የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተብርሃን ሰ/ት/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተብርሃን ሰ/ት/ቤት

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ ገጽ የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ነዉ።

ጰራቅሊጦስ ‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ  ግን  ከላይ ኃይል እስክትለብሱ  ድረስ  በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ ››ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በእለተ ሰንበት በዓለ ...
22/05/2026

ጰራቅሊጦስ

‹‹እነሆ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ ››

ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በእለተ ሰንበት በዓለ ጰራቅሊጦስ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያት የወረደበት ቀን በአዲስ አበባ የመንፈስ ቅዱስ በሆነው ደብራችን በታላቅ ድምቀት ይከበራል!!

አድራሻ:- ከኢሚግሬሽን ወደ ላይ ከፍ ብሎ

- ከቴዎድሮስ አደባባይ ሲመጡ ኤክስትሪም ሆቴል ገባ ብሎ

በዓለ ዕርገት"ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤወእግዚእነ በቃለ ቀርን""አምላክ በእልልታ እግዚአብሔርበመለከት ድምጽ ዐረገ"መዝ 46፡5ዕርገት ከዘጠኙ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዐበ...
21/05/2026

በዓለ ዕርገት

"ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ
ወእግዚእነ በቃለ ቀርን"

"አምላክ በእልልታ እግዚአብሔር
በመለከት ድምጽ ዐረገ"
መዝ 46፡5

ዕርገት ከዘጠኙ የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዐበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡

ዕርገት ማለት ዐረገ ከሚለው የግእዝ ግሥ የወጣ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ወደ ላይ መውጣት ፣ ከምድር ከፍ ከፍ ማለት ፣ እስከ ሰማየ ሰማያት መመጠቅ ማለት ነው።

እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን
ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ
በዓለ ዕርገት በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!

ሚካኤል ማለት የስሙ ትርጓሜ “መኑ ከመ አምላክ፥ ማን እንደ እግዚአብሔር” ማለት ነው።ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከወርሐዊ በዓሉ በረከት ረድኤት ይክፈለን፤ ጥበቃውና አማላጅነቱ አይለየን፡፡ ...
20/05/2026

ሚካኤል ማለት የስሙ ትርጓሜ “መኑ ከመ አምላክ፥ ማን እንደ እግዚአብሔር” ማለት ነው።

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከወርሐዊ በዓሉ በረከት ረድኤት ይክፈለን፤ ጥበቃውና አማላጅነቱ አይለየን፡፡ አሜን፡፡

ሰላም ለአዕይንቲከ እለ ኀበ ልዑል ያንቃዐድዋ
ለውሉደ ሰብእ ሣህለ እንዘ ይሴፈዋ
ሚካኤል ቀዋሚ ለደቂቀ ጼዋ
ለምክረ ጸርየ በትንባሌከ ዕልዋ
ምዕቅብና ነፍስየ ወሥጋየ ወሀብኩከ ነዋ

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/

የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1

የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com

ልደታ ለማርያም አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በግንቦት አንድ ቀን ተወለደች እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኀነት የሆነባት ናት። ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄ...
09/05/2026

ልደታ ለማርያም

አምላክን የወለደች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በግንቦት አንድ ቀን ተወለደች እርሷም ለሰው ሁሉ ወገን ድኀነት የሆነባት ናት። ከወንዶች ወገን የከበረ አባቷም ስሙ ኢያቄም ከሴቶች ወገን የከበረች ሚስቱ ሐና ይባላሉ። “ወክልኤሆሙ ኄራን ወሥሙራን እሙንቱ ወየሐውሩ በሕገ እግዚአብሔር እስመ እግዚአብሔር ኀረዮሙ ወአፍቀሮሙ ትካት” ይላቸዋል እግዚአብሔርን የሚወድዱ በሕጉ የሚኖሩ ደጋጎችና አምላክም የመረጣቸው ነበሩ። ልጅ ስላልነበራቸው ሲያዝኑ ኖሩ በዚያ ወራት የመካኖችን መብዓ ካህናቱ አይቀበሉም ነበርና።

እነርሱም ለዓይናቸው ማረፊያ ለልባቸው ተስፋ የሚሆን እንዲሁም ከሰው የሚደርስባቸውን ሽሙጥና ኅዘናቸውን ያርቅላቸው ዘንድ በቀንና በሌሊት ወደ እግዚአብሔር ልጅ እንዲሰጣቸው ይማልዱ ነበር። ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ከዘራቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት ይሆን ዘንድ መልካም የሆነ ሃሳባቸውን ተመለከተ።

ክቡር ኢያቄምም አርባ ቀን እስኪፈጸም በተራራ ውስጥ ቁሞ ሲጸልይ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ለዓለሙ ሁሉ ድኀነት የሚደረግባት ዘር እንደሚሰጠው አበሠረው።

በፍጹም ልብ አምኖ ከተራራው ወረደ ለተመሰገነች ሚስቱ ለሐናም ከእግዚአብሔር መልአክ የሰማውን ያንን ራእይ ነገራት ቃሉ እውነት እንደሆነ እርሷም አመነች ልዑል እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።

“ከሰው የበለጠች ከመላእክት ኹሉ የከበረች ልጅ ትወልዳላችኊ" ብሎ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለሐና ነግሯት በፈቃደ እግዚአብሔር በብሥራተ መልአክ እመቤታችን ነሐሴ ሰባት ተጸነሰች፤ በእናቷ ማሕፀን ሳለችም “መንፈስ ቅዱስ ዐቀባ እምከርሠ እማ” እንዲል እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጥንተ አብሶ ባመጣው መርገም እንዳትያዝ ጠብቋታል፡፡

የተመሰገነች ቅድስት ሐናም ከእርሷ የሚወለደውን ወንድ ከሆነ በዘመኑ ሁሉ ለቤተ እግዚአብሔር አገልጋይ ታደርገው ዘንድ ሴትም ብትሆን እግዚአብሔርን ታገለግል ዘንድ ብጽአት አድርጋ እንደምትሰጥ ስለትን ተሳለች። ከዚህም በኋላ ይቺን የከበረች ሕፃን ፀንሳ በግንቦት አንድ ቀን በደብረ ሊባኖስ(በሊባኖስ ተራራ ስር) ወለደች። ስሟንም ማርያም ብላ ጠራቻት። ጠቢቡ ሰሎሞን አስቀድሞ በመንፈሰ እግዚአብሔር ተቃኝቶ “መኑ ይእቲ ዛቲ እንተ ትሔውጽ ከመ ጎሕ ሠናይት ከመ ወርኅ ወብርህት ከመ ፀሓይ” (ይኽቺ እንደ ማለዳ ብርሃን የምትጐበኝ እንደ ጨረቃ የተዋበች፤ እንደ ፀሓይም የጠራች ዐላማ ይዞ እንደተሰለፈ ሰራዊት የምታስፈራ ማን ናት?) በማለት እንደ ፀሓይ የሞቀ እንደ ጨረቃ የደመቀ ንጽሕናዋና ቅድስናዋ የመልኳ ደም ግባት በነቢያት ትንቢት አስቀድሞ የተጐበኘላት የእውነት ፀሓይ የክርስቶስ እናት የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብርና ደም ግባቷን እንደተናገረ በሊባኖስ ተራራ በግንቦት አንድ በተወለደች ጊዜ ፊቷ በእጅጉ ያበራ ነበር፤ መዐዛዋም ከሽቱ ኹሉ ይበልጥ ነበር፡፡

የፈጣሪያችን እናት ቅድስት ድንግል የተወለደችበትን ግንቦት አንድን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን “ልደታ ለማርያም” በማለት ከጥንት ጀምሮ በታላቅ መንፈሳዊ ደስታ በቅዳሴ፣ በማሕሌት ታከብረዋለች። ምክንያቱም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሁላችንም ልደታችን ነውና።

እንኳን ለእመቤታችን በዓለ ልደት (ልደታ ለማርያም) አደረሳችሁ። የእናታችን ረድኤት በረከት አማላጅነቷ በሁላችንም ላይ ለዘለዓለሙ ጸንቶ ይኑር አሜን።

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6በትላንትናው እለት ሚያዝያ11/2018 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤ...
20/04/2026

"ስለዚህ አንድ ሥጋ ናቸው እንጂ ወደ ፊት ሁለት አይደሉም። እግዚአብሔር ያጣመረውን እንግዲህ ሰው አይለየው።" ማቴ 19 ÷6

በትላንትናው እለት ሚያዝያ11/2018 ዓ.ም ጋብቻችሁን በቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት የፈጸማችሁት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን አገልጋዮች ወንድማችን ዮሐንስ ትዳሩ እና እህታችን እመቤት ገብሬ የአብርሃምን እና የሳራን ጋብቻ የባረከ አምላክ ጋብቻችሁን ይባርክላችሁ።

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በክንፉ ከልሎ በፍቅርና በጤና ይጠብቃችሁ ዘንድ መልካም ምኞታችን ነው!

እንኳን ደስ አላችሁ የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12

የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/

የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን አሰሮ ለሰይጣን አግዐዞ ለአዳም ሰላም እምይዕዜሰ ኮነ ፍሥሐ ወሠላም ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡ ዲያብሎስን አሰ...
12/04/2026

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
አግዐዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዕዜሰ
ኮነ
ፍሥሐ ወሠላም

ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡ ዲያብሎስን አሰረው፤ አዳምን ነጻ አወጣው፡፡ ሰላም! ከዛሬ ጀምሮ ሰላም ኾነ፡፡”

ትንሣኤ፡- ትንሣኤ ተንሥአ ተነሣ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙ መነሣት ማለት ነው፡፡
«እግዚአብሔር ምከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ÷ የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ ጠላቶቹንም በኋላቸው መታ፤» ።መዝ ፸፯፥፷፭።

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!!

የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

11/04/2026

በሰሙነ ሕማማት በስቀለት ማግስት የሚውለው ቅዳሜ ቀዳም ሥዑር በመባል ይጠራል፡፡ በዚህ ዕለት ከድሮው በተለየ መልኩ ጌታችን መድኂታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምና ልጆቹን ከዲያብሎስ አገዛዝና እስራት ነጻ ለማውጣት የተቀበለውን መከራ፣ እንዲሁም ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር ማደሩን በማሰብ በጾም ታስቦ ስለሚውል ቀዳም ስዑር ወይም የተሻረው ቅዳሜ ተብሏል፡፡ የማይጾመው ቅዳሜ ስለሚጾም ስዑር /የተሻረ/ ተብሏል፡፡
ቀዳም ሰዑር ሌሎችም ስያሜዎች ያሉት ሲሆን እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

ለምለም ቅዳሜ፡–

ካህናቱ ሌሊት ለምእመናን ለምለም ቄጤማ ስለሚያድሉ ዕለቲቱ በዚህ ስያሜ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡
በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለ ዓዋዲ/ እየመቱ “ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ” የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቄጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡
ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡

ቅዱስ ቅዳሜ

ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡

©Mk

10/04/2026

ስቅለት

10/04/2026

ጌታችን ሲሰቅልም የሚከተሉት ሰባት ተአምራት ተፈጽመዋል

፩. ፀሐይ ጨለመ
፪. ጨረቃ ደም ኾነ
፫. ከዋክብት ረገፉ
፬. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ተቀደደ
፭. አለቶች ተፈረካከሱ
፮. መቃብራት ተከፈቱ
፯. ሙታን ተነሡ።

10/04/2026

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸው አምስቱ ቅንዋተ መስቀል

1. ሳዶር
2. አላዶር
3. ዳናት
4. አዴራ
5. ሮዳስ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተብርሃን ሰ/ት/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ፍኖተብርሃን ሰ/ት/ቤት:

Share