Qera Selam Mesjid ቄራ ሰላም መስጂድ

Qera Selam Mesjid ቄራ ሰላም መስጂድ ��� بسم الله الرحمن الرحيم ���
በሸህ ዘይድ አልነህያ በጎ አድራጎት ድርጅት የተሰራ ሲሆን አሁን ባለው መልኩ ታድሶ የተመረቀው በ1996 አ,ል ነው ።

♥♥♥ بسم الله الرحمن الرحيم ♥♥♥
ኢስላም የሚለው ስያሜ አመጣጡ ሰላም ከሚለው ቃል ነው ፡፡ በሌላ ትርጉሙ ደግሞ ፈቃድን ለፈጣሪ ማስገዛት ማለትም ይሆናል እሰልምና ማለት ጥቅል በሆነ አገላለፅ ደግሞ ፍቃድን ለፈጣሪ በማስገዛት የሚገኝ ሰላም ማለት ነው፡፡
ኢስላም ሰላም
መስጅዳችንም ሰላም

ለ180 የቲሞችና አረጋውያን ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ተደረገ! • ​ሀሩን ሚዲያ | ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ል​በቄራ ሰላም መስጂድ የሚገኘው 'ሰላም የየቲም ህጻናትና አረ...
04/08/2026

ለ180 የቲሞችና አረጋውያን ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ተደረገ!

• ​ሀሩን ሚዲያ | ሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ል

​በቄራ ሰላም መስጂድ የሚገኘው 'ሰላም የየቲም ህጻናትና አረጋውያን የልማትና መረዳጃ ተቋም' ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለ180 የቲሞች፣ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ድጋፍ አድርጓል።

​የተቋሙ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳዳም ሀሰን እንደገለጹት፤ በዕለቱ ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የዱቄት፣ የዘይትና የሳሙና ድጋፍ ለ180 የቲሞች፣ አረጋውያንና አካል ጉዳተኛ ግለሰቦች ተሰጥቷል። ይህ ድጋፍም በየሁለት ወሩ በቋሚነት እየተካሄደ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ተቋሙ ከምግብና ከመሠረታዊ ቁሳቁስ ድጋፍ በተጨማሪ፣ በትምህርት፣ በህክምና፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና በአስቤዛ ድጋፍ ከ20 ዓመታት በላይ ለየቲሞችና ለአረጋውያን ዘርፈ ብዙ ማህበራዊ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱንም አቶ ሳዳም ገልጸዋል።

​የቄራ ሰላም መስጂድ ኢማምና የቂርቆስ ክፍለ ከተማ መጅሊስ የሥራ አስፈጻሚ አባል ኡስታዝ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው፤ መስጂዶች ከመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ባሻገር የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳትና በማስተባበር ሁለንተናዊ አገልግሎት ሊሰጡ እንደሚገባ ገልጸው፣ በመስጂዱ ቅጥር ግቢ ውስጥ በቋሚነት እየተካሄደ ላለው የድጋፍ ሥራ የተቋሙን ድጋፍ ሰጪ አባላት አመስግነዋል።

​የቄራ ሰላም መስጂድ የሥራ አስፈጻሚ አባል ቶፊቅ ዳሪ በበኩላቸው፣ ለረጅም ዓመታት እየተደረገ ያለው ድጋፍ የቲሞች የብቸኝነት ስሜት እንዳይበረታባቸውና አረጋውያንም በችግር እንዳይወድቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል።

"የቲምነት ስሜቱ ከባድ ነው" ያሉት ቶፊቅ ዳሪ፤ ወላጅ የሌላቸው ህጻናትን መደገፍ የአካላዊ ፍላጎታቸውን ከማሟላት ባለፈ የስሜት ቁስላቸውን ለማቃለል እንደሚረዳ ጠቅሰው፣ መሰል ተቋማትን ማጠናከር እንደሚገባ ተናግረዋል። በመሆኑም መላው ማህበረሰብ ከተቋሙ ጎን በመቆም ለየቲም ህጻናትና አረጋውያን የሚደረገውን ድጋፍ እንዲያጠናክር ጥሪ አቅርበዋል።

​በ1994 ዓ.ል በበጎ ፈቃደኞች የተመሠረተው 'ሰላም የየቲም ህጻናትና አረጋውያን መርጃ ድርጅት'፣ በአሁኑ ወቅት 500 የየቲም ቤተሰቦችን በቋሚነት ከመደገፉ በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ ማህበራዊና ዲናዊ ሀላፊነቶችን እየተወጣ መሆኑ በድጋፍ መርሃ ግብሩ ላይ ተገልጿል።

​📅 ሰፈር 21 ቀን 1448 ዓ.ሂ

​© ሀሩን ሚዲያ

28/07/2026

ልጆችን ከዚህች ዓለም ፈተናዎች መጠበቅና ለእነሱ መፍራት፤ በመጀመሪያ ደረጃ እራስህን እንድታስተካክል ሊያነሳሳህ ይገባል። ምክንያቱም የራስህ መልካም መሆን (ሳሊህ መሆን) የልጆችህ መልካም አስተዳደግ መሰረት ነውና።

ታላቁ ታቢዒይ ሰዒድ ቢን አል-ሙሰይብ በአንድ ወቅት ለልጃቸው እንዲህ አሉት፦ «ልጄ ሆይ! በአንተ ምክንያት (አላህ አንተን እንዲጠብቅልኝ) ብዬ ሰላቴን (ትጋቴን) እጨምራለሁ…»

በመቀጠልም ይህንን የአላህን ቃል አነበቡ፦ «አባታቸውም ደግ (ሳሊህ) ሰው ነበር።» (ሱረቱ አል-ካህፍ፡ 82)"

19/03/2026

የ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ከነገ በስቲያ ጁምዓ እንደሚውል ተገለጸ!

- ሀሩን ሚዲያ | መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ል

የሳዑዲ አረቢያ የጨረቃ ክትትል ዓቢይ ኮሚቴ የሸዋል ወር አዲስ ጨረቃን ማየት ባለመቻሉ፣ ነገ ሐሙስ መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ.ል የረመዳን 30ኛ ቀን ሆኖ እንዲውል ተወስኗል።

በዚህም መሠረት የዘንድሮው የረመዳን ወር 30 ቀናትን አሟልቶ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የ1447ኛው ዓ.ሂ የኢድ አልፈጥር በዓል የፊታችን ጁምዓ መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ.ል በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ይውላል።

ሀሩን ሚዲያ ለመላው ሙስሊም ማኅበረሰብ እንኳን ለ1447ኛው ዓ.ሂ የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

📅 ረመዳን 29 ቀን 1447 ዓ.ሂ

© ሀሩን ሚዲያ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Qera Selam Mesjid ቄራ ሰላም መስጂድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Qera Selam Mesjid ቄራ ሰላም መስጂድ:

Shortcuts

Share