19/03/2026
የ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ከነገ በስቲያ ጁምዓ እንደሚውል ተገለጸ!
- ሀሩን ሚዲያ | መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ል
የሳዑዲ አረቢያ የጨረቃ ክትትል ዓቢይ ኮሚቴ የሸዋል ወር አዲስ ጨረቃን ማየት ባለመቻሉ፣ ነገ ሐሙስ መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ.ል የረመዳን 30ኛ ቀን ሆኖ እንዲውል ተወስኗል።
በዚህም መሠረት የዘንድሮው የረመዳን ወር 30 ቀናትን አሟልቶ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የ1447ኛው ዓ.ሂ የኢድ አልፈጥር በዓል የፊታችን ጁምዓ መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ.ል በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ይውላል።
ሀሩን ሚዲያ ለመላው ሙስሊም ማኅበረሰብ እንኳን ለ1447ኛው ዓ.ሂ የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።
📅 ረመዳን 29 ቀን 1447 ዓ.ሂ
© ሀሩን ሚዲያ