የክርስቶስ ደቀመዝሙር

የክርስቶስ ደቀመዝሙር " ... እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እ? Disciple of Christ page

  ፲፩/11   #ሀሙስ(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20)27፤ ከዚያም በኋላ ቶማስን። ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለ...
26/02/2026

፲፩/11 #ሀሙስ

(የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 20)

27፤ ከዚያም በኋላ ቶማስን። ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤ እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው፤ ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን አለው።

28፤ ቶማስም። ጌታዬ አምላኬም ብሎ መለሰለት።

መልካም ቀን!

  ፲/10   #ረቡዕ" ከሂሶጵ ቅጠልም ጭብጥ ውሰዱ፥ በዕቃ ውስጥ ባለውም ደም ንከሩት፥ በዕቃውም ውስጥ ካለው ደም ሁለቱን መቃኖችና ጉበኑን እርጩ፤ ከእናንተም አንድ ሰው ከቤቱ ደጅ እስኪነጋ...
25/02/2026

፲/10 #ረቡዕ

" ከሂሶጵ ቅጠልም ጭብጥ ውሰዱ፥ በዕቃ ውስጥ ባለውም ደም ንከሩት፥ በዕቃውም ውስጥ ካለው ደም ሁለቱን መቃኖችና ጉበኑን እርጩ፤ ከእናንተም አንድ ሰው ከቤቱ ደጅ እስኪነጋ ድረስ አይውጣ።"
(ኦሪት ዘጸአት 12:22)

እስራኤላዊያን በግብፅ ሳሉ የበራቸው መቃን ላይ የጠቦት ደም በመቀባት የሞት መለአክን አምልጠዋል ፤ እኛ የአዲስ ኪዳን ነዋሪዎችን ግን ከከበበን የዘለአለም ሞት የሚያስመልጠን የክርስቶስ ደም ነዉ፡፡


ደሙ በመቃኔ ላይ ስለተቀባ
ደሙ በጉበኔ ላይ ስለተቀባ
ሞት አለፈ ሄደ እራቀ ከእኔ ጋር
የጌታዬን ደም አይቶ
የኢየሱሴን ደም አይቶ (፪x)
ሞት አለፈ ፣ ሞት አለፈ ሄደ ከእኔ ርቆ

የሞት መልአክት አያስፈራኝ
ተሸፍኛለሁ አያገኘኝ (፪x)
ዙሪያዬ ከደሙ ታጥሯል
ያን ቅጥር አልፎ እንዴት ይገባል (፪x)

መልካም ቀን!

  ፱/9   #ማክሰኞ" በታላቅም ድምፅ። የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል አሉ።"(የዮሐንስ ራእይ 5:12)ክብርክብርክብርክብር ...
24/02/2026

፱/9 #ማክሰኞ

" በታላቅም ድምፅ። የታረደው በግ ኃይልና ባለ ጠግነት ጥበብም ብርታትም ክብርም ምስጋናም በረከትም ሊቀበል ይገባዋል አሉ።"
(የዮሐንስ ራእይ 5:12)

ክብር
ክብር
ክብር
ክብር
መስዋዕት ሆኖ ላዳነን ለጌቶች ጌታ ለነገስታት ንጉስ ኢየሱስ ይሁን ፡፡

መልካም ቀን !

  ፰/8   #ሰኞ  !" ሙሴም የእስራኤልን ሽማግሌዎች ጠርቶ አላቸው። በየቤታችሁ ጠቦት ምረጡ፥ ወስዳችሁም ለፋሲካ እረዱት።"(ኦሪት ዘጸአት 12:21)በብሉይ ኪዳን የሞት መለአክን በር መቃን...
22/02/2026

፰/8 #ሰኞ

!

" ሙሴም የእስራኤልን ሽማግሌዎች ጠርቶ አላቸው። በየቤታችሁ ጠቦት ምረጡ፥ ወስዳችሁም ለፋሲካ እረዱት።"
(ኦሪት ዘጸአት 12:21)

በብሉይ ኪዳን የሞት መለአክን በር መቃን ላይ የጠቦት ደም በመቀባት አምልጠዋል ፤ እኛ የአዲስ ኪዳን ነዋሪዎች ግን በእኛ ላይ ያለዉ ከዘለአለም ሞት የሚያስመልጠን የክርስቶስ ደም በእኛ ላይ አለ፡፡

ደሙ በመቃኔ ላይ ስለተቀባ
ደሙ በጉበኔ ላይ ስለተቀባ
ሞት አለፈ ሄደ እራቀ ከእኔ ጋር
የጌታዬን ደም አይቶ
የኢየሱሴን ደም አይቶ (፪x)
ሞት አለፈ ፣ ሞት አለፈ
ሄደ ከእኔ ርቆ

መልካም ቀን !

  ፯/7 እሁድ" በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው። እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል።"(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2:14)ኢየሱስ ክ...
22/02/2026

፯/7 እሁድ

" በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው። እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል።"
(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2:14)

ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰዉ ልጆች ሁሉ በደል ሲሰቀል ከኛ ላይ ያልገፈፈልን ነገር አልነበረም ፡፡ የዘላለም ሞታችንን ፣ አበሳችንን መከራችንን ስቃያችንን እንዲሁም በበደላችን ምክንያት የነበረብንን የዕዳ ጽሕፈት አንድ ሳያስቀር በሱ በማመናችን ብቻ አስወገደልን ፡፡ ክብር ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ አንድ አምላክ ይሁን፡፡

መልካም ሰንበት!

  ፮/6 ቅዳሜ" ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።"(የዮሐንስ ወንጌል 3:14-...
22/02/2026

፮/6 ቅዳሜ

" ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።"
(የዮሐንስ ወንጌል 3:14-15)

እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ጊዜ ህዝቡን ከስጋ ሞት ሊያድን ሙሴን የነሀሱን እባብ በመስቀል ላይ እንዲሰቅል አደረገ ፡፡ ያንን የተሰቀለ እባብ ያየ ሁላ ከስጋዉ ሞት ይድን ነበር ፡፡ በእርግጥ በመስቀል ላይ የተሰቀለዉ እባብ የሚወክለዉ እርግማንንን ሀጢያትን ክፋትን በደልን ነበር ፡፡

በሚሻለዉ በአዲሱ ኪዳን ግን እግዚአብሔር ህዝቡን ከስጋዊ ሞት ሳይሆን ከስጋ ሞት ከሚከፋዉ ዘላለማዊ ሞት ሊያድን አንድያ ልጁን በመስቀል ላይ እንዲሞት ወሰነ ፡፡ ኃጢያት የማያዉቀዉንም ቅዱስ ልጁን በመስቀል ላይ ስለሁላችን በደል ኃጢያት አርጎ ስለኛ ክፋት እኛን ለማዳን ሰቀለዉ ፡፡

ማጣቀሻ

(ኦሪት ዘኍልቍ ምዕራፍ 21)

6፤ እግዚአብሔርም በሕዝቡ ላይ እባቦችን ሰደደ፥ ሕዝቡንም ነደፉ፤ ከእስራኤልም ብዙ ሰዎች ሞቱ።

7፤ ሕዝቡም ወደ ሙሴ መጥተው። በእግዚአብሔርና በአንተ ላይ ስለ ተናገርን በድለናል፤ እባቦችን ከእኛ ያርቅልን ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይልን አሉት።

8፤ ሙሴም ስለ ሕዝቡ ጸለየ። እግዚአብሔርም ሙሴን። እባብን ሠርተህ በዓላማ ላይ ስቀል፤ የተነደፈውም ሁሉ ሲያያት በሕይወት ይኖራል አለው።

9፤ ሙሴም የናሱን እባብ ሠርቶ በዓላማ ላይ ሰቀለ፤ እባብም የነደፈችው ሰው ሁሉ የናሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ።

2ኛ ወደ ቆሮንቶስ 5:21

እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
መልካም ቀን!

  ፭/5 አርብ" እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል። "(ወደ ዕብራውያን 9:28...
22/02/2026

፭/5 አርብ

" እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ፥ የብዙዎችን ኃጢአት ሊሸከም አንድ ጊዜ ከተሰዋ በኋላ፥ ያድናቸው ዘንድ ለሚጠባበቁት ሁለተኛ ጊዜ ያለ ኃጢአት ይታይላቸዋል። "
(ወደ ዕብራውያን 9:28)

በኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት አምነን ለዳንን እኛ ፦ በአብ ዘንድ ሁልጊዜ የሚታይልን ዘራችን ፣ ቋንቋችን ፣ የትምህርት ደረጃችን ፣ የሀብት መጠናችን ፣ የጤና ሁኔታችን ሳይሆን ስለኛ እንደተሰቀለ ያመነዉ ክርስቶስ ነዉ ፡፡ እሱ ደግሞ በእግዚአብሔር አብ ፊት ቅዱስ መስዕዋትና ለእኛ ጠበቃ ነዉ ፡፡

መስቀሉን ስናስብ ፍቅሩን እናስታዉስ ፤
መስቀሉን ስናይ የተከፈለልንን አንርሳ ፤
ይህ ሁሉ ስቃይ ፣ ይህ ሁሉ መከራ በአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የደረሰዉ እኛን ከዘላለም ፍርድ ለማዉጣት ስለኛም በአብ ፊት በፍፅምና ለመታየት ነዉ ፡፡

መልካም ቀን!

  ፬/4 ሀሙስ" የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥   ።"(ወደ ዕብራውያን 12:24)በመስቀል ላይ የፈሰሰልን ደም ተራ የአንድ ሰዉ ደም ብቻ አይደለም በመስቀል ላይ የፈሰሰዉ ...
22/02/2026

፬/4 ሀሙስ

" የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ።"
(ወደ ዕብራውያን 12:24)

በመስቀል ላይ የፈሰሰልን ደም ተራ የአንድ ሰዉ ደም ብቻ አይደለም በመስቀል ላይ የፈሰሰዉ ደም አምላክ ሰዉ ሁኖ ስለኛ መተላለፍና በደል የከፈለዉ ዋጋ እንጂ ፡፡ ይህ ደም እንደ ዋዛ ፈሶም የቀረ ደም አይደለም ይልቁንስ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር
ስለ ምህረት ፣ ይቅርታ ስለኛ የሚጮህ ነዉ ፡፡

" አለውም። ምን አደረግህ? የወንድምህ የደሙ ድምፅ ከምድር ወደ እኔ ይጮኻል። "
(ኦሪት ዘፍጥረት 4:10)

በእርግጥ ቃየን ወንድሙ አቤልን ሲገለዉ የአቤል ደም ስለ ራሱ ፍትህ ወደ እግዚአብሔር ይጮህ ነበር በመስቀል ላይ ስለኔና ስለናንተ የፈሰሰዉ የንጉሳችን ኢየሱስ ደም ግን ስለ ራሱ ሳይሆን ስለኛ ምህረትና ይቅርታ ዘወትር ይጮኸል ፡፡ በእርግጥ እግዚአብሔር ከአቤል ይልቅ ለሚጮኸዉ ደም እንዴት ምህረቱን በኢየሱስ በኩል ለህዝቡ አይሰጥ???!
መልካም ቀን!

  ፫/3 ረቡዕ" አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ   ።"(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2:13)ሰዋች ሁላ በኃጢአታችን ምክንያት የቁጣ ልጆች የነበርን ሲሆን ከእግዚአብሔር ክብር ርቀን በመከ...
18/02/2026

፫/3 ረቡዕ

" አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ ።"
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2:13)

ሰዋች ሁላ በኃጢአታችን ምክንያት የቁጣ ልጆች የነበርን ሲሆን ከእግዚአብሔር ክብር ርቀን በመከራ በሀዘን እንኖር ነበር ፡፡ ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ስለ በደላችንና ስለ መተላለፋችን ባፈሰሰልን ደም ወደ እግዚአብሔር ክብር መቅረብ ሆነልን ይህም ሳይበቃ የእግዚአብሔር ወራሽ አደረገን ደግሞም እግዚአብሔርን እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብርም እየለወጠን ልጆቹ አደረገን፡፡

ድሮ ለእግዚአብሔርም ሆነ ለእርሱ ሕዝቦች ባዳ ሁነን እንኖር ነበር አሁን ግን ቤተኛ ብሎም ልጆች ሁነናል ፡፡

እዩት ኢየሱስን መስቀሉ ማማሩ
ለተመራመረዉ ብዙ ነዉ ሚስጥሩ !

በእዉነት ለሰዉ ልጆች በመስቀል ላይ የተሰራዉ ስራ ከመረዳት ያለፈና የሰዉ ልጅ ታሪክን ላንዴና ለመጨረሻ የቀየረ ስራ ነዉ ፡፡ በመስቀል ላይ በክርስቶስ ያየነዉ ፍቅር ለስፋቱ ድንበር ፣ ለጥልቀቱ መድረሻ የሌለዉ እጅግ በጣም ሰፊ የሆነ ነዉ ፡፡ መልካም ቀን!

18/02/2026

፪/2 ማክሰኞ

" ... ።"
(1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:7)

ከአዳም ጀምሮ የሰዉ ልጅን ባሪያ አርጎ ሲገዛ የነበረዉ ፣ ወደማይፈልግበት የሚነዳዉ ትልቁ የሰዉ ልጅ ጠላት ኃጢያት ነበር ፡፡ ኃጢያት ደግሞ የሚሰራ ብቻ ሳይሆን የሰዉ ማንነት ሆኖ ሰዉን ከአምላኩ አጣልቶ ከወንድሙ አባልቶ የሰዉ ልጆችን ሁሉ በምድር ያልተገባ ሕይወት እንዲኖሩ የሚያስገድድ ሀይል ነበር፡፡
የሰዉ ልጆች በዘመናቸዉ ከጥንት ጀምሮ ከዚህ ጨቋኝ ገዢ ለመላቀቅ ቢያስቡም የሚቻልና የሚዘለቅ አልነበረም ፡፡ አምላክም ፍጡሩን ስለሚወድ ከዚህ እንዲወጡ የተለያየ መንገድ ሲያዘጋጅላቸዉ እንደነበር መፀሀፍ ቅዱስ ይነግረናል ፡፡ ይሁን እንጂ የሰዉ ልጆች አምላክ የሰጣቸዉን ህግ ለመጠበቅ ሲጣጣሩ ነገር ግን ሳይችሉ ደግሞም መስዋት በማቅረብ ለኃጢአታቸዉ ስርየት ደም ሲያፈሱ እንደነበር ቅዱስ ቃሉ ይነግረናል፡፡

ይህም ሆኖ ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አልተቻለም ፡፡ ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ስለ ሰዋች ሁሉ ኃጢያት መስቀል ላይ ሰዋዉ ፡፡ ልጁም ኢየሱስ ስለኛ ታዞ በመስቀል ላይ ደሙን አፈሰሰልን ይህንንም ደም ይዞ ስለኛ ዘወትር ሊማልድ በአብ ቀኝ ተቀመጠ ፡፡ አሁን በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ ባፈሰሰዉ ደም ኃጢያታቸዉን ሊያነጻ ስለኛ በአብ ዘንድ ጠበቃ ሆኖ ተቀምጧል፡፡

የኢየሱስ ደም ከኃጢያት ሁሉ ያድናል ፡፡ ወንድሜ ፥ በኃጢያት ዉስጥ አለህ ፣ ማንነትህ ኃጢያት ነዉ ? እንግዲያዉስ ኃጢአትህን ሁሉ ሊያነፃ ወደሚችል ወደ ኢየሱስ ተመለስ፡፡

ማመሳከሪያ ጥቅስ ፦" ... ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።"
(ሮሜ 8:34) መልካም ቀን!

  ፩/1 (የመጀመሪያ ቀን) ሰኞ"  ፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።" (ወደ ገላትያ ሰዎች 5:1)ክርስቶስ በሞቱና ትንሳኤዉ ከህግ ቁጥጥርና አድርግ አታድርግ...
16/02/2026

፩/1 (የመጀመሪያ ቀን) ሰኞ

" ፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።" (ወደ ገላትያ ሰዎች 5:1)

ክርስቶስ በሞቱና ትንሳኤዉ ከህግ ቁጥጥርና አድርግ አታድርግ ከሚል ስርአት ወደ ጸጋዉ ሕይወት ነጻ አዉጥቶናል ፡፡

በእርግጥ ሕጉ የሚታዘዙትን (የሚፈፅሙትን) ቢያጸድቃቸዉም የሰዉ ልጅ በሙሉ ግን በፍፅምና ሕጉን መጠበቅ ተስኖት የኃጢአት ባሪያ ሁኖ ሕይወቱን መርቷል ፡፡ ኢየሱስ ግን ራሱ በመስቀል የሁላችንን ኃጢያት ሁኖ ተሰቅሎልን በሕግ ከመጽደቅ ያለ ስራ በፀጋዉ ወደ መፅደቅ ነፃነት ወሰደን ፡፡
፡፡ ከዘላለም ሞትና ፍርድ ነፃ አዉጥቶናል

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የክርስቶስ ደቀመዝሙር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share