፡ ምንም ለውጥ የለም፡፡ ከጾምና ከጸሎት ሲመለሱ በግፍ ጡጫ ይማታሉ፣ ፍትህ ማጓደል፣ እብሪት ና ንፉግነት ያጠመቀው የኑሮ ዘይቤያቸው በሀይማኖተኝነት ካባ ተጀቡኖ ይጎማለላል፡፡

አምላክ እንዴት ይስማ?

የዕዝራ-ነህምያ ዘመን ሰዎች ደግሞ የገቡበት አስጨናቂ በደል ድብልቅነት ነበር፡፡ የተመረጠው ሕዝብ ከአሕዛብ ጋር ተደባለቀ፣ከርኩሰታቸው እና ከጸያፍ ሥራቸው ጋር ተባበረ፡፡ ልዩ ማንነቱን አሽቀንጥሮ ጥሎ ያው እንደጀማው፣ ያው እንደሰፈሩ፣ ያው እንደጎረቤቱ ሆነ፡፡ ‹‹ ፊቴን ወዳንተ ለማንሣት አፍራለሁ፣ እፈራማለሁ›› እስኪል ድረስ የካህኑ የዕዝራ ለቅሶ ከባድ ነበር፡፡ ለአገራዊ ችግሮቻችን ብዙ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ምናልባትም ሥነልቦናዊ ትንታኔ ሊሰጥ እንደሚችል አይጠፋኝም፡፡ሁሉም በአግባቡ ቦታ ይኖረዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንደ እግዚአብሔር ሰዎች መሰረታዊ ምክንያቱን ቆፍረን ማግኘት ይገባናል እላለሁ፡፡

እንደ ሕዝበ እስራኤል ሆነንስ ቢሆን?
በነባር ባህል ስም፣ በአባቶቻችን ቅርስ ስም ባዕድ አምልኮን አንግሠንስ ቢሆን?
ዐደባባዮቻችን ለሌሎች አማልዕክት መሠዊያ መሥሪያ ሜዳ ሆነውስ ቢሆን?
በየልባችን ጓዳ የፍቅረ ነዋይ፣ የአውስቦ፣ የዝና ጣዖታት እያባበለን ቢሆንስ?
በዘር፣በታሪክ ትምክህት ልባችን ተደፍኖ ዕብሪት እና ትዕቢት አፍኖን ከሆነስ?
በዝሙት፣ በርኩሰት፣ በከንቱ ፈንጠዝያ፣ በዓለማዊ ልማድ ተጠፍረን፣ እየፀለይንም፣ እየጾምንም እዚያው ረግረግ ውስጥ ተዘፍቀን እንደሆነስ?
በየቤታችን ፣በየመሥሪያ ቤታችን ግፍ እየፈፀምን፣ፍትህ እያዛባን ማስነን እንደሆነስ?
ይህን ሁሉ በክርስትና ካባ፣ በጮሌ ቋንቋ ሸፋፍነን እየተሳሳቅን ቢሆንስ?
የጥላቻ መርዝ በሠራ አካላችን ተሰራጭቶ በቁም የሞትን ሬሳ አድርጎንስ ቢሆንስ?


ይህን ሁሉ የምጠይቀው በትህትና ነው፤ተጨንቄ ነው፤ ራሴንም እዚያው ውስጥ እየተመለከትኩ ነው፡፡ ወገኖች‹‹ ይህ ነገር ሁሉ ለምን ደረሰብን?›› ብሎ መጠየቅ ነውር ነው እንዴ? አምላክ ጥያቄ አይፈራም፤ ለመልስም አይቸገርም፤ ስለዚህ በቅንነት እንጠይቅ፡፡



‹‹ አሁን የእኛ ኀጢአት ከሌሎች አገሮች እና ሕዝቦች በደል በልጦ ነው እንዴ?›› ቢባልስ?‹‹ እግዚአብሔርን ሽምጥጥ አድርገው የካዱት፣የሰደቡት ሕዝቦች ተመችቷቸው ይኖሩ የለ? እኛ ከእነርሱ ብሰን ነው?›› ወዳጆቼ መጽሐፍ ምን ይላል---- ‹‹ ለእያንዳንዱ እንደሥራው እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር አለ›› የሚል የምድር ሁሉ ዳኛ እንዳለ ይነግረናል፡፡ ለማን፣ መቼ ምን እንዳቆየለት አናውቅም፤ ብያኔው በእጁ ነው፡፡ ታሪክም በአንድ ትውልድ ዕድሜ አይቋጭም፡፡ እስራኤል የወጓቸው የአሞራውያን ኀጢአት ጽዋ እስኪሞላ አራት መቶ ዓመት ተጠብቋል፡፡ የዘመንን እና የፍርድ ነገር በጻድቁ አምላክ አጅ ነው፡፡ የእነርሱን ለእነርሱና ለእውነተኛው ዳኛ ትተን በራሳችን ጉዳይ ላይ ማትኮር ይሻለናል፡፡

ይህስ ይሁን----- መዳኛ፣ መቃኛ መንገድ የለም ወይ? ካልን ግን ለሁሉም አጥጋቢ መልስ ተሰጥቷል፡፡ ጌዴዎን ከመዝመቱ በፊት አባቱ የሠራውን የበዓልን መሠዊያ እንዲያፈርስ ተጠየቀ፡፡ በኢሳይያስ ትንቢት የተጠቀሱት ሰዎች የግፍ ሥራን ትተው በርኅራኄ እና በጽድቅ እንዲኖሩ ተነገራቸው፡፡ የዕዝራ-ነህምያ ዘመን የምርኮ ተመላሾች እራሳቸውን ከድብልቅ ሕዝብ እንዲያጠሩ ታዘዙ፡፡ ለእኛም ይኸው ነው፡፡ ቁርጠኛ የመመለስ እርምጃ መውሰድ፡፡

‹‹ በዚያን ጊዜ ብርሃንህ እንደንጋት ይበራል፣ ፈውስህም ፈጥኖ ይበቅላል፣ ጽድቅህም በፊትህ ይሄዳል፣ የእግዚአብሔርም ክብር በኋላህ ሆኖ ይጠብቅሃል፡፡ የዚያን ጊዜ ትጣራለህ እግዚአብሔርም ይሰማሀል፣ትጮኻለህ እርሱም እነሆኝ ይላል------;
(እባካችሁ ኢሳይያሰ 58 ን አንብቡ እና የእግዚአብሔርን ደግነት አስተውሉ፡፡)

በመካተቻው ግን እስከዛሬ ከተጠየቁት ‹‹ ለምን)›› ኦች ሁሉ የላቀውን ‹‹ለምን›› የመልሶች ሁሉ ዐውራ የሆነውንም መልሱን መናገር አለብኝ፡፡ ጠያቂው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነበረ፡፡ ‹‹ አምላኬ ፣ አምላኬ ለምን ተውኸኝ?›› ሰበቡም (መልሱም) የእኔ እና የእናንተ ኀጢአት ነበረ፡፡ መትረፊያውም መስቀሉ ነበረ፤ ነውም፡፡ ለዓለሙ ሁሉ ‹‹ለምን››ታ የእግዚአብሔር ቁርጥ መልስ የክርስቶስ ኢየሱስ መስቀል ነው፡፡ ወዳጆቼ ሆይ በመስቀሉ አምባ ውስጥ ተገን እናገኛለን፡፡ ሙጥኝታችን፣ ትምክህታችንም ራቁቱን የተሰቀለው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

እኛን ያድነን ፤ አገራችንን ይፈውስልን፤ ቤተክስቲያንንም ያድስልን፡፡

ዛሬ ዛሬ መጽሐፍ ቅዱስ ከፍተን ነው ሰባኪ መከታተል ያለብን። እጅ አጣጥፈን ከመድረክ ወደ እኛ የሚወረወረውን እንዲሁ እንደወረደ ለመቀበል መምጣት የለብንም። በሰባኪው እና በእኛ መካከል መጽሐ...
28/07/2026

ዛሬ ዛሬ መጽሐፍ ቅዱስ ከፍተን ነው ሰባኪ መከታተል ያለብን። እጅ አጣጥፈን ከመድረክ ወደ እኛ የሚወረወረውን እንዲሁ እንደወረደ ለመቀበል መምጣት የለብንም። በሰባኪው እና በእኛ መካከል መጽሐፍ ቅዱስ መከፈት አለበት፤ ሚዛናችን እሱ ስለሆነ ማለት ነው።

አንደኛ ተሰሎንቄ 2: 6-12፡ "ከእናንተም ሆነ ከሌሎች ከማንም ከሰው የሚገኝ ክብር አልፈለግንም። የክርስቶስ ሐዋርያት እንደመሆናችን መጠን ሸክም ብንሆንባችሁም ነበር" ይላል። ክብርን ከሰው በመፈለግ ማንም ሊከሳቸው እንደማይችል በድፍረት ነው የሚጽፍላቸው።

ብዙዎች እንደምትስማሙት ዛሬ ዛሬ በጣም በሚያስፈራው ሁኔታ አገልጋይ መሆን እና ክብርን ከሰው መፈለግ ላይፋቱ እርስ በርስ የተጋመዱ ሆነዋል። አገልጋይ መሆን እና ከበሬታን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ (intentionally) ከጉባኤው መፈለግ እነዚህ ሁለቱ እርስ በርስ እየተጋመዱ ሆነዋል። በተለይ አገልጋይ ስለሆኑ ብቻ የፊት ወንበር እንዲለቀቅላቸው፣ ነጭ ሶፋ እንዲሰራላቸው፣ ወደ ጉባኤ ደግሞ ሲገቡ ካሜራውም ሕዝቡም እነሱን በአይኑ አስገብቶ አስቀምጦ... ያው የምታውቁት ትዕይንታዊ የሚመስል የአገልጋዮች ከጉባኤ ከበሬታን የመፈለግ አደገኛ ባህል እዚህ ምድርም ላይ እየገነነ መጥቷል።

አሁን አሁን አልፎ አልፎ ሶሻል ሚዲያ ላይ የምታዝበው ነገር፣ ልክ እንዲህ እናንተ በእሁድ ፕሮግራም ከቅዱሳን ጋር ህብረት ለማድረግ ስትመጡ አገልጋዮቹ እዛ ጋር ተጠባብቀው ነው የሚገቡት። ካሜራማኑ ግቡ ሲላቸው ነው... ልክ ሰልፉን ሲጀምሩት፣ መራመዱን ሲጀምሩት ራሱ ያስታውቃል። ሳያውቁት እራሳቸው ላይ ፓፓራዚ (paparazzi) ሆነዋል። እራሳቸውን በካሜራ እያደኑ የሚቀርጹ ናቸው። በግድ እጃቸው ላይ ባለው ስልክ፣ ሁልጊዜ እሁድ እሁድ ሙሽራ ሆኖ በጉባኤ የመታጀብ ባህል ወደ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እየመጣ ነው።

አገልጋይ ሆኖ፣ በተለይ የክርስቶስ አገልጋይ ሆኖ ከሚያገለግሉት ጉባኤ ክብርን መፈለግ ከትምህርት መሳሳት ጋር ብቻ አይደለም የሚገናኘው። ከስነ-ልቦና ቀውስም ጋር ይገናኛል። በልጅነት ትኩረት አጥቶ ያደገ ሰው ምልክትም ሊሆን ይችላል። ፍቅር አግኝቶ ያለማደግ ቀውስ (attachment disorder) ሊሆን ይችላል፣ ወይም ናርሲስቲክ ኢንጁሪ (narcissistic injury) ሊሆን ይችላል። ሁልጊዜ እየተገፋ ያደገ ሰው፣ እድልና አጋጣሚ በአመቻቸለት መድረክ ላይ ሲቆም ሰዎች ሁሉ በግንባራቸው ተደፍተው እንዲሰግዱለት ሊፈልግ ይችላል። አንዳንዱ የስህተት ትምህርት ነው፣ አንዳንዱ የስነ-ልቦና ቀውስ ነው፣ አንዳንዱ ፍጥጥ ያለ ወንጀል ነው።

በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት (approval) ያገኘ፣ ልቡን ኩላሊቱን እግዚአብሔር የሚመረምርለት፣ ወንጌልን በአደራ መልክ ከእግዚአብሔር እጅ የተቀበለ አገልጋይ፣ ከሰው የሚገኝ ክብር አያማልለውም።

ጳውሎስ ይህንን ነው ቁጥር ስድስት ላይ የሚናገራቸው። "ከሰው የሚገኝ ክብር አልፈለግንም" ነው የሚለው። ከእናንተም ሆነ ከሌሎች ከማንም የሚል ቃል አለ። ከእናንተ ከተሰሎንቄ ሰዎች፣ ከአማኞች፣ ከሌሎችም በዙሪያችሁ ካሉ በሌሎች ከተሞችም ካሉ ቅዱሳን ከሰው ይለዋል... በጣም በእርከን እያሰፋው ይሄድና ክብርን አልፈለግንም። ምንም እንኳ የተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን የተተከለችው በሐዋርያው ጳውሎስ ሚሲዮናዊ አገልግሎት ቢሆንም፣ ጳውሎስ ግን ክብርን ከተከለው ቤተክርስቲያን ነው አልፈልግም እያለው ያለው። ገና ለገና በእኔ ስብከት እና የወንጌል ተልዕኮ ነው የተተከላችሁት ብሎም፣ እንደ ዘመኑ መስራች ባለ ራዕይ ፓፓ ካላላችሁኝ ብሎ ጉባኤውን አላሰቃየም። ምንም ቢገባውም እንኳን፣ አልፈልግም የሚልን ግልጽ የሆነ መመሪያን ነው ለተከለው ቤተክርስቲያን የጻፈው።

በንግዱ አለም መውደቅም ሆነ መነሳት በአጋጣሚ ስለማይከሰት፣ ሆን ብለን የምንሰራው ስራ እና የምንገነባው ጠንካራ አስተሳሰብ (Mindset) ሊኖረን ይገባል። በማንኛውም የንግድ ስራ ውስጥ ስኬ...
23/07/2026

በንግዱ አለም መውደቅም ሆነ መነሳት በአጋጣሚ ስለማይከሰት፣ ሆን ብለን የምንሰራው ስራ እና የምንገነባው ጠንካራ አስተሳሰብ (Mindset) ሊኖረን ይገባል። በማንኛውም የንግድ ስራ ውስጥ ስኬታማ ለመሆን መጀመሪያ አስተሳሰባችንን በትክክለኛው መንገድ መቃኘት ያስፈልጋል።
በአጠቃላይ በዩኒቨርስ ውስጥ ሁለት ዋና ዋና የንግድ መንገዶች ወይም ስብዕናዎች አሉ። አንደኛው እግዚአብሔር የሚያካሂደው ሲሆን፣ እርሱም የአንድን ሰው ነፍስ ከአለም ሁሉ በላይ አብልጦ የሚገምት ትርፍ ፈላጊ አምላክ ነው።
እግዚአብሔር ትርፍ ፈላጊ አምላክ ነው። እግዚአብሔር ኪሳራ አጋጥሞት ያውቃል። አንዱ ኪሳራ ያጋጠመው በኛ ምክንያት ነው። እኛ በወደቅን ጊዜ አዝኗል። አንድ ጊዜ እንደውም ቢዝነስ ዘግቷል፤ ሙሉ አለምን በጥፋት ውሃ አጥፍቶ አንድ ቅርንጫፍ (branch) ብቻ አስቀርቶ ሌላውን ሁሉ ዘግቷል። አሁንም ደግሞ ያለውን ቢዝነስ ቁጭ ብሎ ኦዲት የሚያደርግበት ጊዜ ይመጣል። የሚያተርፈው ትርፍ አለው፤ ኪሳራ ብሎ የሚያስበው ነገር ደግሞ አለው። ኤጀንቶች በየቦታው እንዲኖሩት ይፈልጋል። ይሄ ትልቅ የሆነ የቢዝነስ አመለካከት ነው። እግዚአብሔር በጣም ኢኮኖሚካል የሆነ አምላክ ነው። የሚያወጣውን ወይም የሚከፍለውን ዋጋ የሚያክል ምላሽ ይፈልጋል። ለምሳሌ የኛ ዋጋ አንድ ሰው “ነብሱን ቢያጎድልና አለምን ቢያተርፍ ምን ይጠቅመዋል” ሲል የአንድ ነፍስ ዋጋ በእግዚአብሔር ዘንድ ጠቅላላ አለም ተደምሮ ከአንድ ሰው ነፍስ እንደማይበልጥ ያሳየናል። አሁን እኛ እንደሱ እናስብ አናስብ አላቅም። ቢዝነሳችሁ ከአንድ ሰው ነፍስ ይበልጣል? እናንተ ቢዝነስ ውስጥ የአንድ ሰው ነፍስ ዋጋው ስንት ነው? ለእግዚአብሔር የአንድ ነፍስ ዋጋ፤ ልጁን በመላክ፤ የልጁን ህይወት በመሰዋት ያተረፈው ነው። ይሄ አለም ሁሉ የሚያልቀው በነጩ ዙፋን ፍርድ እግዚአብሔር ቢዝነሱን ሁሉ የሚዘጋበትና አዲስ የቢዝነስ አቅጣጫውን ወይም ደግሞ አዲስ ሰማይ እና አዲስ ምድር በሚለው መንገድ የሚጀመርበት ነው ።
በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 25 ላይ እንደተገለጸው የመክሊት ምሳሌ፣ ለእያንዳንዳችን እንደ አቅማችን የተሰጠን ሀብት፣ እውቀትም ሆነ ንግድ የባለቤትነት መብት ሳይሆን እግዚአብሔር በባላደራነት የሰጠንና ነግደን እንድናተርፍበት የሚፈልገው ልዩ ጥቅም (previlage) ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ በአቋራጭ ጥቅም ለማግኘት መርህን በመጣስ፣ ሃሳብን በመሸጥ እና ራስን በማክበር ላይ የተመሰረተ የጠላት የንግድ መንገድ አለ። በትንቢተ ሕዝቅኤል 28 ቁጥር 12 ጀምሮ እንደተጻፈው፣ ሰይጣን (በጢሮስ ንጉስ ተመስሎ የተገለጸው) የተሰጠውን ግዛት በማበላሸቱና "በንግድህ ብዛት ግፍ ውስጥህ ተሞላ" በተባለው መሰረት ንግዱን ለራሱ ክብር ስላዋለ ከእግዚአብሔር ተራራ ተጥሏል። ይሄው ነጋዴ በዘፍጥረት 3 ላይ ለአዳምና ሔዋን የተሳሳተ አስተሳሰብን በመሸጥ ከሰጣቸው ሰፊ ቦታ እንዲያጡ አድርጓቸዋል።
በንግድ እና በሀብት ዙሪያ ያለውን መንፈሳዊ ውጊያ በደንብ ለመረዳት የመጽሐፈ ኢዮብ ታሪክን ማየት እንችላለን። ሰይጣን በምድር ላይ ዞሮ ሲመጣ እግዚአብሔር ስለ ኢዮብ ጽድቅ እና ቅንነት ሲነግረው፣ ሰይጣን ግን ኢዮብ እግዚአብሔርን የሚፈራው በከብቱ እና በሀብቱ ዙሪያ በተሰራለት አጥር ምክንያት እንደሆነ ተከራከረ። እግዚአብሔር አጥሩን ሲያነሳለት እና ህይወቱን ብቻ ሲተውለት፣ ሰይጣን የኢዮብን ሀብት በአንድ ቀን ሊያጠፋው ችሏል። ይህ የሚያሳየው ጠላት የሀብታችንን አድራሻ ጠንቅቆ እንደሚያውቅ እና በንግድ አለም ውስጥ ትልቅ መንፈሳዊ ኦዲት እና ፈተና እንዳለ ነው። በተመሳሳይ በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 4 ላይ ሰይጣን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ረጅም ተራራ አውጥቶ የአለምን መንግስታት ክብር ሁሉ አሳልፎ እንደሚሰጠው ቃል ገብቶ እንዲሰግድለት ሲፈትነው እንመለከታለን። ኢየሱስ ግን በአቋራጭ ሀብት ከማግኘት ይልቅ "ለጌታ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ" በማለት አቋሙን በማሳየት በእግዚአብሔር መንገድ ንግዱን ቀጥሏል።
ስለዚህ በእውነተኛ ስኬታማ መንገድ የቢዝነስ ለመገንባት በንግዳችን ውስጥ የሶስት ነገሮችን ትክክለኛ ተዋረድ መጠበቅ ግዴታ ነው። እነዚህም እግዚአብሔር፣ ሰው እና ገንዘብ ናቸው። በማንኛውም ጊዜ እግዚአብሔር ከሁሉ በላይ ሊሆን ይገባዋል፤ ከላይ ካልሆነ በስተቀር ሌላ ቦታ የለውም። በሁለተኛ ደረጃ ሰውን ከመካከል በማድረግ፣ "ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ" በሚለው መርህ ሰውን ማክበር እና መውደድ ያስፈልጋል። ሰራተኞችንም ሆነ ደንበኞችን ከእኛ በታች አድርገን ባሪያ ማድረግም ሆነ ከእግዚአብሔር በላይ ጌታ ማድረግ አይፈቀድም። ገንዘብ ደግሞ ሁልጊዜም ከታች ሆኖ እንደ መሳሪያ (Tool) ብቻ ሊያገለግለን ይገባል፤ ምክንያቱም ገንዘብ በባህሪው ከመሃል መሆን ስለማይችል ወይ ባሪያ ነው ወይ ጌታ ነው።
ይህንን ተዋረድ የጠበቀ ቢዝነስ ጌታ "እናንተ የአለም ብርሃን እና የምድር ጨው ናችሁ" ባለው መሰረት በማህበረሰቡ ውስጥ ትልቅ ሃላፊነትን መወጣት ይችላል። የንግዳችን ብርሃንነት የሚታየው በንግዳችንን አቋም፣ መርህ እና ስነ-ምግባር (Ethics) ሲሆን፣ ዋጋ የሚያስከፍል ነገር ቢመጣም እውነትን አለመተው እና አለማመቻመችን ያመለክታል። በሌላ በኩል የንግዳችን ጨውነት ማለት ነው። ልክ ጨው ምግብ ውስጥ ገብቶ ሟምቶ እንደሚያጣፍጥ፣ ንግዳችንም ማህበረሰቡ ውስጥ ገብቶ የሰዎችን ችግር መፍታት፣ ሰዎችን ማገልገል እና ጠቃሚ መሆን ማለት ነው። እውነትን ሳንጥስ ሰዎችን የሚያገለግል ተቋም መፍጠር የዘመኑ ትልቁ የንግድ ጥሪ ነው።

EBN Ethiopia Mindset Matters በሚል ርዕስ ባዘጋጀው ለባለሙያዎችና ነጋዴዎች በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ከቀረበው ከዶክተር ምህረት መልእክት የተወሰደ | ሙሉ መልእቱን በሚከተው መስፈንጠሪያ ያገኙታል
https://youtu.be/pCJ4tMuFwQg

MindSet-ማይንድሴት

21/06/2026

መልካም ፖድካስት፣ የእግዚአብሔርን ሥራ የሚተርክ እና የሕይወት መንገድን የሚያመለክት አዲስ ሳምንታዊ የክር...

አሁን የምናጸባርቀው አቋም የቆየ አቋም ነው፤ አልተቀየረም፡፡ ምክንያቱም ከአስራ ምናምን አመት በፊት በእነዚህ በሐዋርያት፣ በነቢያት ጉዳይ ሆነ በሌሎች የቃልእምነት እንቅስቃሴዎች ላይ የነበረ...
09/06/2026

አሁን የምናጸባርቀው አቋም የቆየ አቋም ነው፤ አልተቀየረም፡፡ ምክንያቱም ከአስራ ምናምን አመት በፊት በእነዚህ በሐዋርያት፣ በነቢያት ጉዳይ ሆነ በሌሎች የቃልእምነት እንቅስቃሴዎች ላይ የነበረን አቋም ነው፡፡ አዲስ ዛሬ ያወጣነው አይደለም፡፡ ነገር ግን የእኛ ፕሬዝዳንቶች የካውንስል፣ ፕሬዝዳንት ሲሆኑ እዚያ ጋ የሚመሩት ካውንስሉን ነው፡፡ ካውንስሉ ደግሞ ቃለ ህይወት ብቻ አይደለም፤ መካነ ኢየሱስ ብቻ አይደለም፤ ሁሉም አለ፡፡ ስለዚህ የቃለህይወትን አጀንዳና የቃለ ህይወትን ትምህርት እዚያ ላይ ማስረጽና የመጫን መብት የላቸውም፡፡ የካውንስሉ ተወካይ ናቸው፡፡

በየስብሰባዎቻችን ችግሮችን ለማስተካከል፣ መጥፎና ትክክል ያልሆኑ ልምምዶች፤ ካውንስሉ ያወጣውን የስነምግባር መመሪያ የጣሱ ሰዎችን የማረም እርምጃዎች ይደረጋሉ፣ ውይይቶችም ነበሩ፡፡ ግን ብዙ መፍትሄ አላመጡም፡፡ ስለዚህ መንፈሳዊ ነገሮች ይውጡና አስተዳደር ነገር ላይ ትኩረት ይደረግ እያልን ግፊት ብናደርግም፤ እሱ አልሆነም፡፡ አሁንም መንፈሳዊውም አለ፤ ሌላውም አለ፡፡ ያ ደግሞ ብዙ ግራ መጋባት እየተፈጠረ ስለመጣ ከዚህ በላይ ዝም ማለት የለብንም፡፡ በቃ መስመሩን ማስመር ነበረብን፡፡ ካውንስሉ ያስፈልገናል አብረን መሆናችን የጠቀሙ ነገሮች አሉ፡፡ ግን ያ ማለት እኛና ካውንስሉ ውስጥ ያለ አባል በሙሉ በሁሉም መሰረታዊ እምነት እንስማማለን ማለት አይደለም፡፡ ስለዚህ እኛና እነሱን አብራችሁ አይታችሁ ነገ አውጥተን ሐዋርያትና ነቢያት የዘመኑን አገልግሎት አንቀበልም ስንል ህዝቡ መደናገጥ የለበትም፡፡

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤም አለ፡፡ አሁን ካውንስሉ ሁላችንም ወክሎ ከመግባቱ በፊት ከሙስሊም ወገኖቻችን፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ፣ ከካቶሊክ፣ ከሌሎችም ጋር ቃለ ህይወት፣ መካነ ኢየሱስ አብረን ቁጭ እንል ነበረ፡፡ የምንነጋገርባቸው ጉዳዮች ዶክትሪናል ጉዳዮች አይደሉም፡፡ በሀገር ጉዳይ፣ በሰላም ጉዳይ፣ በሌላ ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ ከማንም ጋር እንደዚያ አይነት እንደየሁኔታው ምናደርጋቸው ነገሮች አሉ፡፡ ካውንስሉም ቢሆን ሁሉም መጽሐፍ ቅዱስ ስለያዘና ሁሉም ወንጌላውያን ነን ስላለን ብቻ የሚሆን ነገር ስላልሆነ፤ አንድ ላይ በምንሰራቸው ነገሮች አብረን እንስራ፡፡ ከዚያ ውጪ በሆነ ነገር ግን የምንለይበትን በግልጽ መናገርና ማስተማር አለብን፡፡

ድሮ በሰባዎቹ በሰማኒያዎቹ አካባቢ፣ በየቤቱ የነበሩ ቴፖች ነበሩ። ሳንዮ (Sanyo)፣ ሶኒ (Sony)፣ ፓናሶኒክ (Panasonic) ምናምን የሚባሉ በየቤቱ ነበሩ፣ እንዲያውም ዳንቴል ለብሰው...
09/06/2026

ድሮ በሰባዎቹ በሰማኒያዎቹ አካባቢ፣ በየቤቱ የነበሩ ቴፖች ነበሩ። ሳንዮ (Sanyo)፣ ሶኒ (Sony)፣ ፓናሶኒክ (Panasonic) ምናምን የሚባሉ በየቤቱ ነበሩ፣ እንዲያውም ዳንቴል ለብሰው እንደትልቅ የቤት ዕቃ ይቀመጡ ነበር። ሬዲዮም፣ ቴፕም አላቸው።

ግን የቴፕ ማጫወቻው ብዙ ጊዜ ቶሎ ይበላሻል። ክር ይነክሳል፣ ይጎለጉላል፣ መጎተት ይጀምራል፣ 'አልማዙ ተበላሸ' ይባላል። ከዛ መስራት ያቆማል። መስራት አቁሞም ግን፣ ሰዎቹ ወደ ሰሪ ቤት አይወስዱትም።
ለምን ብለሽ ብትጠይቂ፣ ሬዲዮው ይሰራል። ስለዚህ ቪኦኤ (VOA) ይሰሙበታል፣ ዶይቼ ቬሌ (DW) ይሰሙበታል፣ የኢትዮጵያ ሬዲዮ ይሰሙበታል፤ ስለዚህ ቴፑ 'ይሰራል' ተብሎ ነው የሚታሰበው፣ ይጫወታል። ነገር ግን ተበላሽቷል።

ለምንድነው ይሄ የሆነው? ሁለት ስራ ስላለው፣ አንደኛው ስለሚሰራ የአንደኛው መበላሸት ብዙ ትኩረት አልተሰጠውም።

አእምሯችን ልክ እንደዚህ ነው። የሰው አእምሮ ሁለት ክፍሎች አሉት። አንደኛው ማወቂያ ነው። ይሄንን ተወልደን የገባንበትን፣ ተፈጥረን የገባንበትን፣ ይሄን የምንኖርበትን ዓለም የምናውቅበት ነው። ሁለተኛው ግን፣ መንፈስ የሆነውን እግዚአብሔርን፣ ወይም መንፈሳዊውን ዓለም የምናውቅበት ነው። እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥረው መጀመሪያ ላይ ሁለቱም ፋኩልቲ (faculty)፣ ሁለቱም አቅም (capacity) እንዲኖረው አድርጎ ነው የፈጠረው።

ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን፣ በዘፍጥረት ምዕራፍ 3 ላይ፣ ሰው በኃጢያት፣ በእምቢተኝነት፣ በእልከኝነት፣ በሰይጣን ተንኮል፣ በሄዋን መታለል አዳም በወደቀበት ጊዜ፣ መንፈሳዊ ሞትን ነው የሞተው። ስለዚህ አንደኛው ጨልሟል፣ ታውሯል፤ ሰው እግዚአብሔርን ሊያውቅ የሚችልበት የአእምሮው ክፍል ተበላሽቷል።

ግን ሁለተኛው፣ ሰው ዓለም የሚያውቅበት ስለሚሰራ፣ እንደዛ ቴፕ መበላሸቱ ብዙ አልታወቀውም። ሰው ደግሞ መታመሙን ካላወቀ ሀኪም ጋር ሊሄድ አይችልም፤ እቃው መበላሸቱን ካላወቀ ሰሪ ጋር ሊወስደው አይችልም። አንድ ነገር የሚታደሰው ሲበላሽ ነው፣ መበላሸቱ ሲታወቅ ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ ላይ፣ በተለይ ሐዋርያው ጳውሎስ ሮሜ ምዕራፍ 1 ላይ፣ እንዲሁም ደግሞ 1ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 1 ላይ፣ ስለዚች አለም ጠቢባንና ሊቃውንቶች፣ መርማሪዎች፣ ጥበበኞች ሲናገር የሚጠራቸው አጠራር በጣም ይገርመኛል። 'ጥበበኛ ደንቆሮ' ብሎ ይጠራቸዋል፣ 'ጥበበኛ ሞኞች' ብሎ ይላቸዋል።

ለምንድነው እንዲህ የሚለው ብለን ብንጠይቅ፣ ለካ አንደኛው ክፍል ይሰራል። ስለሚሰራ ምድርን ይመረምራሉ፣ ዙሪያ-ገባቸውን ያውቃሉ፣ እንዲያውም ይፈላሰፋሉ፣ ይራቀቃሉ። ስለዚህ ከዛ አንፃር ጥበበኞች ይላቸዋል። ነገር ግን እግዚአብሔርን ሊያውቁበት፣ መንፈሳዊውን ዓለም፣ የተፈጠሩበትን አላማ ሊረዱበት የሚችሉበት ያ ማወቂያ ግን ተቃጥሏል። በዛ ረገድ ሞኞች ናቸው። ስለዚህ ጥበበኛ ሞኝ፣ ጥበበኛ ደንቆሮ ብሎ ይጠራቸዋል። ለዚህ ነው ሰዎች ችግራቸውን፣ መታመማቸውን ቶሎ የማይቀበሉትና ወደ ሰሪው፣ ወደ አዳሹ የማይሄዱት።

እግዚአብሔር ፈጣሪ ብቻ ቢሆን ኖሮ ጉዳችን ፈልቶ ነበር። እግዚአብሔር ግን አዳሽም ነው። ስለዚህ የሰራው ነገር ቢበላሽ መልሶ የሚያድስ ነው። 'እነሆ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ' አይደል ያለው? ስለዚህ እኔ ለሰው ልጅ መንፈሳዊም፣ አእምሮአዊም፣ አካላዊም ችግር (ተግዳሮት) መፍትሄው ወደ ሰሪው መውሰድ ነው ብዬ አምናለሁ።

Evangelist Yared Tilahun

የአናን የወተት እና እርሻ (Anan Diary Farm) መስራች ከሆነው ከእስክንድር ዮሴፍ ጠቃሚ የልምድ ልውውጥ ያድርጉ :: 📅 ቀን፦ ሰኔ 6፣ 2018 (June 13, 2026)⏰ ሰዓት፦ 1:...
05/06/2026

የአናን የወተት እና እርሻ (Anan Diary Farm) መስራች ከሆነው ከእስክንድር ዮሴፍ ጠቃሚ የልምድ ልውውጥ ያድርጉ ::
📅 ቀን፦ ሰኔ 6፣ 2018 (June 13, 2026)
⏰ ሰዓት፦ 1:30 ጠዋት (7:30 AM)
📍 ቦታ፦ ማሪዮት ሆቴል (Marriott Hotel)፣ አዲስ አበባ
ለመመዝገብ :- https://ebnethiopia.org/index.php/next-event

Don't miss this upcoming Heaven on Business networking breakfast featuring an exclusive experience-sharing session with Eskender Yoseph (Anan Diary Farm) .
Join us at the Marriott Hotel on June 13, 2026, at 7:30 AM

ከሁለት ሳምንት በኋላ እንገናኝ! ⏳ቅዳሜ ሰኔ 6 2018 ዓ.ም ማለዳ 1:30 ሰዓት በማሪዮት ሆቴል የአስተሳሰብ ለውጥ ለስኬታማ ህይወት! ከዶ/ር ምህረት ደበበ ጋር የሚኖረንን ልዩ የቁርስ፣ ...
31/05/2026

ከሁለት ሳምንት በኋላ እንገናኝ! ⏳
ቅዳሜ ሰኔ 6 2018 ዓ.ም ማለዳ 1:30 ሰዓት በማሪዮት ሆቴል
የአስተሳሰብ ለውጥ ለስኬታማ ህይወት! ከዶ/ር ምህረት ደበበ ጋር የሚኖረንን ልዩ የቁርስ፣ የፀሎት እና የኔትወርኪንግ ፕሮግራም ለመታደም የቀረን 2 ሳምንት ብቻ ነው።
አሁኑኑ ይመዝገቡ! bit.ly/4nWsNnt
አዘጋጅ : የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን ነጋዴዎች ኔትወርክ (EBN ETHIOPIA )
ለበለጠ መረጃ :0961434445

29/05/2026
ይቅርታ እጠይቃለሁ!ሰዶማውያን ከሆኑ ወይም በፅንሰ ዐሳብ ደረጃ ሰዶማዊነትን ከሚደግፉ ሰዎች:—(1)   ስጦታዎቻቸውን ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ በድፍን ቅል መቀበል እንችላለን፣ የሚል እምነት ድ...
28/05/2026

ይቅርታ እጠይቃለሁ!

ሰዶማውያን ከሆኑ ወይም በፅንሰ ዐሳብ ደረጃ ሰዶማዊነትን ከሚደግፉ ሰዎች:—

(1) ስጦታዎቻቸውን ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ በድፍን ቅል መቀበል እንችላለን፣ የሚል እምነት ድሮም አልነበረኝም ዛሬም የለኝም።
የእኔ አቋም የነበረው:—

(2) ቢያንስ በንድፈ ዐሳብ ደረጃ፣ ስጦታዎች አስገዳጅ ጫና ካልተደረገባቸው (no hidden obligations) መቀበል እንችላለን የሚል ዐሳብ ነበር። ብዙ አስተያየት ሰጪዎችና ኂስ አቅራቢዎች ይህን በውል የተረዱልኝ አልመሰለኝም።

አንዳንድ ወንድሞች በፅንሰ ዐሳብ ደረጃ ካልሆነ በቀር፣ ይህ ጫና ያልተደረገበት ስጦታ በምንኖርበት ዓለም እውን ሊሆን እንደማይችል አስረድተውኛል። ስለዚህ በምንኖርበት ዓለም ከሰዶማውያን ወይም ሰዶማዊነትን ከሚደግፉ ሰዎች፣ አንዳችም ስጦታ መቀበል እንደማንችል ግልጽ ሆኖልኛል። ስለዚህ ከዚህ በፊት የነበረው አቋሜ በዚህ አግባብ እንደ ተስተካከለ እንድታውቁት በትልቅ አክብሮት እጠይቃለሁ።
ይህ እንዳለ ሆኖ፣ ይህን ርእሰ ጒዳይ ያነሣሁት፣ ለውይይት በሚል እንጂ የትኛውንም ወገን ለማስደሰትም ሆነ ለማስከፋት አይደለም።

ከወገንተኝነት ተነሥቶ ነው፣ የሚሉ አስተያየቶች ስሕተት ናቸው። እንደ እውነቱ ከሆነ የመካነ ኢየሱስ መሪዎችንም ሆነ የመሠረተ ክርስቶስ መሪዎችን አላውቃቸውም። እንወያይበት የሚለውን ጒዳይ ያመጣሁት በፍጹም ቅን ከሆነ ኅሊና በመነጨ መንገድ ነው።

ዘጠና ከመቶ (90%) የሚሆነው የአገልግሎቴ ዕገዛ የሚመጣው ከቤተሰቤ ሲሆን፣ ዐሥር ከመቶ (10%) የሚሆነው ደግሞ ከሁለት ኢትዮጵያውያን አብያተ ክርስቲያናትና አገልግሎቴን ከሚደግፉ ጥቂት ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ነው።

ይህ እንዳለ ሆኖ ርእሰ ጒዳዩን በማንሣቴ ያዘናቹ ወንድሞቼንና እኅቶቼን ይቅርታ እጠይቃለሁ።

Tesfaye Robele

Address

Dembel City Center 12th Floor
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Semayawi Thought posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Semayawi Thought:

Shortcuts

Share