New Creation International Church

New Creation International Church This Page is official page for NEW CREATION INTERNATIONAL CHURCH ETH.
(244)

ርእስ፣ መለኮታዊ አቅጣጫ (divine direction)‎‎      በዶክተር ዳዊት‎‎       ዘፍጥረት 21‎‎14 አብርሃምም ማልዶ ተነሣ፥ እንጀራንም ወሰደ፥ የውኃ አቁማዳንም ለአጋር በትከ...
24/05/2026

ርእስ፣ መለኮታዊ አቅጣጫ (divine direction)

‎ በዶክተር ዳዊት

‎ ዘፍጥረት 21

‎14 አብርሃምም ማልዶ ተነሣ፥ እንጀራንም ወሰደ፥ የውኃ አቁማዳንም ለአጋር በትከሻዋ አሸከማት፥ ብላቴናውንም ሰጥቶ አስወጣት፤ እርስዋም ሄደች በቤርሳቤህም ምድረ በዳ ተቅበዘበዘች።

‎15 ውኃውም ከአቁማዳው አለቀ፤ ብላቴናውንም ከአንድ ቍጥቋጦ በታች ጣለችው፤
‎16 እርስዋም ሄደች፡— ብላቴናው ሲሞት አልየው ብላ ቀስት ተወርውሮ የሚደርስበትን ያህል ርቃ በአንጻሩ ተቀመጠች። ፊት ለፊትም ተቀመጠች፥ ቃልዋንም አሰምታ አለቀሰች።

‎17 እግዚአብሔርም የብላቴናውን ድምፅ ሰማ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ ከሰማይ አጋርን እንዲህ ሲል ጠራት፡— አጋር ሆይ፥ ምን ሆንሽ? እግዚአብሔር የብላቴናውን ድምፅ ባለበት ስፍራ ሰምቶአልና አትፍሪ።

‎18 ተነሺ፥ ብላቴናውንም አንሺ፥ እጅሽንም በእርሱ አጽኚው፤ ትልቅ ሕዝብ አደርገዋለሁና።

‎19 እግዚአብሔርም ዓይንዋን ከፈተላት፥ የውኃ ጕድጓድንም አየች፤ ሄዳም አቁማዳውን በውኃ ሞላች፥ ብላቴናውንም አጠጣች።

‎¶ እግዚአብሔር ራዕይን ከሰጠን የሚያስፈልገን ነገር አቅጣጫ መቀበል ነው።

‎¶ አቅጣጫ የሚፈልግ ሰው የመንፈስ ቅዱስ ጥገኛ ይሆናል።ሁሌም ድምጹን ለመስማት ዝግጁም ይሆናል።

‎¶ አቅጣጫ ያልተቀበለ ሰው እጁ ላይ ያለውን ነገር ሊጥለው ይችላል።

‎¶ አቅጣጫ የሌለው ሰው ሃብት ያባክናል ፣ ራዕይውን ይጥላል ከዚያም እራሱን ወደ መጣል ይሄዳል።

‎¶ እግዚአብሔር ተጀምሮ የሚቋረጥ አቅጣጫ ስላልሰጠን አቅጣጫ ጠይቀን መውጣት አለብን።

‎¶ እግዚአብሔር በእኛ ህይወት ውስጥ ትልቅ አላማ አለው።እግዚአብሔር አቃታጫ ይሰጠናል።

‎¶ አቅጣጫ የህይወት ዘመን ጥያቄ ነው እግዚአብሔር አቅጣጫ ሲሰጠን ግን ማረፍ ይሆንልናል።

‎ መለኮታዊ አቅጣጫ ለምን ያስፈልገናል?

‎1 ባለራዕይ እንዲጀምር

‎2 የጀመረ እንዲቀጥል

‎¶ መለኮታዊ አቅጣጫ የሌለው ሰው መድረሻውን ማረጋገጥ አይችልም።ሁሌም እየተገዛን ልንቀበለው የሚገባን ጉዳይ መለኮታዊ አቅጣጫ ነው።

‎ አቅጣጫ የሌለው ሰው ምን ይሆናል?

‎1 ባለበት ይቆማል

‎2 ይቅበዘበዛል

‎¶ እግዚአብሔር አቅጣጫ ሲሰጥ ግን ማረፍ ይሆናል።

‎ አቅጣጫ ሲኖር ደግሞ.....

‎1 ራዕይ ይቀጥላል

‎2 መንገድ ላይ መቅረት አይሆንም

‎3 ከቀስት ማምለጥ ይሆናል

‎4 በሌሎች ህይወት ተጽዕኖ ማድረግ ይችላል

‎5 ምርኮን ያስመልሳል

‎ ዘጸአት 13

‎21 በቀንና በሌሊትም ይሄዱ ዘንድ፥ መንገድ ሊያሳያቸው ቀን በደመና ዓምድ፥ ሊያበራላቸውም ሌሊት በእሳት ዓምድ እግዚአብሔር በፊታቸው ሄደ።
‎22 የደመና ዓምድ በቀን፥ የእሳት ዓምድ በሌሊት ከሕዝቡ ፊት ከቶ ፈቀቅ አላለም።

‎¶ አቅጣጫን ከእግዚአብሔር የተቀበለ ሰው መንገድ ላይ አይቀርም።ምክንያቱም እግዚአብሔር በፊቱ ይሄድለታል።

‎ መዝሙር 60

‎4 ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው።

‎ 1ኛ ነገስት 19

‎13 ኤልያስም ያን በሰማ ጊዜ ፊቱን በመጐናጸፊያው ሸፈነ፥ ወጥቶም በዋሻው ደጃፍ ቆመ። እነሆ፡— ኤልያስ ሆይ፥ በዚህ ምን ታደርጋለህ? የሚል ድምፅ ወደ እርሱ መጣ።
‎14 እርሱም፡— ለሠራዊት አምላክ ለእግዚአብሔር እጅግ ቀንቻለሁ፤ የእስራኤል ልጆች ቃል ኪዳንህን ትተዋልና፥ መሠዊያዎችህንም አፍርሰዋልና፥ ነቢያትህንም በሰይፍ ገድለዋልና፤ እኔም ብቻዬን ቀርቻለሁ፤ ነፍሴንም ሊወስዱአት ይሻሉ፡ አለ።

‎15 እግዚአብሔርም አለው፡— ሂድ፥ በመጣህበትም መንገድ በምድረ በዳ ወደ ደማስቆ ተመለስ፤ ከዚያም በደረስህ ጊዜ በሶርያ ላይ ንጉሥ ይሆን ዘንድ አዛሄልን ቅባው፤
‎16 በእስራኤልም ላይ ንጉሥ ይሆን ዘንድ የናሜሲን ልጅ ኢዩን ቅባው፤ በፋንታህም ነቢይ ይሆን ዘንድ የአቤልምሖላን ሰው የሣፋጥን ልጅ ኤልሳዕን ቅባው ከአዛሄልም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ።
‎17 ኢዩ ይገድለዋል፤ ከኢዩም ሰይፍ ያመለጠውን ሁሉ ኤልሳዕ ይገድለዋል።

‎18 እኔም ከእስራኤል ጕልበታቸውን ለበኣል ያላንበረከኩትን ሁሉ፥ በአፋቸውም ያልሳሙትን ሁሉ፥ ሰባት ሺህ ሰዎች ለእኔ አስቀራለሁ።

‎¶ አቅጣጫ ከሰጠን ከእግዚአብሔር ጋር ስንሆን ፣አንያዝም ክፉዎች አይጠጉንም በሁሉ ነገር ማምለጥ ይሆንልናል።

‎ 1ኛ ሳሙኤል 30

‎5 የዳዊትም ሁለቱ ሚስቶቹ ኢይዝራኤላዊቱ አኪናሆምና የቀርሜሎሳዊው የናባል ሚስት የነበረችው አቢግያ ተማርከው ነበር።
‎6 ስለ ወንዶችና ስለ ሴቶች ልጆቻቸው የሕዝቡ ሁሉ ልብ ተቈጥቶ ነበርና ሕዝቡ ሊወግሩት ስለ ተናገሩ ዳዊት እጅግ ተጨነቀ፤ ዳዊት ግን በአምላኩ በእግዚአብሔር ልቡን አበረታ።

‎7 ዳዊትም የአቢሜሌክን ልጅ ካህኑን አብያታርን፡— ኤፉዱን አቅርብልኝ አለው፤ አብያታርም ኤፉዱን ለዳዊት አቀረበለት።
‎8 ዳዊትም፡— የእነዚህን ሠራዊት ፍለጋ ልከተልን? አገኛቸዋለሁን? ብሎ እግዚአብሔርን ጠየቀ፤ እርሱም፡— ታገኛቸዋለህና፥ ፈጽመህም ምርኮውን ትመልሳለህና ፍለጋቸውን ተከተል ብሎ መለሰለት።

‎18 ዳዊትም አማሌቃውያን የወሰዱትን ሁሉ አስጣላቸው፥ ሁለቱንም ሚስቶቹን አዳነ።
‎19 ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች፥ ከወሰዱትም ምርኮ ሁሉ፥ ታላቅም ሆነ ታናሽም ሆነ፥ ምንም የጐደለባቸው የለም፤ ዳዊትም ሁሉን አስጣለ።
‎20 ዳዊትም የበጉንና የላሙን መንጋ ሁሉ ወሰደ፥ ከራሱም ከብት ፊት እየነዳ፡— ይህ የዳዊት ምርኮ ነው፡ አለ።

‎ አቅጣጫ ለምን ከባድ ሆነ?

‎1 ራዕይ ካለ ሁሉ አለ የሚል አስተሳሰብ ስላለ

‎ዘፍጥረት 12÷1

‎2 እግዚአብሔር አስጀምሮኛል ከዚህ ቡሃላ ምንም አይሆንም

‎3 በስራረ ተይዘን የአቅጣጫ ጉዳይ ቅድሚያ ስለማንሰጠው

‎ዘሑልቅ 20÷8 ፣11፣12

‎4 ፍርሃት

‎5 በክፉ ሰዎች ምክንያት

‎1ኛ ነገስት 13÷1 18 ፣21፣ 22

‎¶ በአላማ ይጠናል፣አቅጣጫ ይቀየራል።

‎ አቅጣጫን ለመከተል

‎1 አይን መክፈት

‎ዘፍጥረት 21

‎2 መለኮታዊ ጥበብ

‎መክብብ 10÷10

‎3 የእግዚአብሔርን ድምጽ በልዩነት መስማት

‎ ኢሳያስ 30÷21
‎ ሉቃስ 8÷18

‎4 እግዚአብሔርን መጠየቅ

‎2ኛ ሳሙኤል 2÷1

‎¶ ህብረት መለኮታዊ አቅጣጫ ለመቀበል ወሳኝ ነው።

‎ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው

23/05/2026
https://www.youtube.com/watch?v=NC2Y5u0c5z8&t=35s
20/05/2026

https://www.youtube.com/watch?v=NC2Y5u0c5z8&t=35s

- Apostle Bisrat Bezuayene - Japi - ሐዋርያው ብስራት ብዙአየን ጃፒThis Video Clip is Dedicated Only to New Creation Church Ethiopia Channel /Bisrat Bezuayene/! Subscrib...

ርዕስ፣በመንፈስ መመራት‎‎        በእህት መታሰቢያ ተስፋዬ‎‎¶  መንፈስ ቅዱስ አምላክ ነው ፣እግዚአብሔር ነው ህይወት ነው።‎‎¶  መንፈስ ቅዱስ ወደ እውነት ሁሉ የሚመራን የሚያበረታን ...
20/05/2026

ርዕስ፣በመንፈስ መመራት

‎ በእህት መታሰቢያ ተስፋዬ

‎¶ መንፈስ ቅዱስ አምላክ ነው ፣እግዚአብሔር ነው ህይወት ነው።

‎¶ መንፈስ ቅዱስ ወደ እውነት ሁሉ የሚመራን የሚያበረታን ነው፣የቅርብ ወዳጃችን ነው።በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ትቶን የማይሄድ ችላ የማይለን ነው።

‎ ማቴዎስ 16

‎13 ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡— ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ።

‎14 እነርሱም፡— አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው፥ ይላሉ፡ አሉት።

‎15 እርሱም፡— እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።
‎16 ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ፡— አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ፡ አለ።

‎17 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፡— የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ።

‎¶ ደቀ መዛሙርቱ አብረውት የነበሩ ሁሉንም ትተው የተከተሉት ናቸው፣ከእርሱ ጋር ውለው አድረዋል የጠየቃቸው ጥያቄ ግን ሁሉ እርሱን ማን እንደሚሉት ሳይሆን እነሱ እርሱን ማን እንደሚሉት ነበር

‎ ማቴዎስ 19

‎27 በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ፡— እነሆ፥ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ፤ እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን? አለው።

‎¶ መንፈስ ቅዱስ በእኛ ቤት ውስጥ ማነው የሚለውን ጥይቄ መመለስ አለብን።

‎¶ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለን ህብረት የምንሰጠውን ጊዜ ለመወሰን ያግዘናል።

‎ ...የእይታ መፈተሽ

‎¶ ኢየሱስ መጀመሪያ ሲጠይቃቸው ሰዎች የሰው ልጅን ማን ይሉታል?ብሎ ነው።ይህ ደግሞ ጥቅል ጥያቄ ነው።

‎¶ ቀጥሎ የጠየቃቸው ደግሞ በግል ነው፣እናንተስ?ብሎ

‎¶ አደባባይ ምንም ነገር ቢል እንኳ እይታ ግን የግል ነው።

‎ መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ማነው?

‎¶ መኖሪያችን ፣መገኛ ምንጫችን ፣ሁሉን የሚያውቅ ደግሞም ሁሉን የሚችል አምላክ ነው።

‎¶ እይታ እግዚአብሔር ላስቀመጠልን ነገር ዋጋ የሚሰጥ ነው።

‎ 2ኛ ነገስት 1÷4

‎¶ ኢየሱስ እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ ብሎ ሲጠይቃቸው ቀጣዩን ጊዜ የሚሻገሩት ማንነቱን ከማወቅ ሲጀምሩ ብቻ እንደሆነ ያመላክት ነበር።

‎¶ እኛም ለዚህ መዘጋጀት ዘመኑን መዋጀት አለብን መንፈስ ቅዱስ በሃይል እየሰራበት ያለበት ጊዜ እንደመሆኑ በብርቱ መዘጋጀት አለብን።

‎¶ መንፈስ ቅዱስ አልፎ እንዲሰራ የገደብነውን ማንሳት አለብን፣በምንም ነገር ልንወስነው አይገባም፣መሪያችንን ስንሰጠው መንፈስ ቅዱስ አደራረጉ ይለያል፣እርሱ እንደወደደ መንቀሳቀስ ይሆንልናል፣ለዚህ ደግሞ ልባችንን መስጠትና መፍቀድ አለብን።

‎ ዮሃንስ 16

‎12 የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም።

‎13 ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል።

‎14 እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና።

‎¶ የእግዚአብሔርን መንፈስ ማመንና መንገዳችንን ለእርሱ መስጠት አለብን።

‎¶ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ህብረት ስናደርግ ድምጹንም ከሰማን ምንም አይነት ሌላ ድምጽ አይረብሸንም ፣እርግጠኛ እንሆናለን።

‎¶ መንፈስ ቅዱስ የጓዳችን ከሆነ አደባባይ ላይ እርግጠኛ ሆነን፣ብሎናል ብለን እንናገርለታለን።

‎¶ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መትመም እንዲሆንልን ቃሉ ውስጥ፣ ህልውናው ውስጥ መቆየት አለብን።

‎¶ በሁሉም ነገር ለመንፈስ ቅዱስ አብሮነት እውቅና መስጠት አለብን።

‎ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው።

Address

New Creation Church
Addis Ababa

Opening Hours

Tuesday 17:30 - 20:30
Friday 17:30 - 20:30
Sunday 10:00 - 12:30

Telephone

+251940400000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New Creation International Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to New Creation International Church:

Share