24/05/2026
ርእስ፣ መለኮታዊ አቅጣጫ (divine direction)
በዶክተር ዳዊት
ዘፍጥረት 21
14 አብርሃምም ማልዶ ተነሣ፥ እንጀራንም ወሰደ፥ የውኃ አቁማዳንም ለአጋር በትከሻዋ አሸከማት፥ ብላቴናውንም ሰጥቶ አስወጣት፤ እርስዋም ሄደች በቤርሳቤህም ምድረ በዳ ተቅበዘበዘች።
15 ውኃውም ከአቁማዳው አለቀ፤ ብላቴናውንም ከአንድ ቍጥቋጦ በታች ጣለችው፤
16 እርስዋም ሄደች፡— ብላቴናው ሲሞት አልየው ብላ ቀስት ተወርውሮ የሚደርስበትን ያህል ርቃ በአንጻሩ ተቀመጠች። ፊት ለፊትም ተቀመጠች፥ ቃልዋንም አሰምታ አለቀሰች።
17 እግዚአብሔርም የብላቴናውን ድምፅ ሰማ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ ከሰማይ አጋርን እንዲህ ሲል ጠራት፡— አጋር ሆይ፥ ምን ሆንሽ? እግዚአብሔር የብላቴናውን ድምፅ ባለበት ስፍራ ሰምቶአልና አትፍሪ።
18 ተነሺ፥ ብላቴናውንም አንሺ፥ እጅሽንም በእርሱ አጽኚው፤ ትልቅ ሕዝብ አደርገዋለሁና።
19 እግዚአብሔርም ዓይንዋን ከፈተላት፥ የውኃ ጕድጓድንም አየች፤ ሄዳም አቁማዳውን በውኃ ሞላች፥ ብላቴናውንም አጠጣች።
¶ እግዚአብሔር ራዕይን ከሰጠን የሚያስፈልገን ነገር አቅጣጫ መቀበል ነው።
¶ አቅጣጫ የሚፈልግ ሰው የመንፈስ ቅዱስ ጥገኛ ይሆናል።ሁሌም ድምጹን ለመስማት ዝግጁም ይሆናል።
¶ አቅጣጫ ያልተቀበለ ሰው እጁ ላይ ያለውን ነገር ሊጥለው ይችላል።
¶ አቅጣጫ የሌለው ሰው ሃብት ያባክናል ፣ ራዕይውን ይጥላል ከዚያም እራሱን ወደ መጣል ይሄዳል።
¶ እግዚአብሔር ተጀምሮ የሚቋረጥ አቅጣጫ ስላልሰጠን አቅጣጫ ጠይቀን መውጣት አለብን።
¶ እግዚአብሔር በእኛ ህይወት ውስጥ ትልቅ አላማ አለው።እግዚአብሔር አቃታጫ ይሰጠናል።
¶ አቅጣጫ የህይወት ዘመን ጥያቄ ነው እግዚአብሔር አቅጣጫ ሲሰጠን ግን ማረፍ ይሆንልናል።
መለኮታዊ አቅጣጫ ለምን ያስፈልገናል?
1 ባለራዕይ እንዲጀምር
2 የጀመረ እንዲቀጥል
¶ መለኮታዊ አቅጣጫ የሌለው ሰው መድረሻውን ማረጋገጥ አይችልም።ሁሌም እየተገዛን ልንቀበለው የሚገባን ጉዳይ መለኮታዊ አቅጣጫ ነው።
አቅጣጫ የሌለው ሰው ምን ይሆናል?
1 ባለበት ይቆማል
2 ይቅበዘበዛል
¶ እግዚአብሔር አቅጣጫ ሲሰጥ ግን ማረፍ ይሆናል።
አቅጣጫ ሲኖር ደግሞ.....
1 ራዕይ ይቀጥላል
2 መንገድ ላይ መቅረት አይሆንም
3 ከቀስት ማምለጥ ይሆናል
4 በሌሎች ህይወት ተጽዕኖ ማድረግ ይችላል
5 ምርኮን ያስመልሳል
ዘጸአት 13
21 በቀንና በሌሊትም ይሄዱ ዘንድ፥ መንገድ ሊያሳያቸው ቀን በደመና ዓምድ፥ ሊያበራላቸውም ሌሊት በእሳት ዓምድ እግዚአብሔር በፊታቸው ሄደ።
22 የደመና ዓምድ በቀን፥ የእሳት ዓምድ በሌሊት ከሕዝቡ ፊት ከቶ ፈቀቅ አላለም።
¶ አቅጣጫን ከእግዚአብሔር የተቀበለ ሰው መንገድ ላይ አይቀርም።ምክንያቱም እግዚአብሔር በፊቱ ይሄድለታል።
መዝሙር 60
4 ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው።
1ኛ ነገስት 19
13 ኤልያስም ያን በሰማ ጊዜ ፊቱን በመጐናጸፊያው ሸፈነ፥ ወጥቶም በዋሻው ደጃፍ ቆመ። እነሆ፡— ኤልያስ ሆይ፥ በዚህ ምን ታደርጋለህ? የሚል ድምፅ ወደ እርሱ መጣ።
14 እርሱም፡— ለሠራዊት አምላክ ለእግዚአብሔር እጅግ ቀንቻለሁ፤ የእስራኤል ልጆች ቃል ኪዳንህን ትተዋልና፥ መሠዊያዎችህንም አፍርሰዋልና፥ ነቢያትህንም በሰይፍ ገድለዋልና፤ እኔም ብቻዬን ቀርቻለሁ፤ ነፍሴንም ሊወስዱአት ይሻሉ፡ አለ።
15 እግዚአብሔርም አለው፡— ሂድ፥ በመጣህበትም መንገድ በምድረ በዳ ወደ ደማስቆ ተመለስ፤ ከዚያም በደረስህ ጊዜ በሶርያ ላይ ንጉሥ ይሆን ዘንድ አዛሄልን ቅባው፤
16 በእስራኤልም ላይ ንጉሥ ይሆን ዘንድ የናሜሲን ልጅ ኢዩን ቅባው፤ በፋንታህም ነቢይ ይሆን ዘንድ የአቤልምሖላን ሰው የሣፋጥን ልጅ ኤልሳዕን ቅባው ከአዛሄልም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ።
17 ኢዩ ይገድለዋል፤ ከኢዩም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ ኤልሳዕ ይገድለዋል።
18 እኔም ከእስራኤል ጕልበታቸውን ለበኣል ያላንበረከኩትን ሁሉ፥ በአፋቸውም ያልሳሙትን ሁሉ፥ ሰባት ሺህ ሰዎች ለእኔ አስቀራለሁ።
¶ አቅጣጫ ከሰጠን ከእግዚአብሔር ጋር ስንሆን ፣አንያዝም ክፉዎች አይጠጉንም በሁሉ ነገር ማምለጥ ይሆንልናል።
1ኛ ሳሙኤል 30
5 የዳዊትም ሁለቱ ሚስቶቹ ኢይዝራኤላዊቱ አኪናሆምና የቀርሜሎሳዊው የናባል ሚስት የነበረችው አቢግያ ተማርከው ነበር።
6 ስለ ወንዶችና ስለ ሴቶች ልጆቻቸው የሕዝቡ ሁሉ ልብ ተቈጥቶ ነበርና ሕዝቡ ሊወግሩት ስለ ተናገሩ ዳዊት እጅግ ተጨነቀ፤ ዳዊት ግን በአምላኩ በእግዚአብሔር ልቡን አበረታ።
7 ዳዊትም የአቢሜሌክን ልጅ ካህኑን አብያታርን፡— ኤፉዱን አቅርብልኝ አለው፤ አብያታርም ኤፉዱን ለዳዊት አቀረበለት።
8 ዳዊትም፡— የእነዚህን ሠራዊት ፍለጋ ልከተልን? አገኛቸዋለሁን? ብሎ እግዚአብሔርን ጠየቀ፤ እርሱም፡— ታገኛቸዋለህና፥ ፈጽመህም ምርኮውን ትመልሳለህና ፍለጋቸውን ተከተል ብሎ መለሰለት።
18 ዳዊትም አማሌቃውያን የወሰዱትን ሁሉ አስጣላቸው፥ ሁለቱንም ሚስቶቹን አዳነ።
19 ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች፥ ከወሰዱትም ምርኮ ሁሉ፥ ታላቅም ሆነ ታናሽም ሆነ፥ ምንም የጐደለባቸው የለም፤ ዳዊትም ሁሉን አስጣለ።
20 ዳዊትም የበጉንና የላሙን መንጋ ሁሉ ወሰደ፥ ከራሱም ከብት ፊት እየነዳ፡— ይህ የዳዊት ምርኮ ነው፡ አለ።
አቅጣጫ ለምን ከባድ ሆነ?
1 ራዕይ ካለ ሁሉ አለ የሚል አስተሳሰብ ስላለ
ዘፍጥረት 12÷1
2 እግዚአብሔር አስጀምሮኛል ከዚህ ቡሃላ ምንም አይሆንም
3 በስራረ ተይዘን የአቅጣጫ ጉዳይ ቅድሚያ ስለማንሰጠው
ዘሑልቅ 20÷8 ፣11፣12
4 ፍርሃት
5 በክፉ ሰዎች ምክንያት
1ኛ ነገስት 13÷1 18 ፣21፣ 22
¶ በአላማ ይጠናል፣አቅጣጫ ይቀየራል።
አቅጣጫን ለመከተል
1 አይን መክፈት
ዘፍጥረት 21
2 መለኮታዊ ጥበብ
መክብብ 10÷10
3 የእግዚአብሔርን ድምጽ በልዩነት መስማት
ኢሳያስ 30÷21
ሉቃስ 8÷18
4 እግዚአብሔርን መጠየቅ
2ኛ ሳሙኤል 2÷1
¶ ህብረት መለኮታዊ አቅጣጫ ለመቀበል ወሳኝ ነው።
ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው