አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ አቤኔዘር እባላለሁ፥ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና እምነት ተከታይ ነኝ። በዚህ ገፅ የቤተክርስቲያንን ዶግማ ቀኖና እና ትውፊት የጠበቁ መንፈሳዊ መርሐግብሮች ይቀርባሉ።
(295)

በቅዱስ ሚካኤል ስም። እንኳን ወደ አቤኔዘር ዘተዋሕዶ የፌስቡክ ገፅ በደህና መጡ።
9ኛ ዓመት የምስረታ በዓል! 🎊
​ከሚያዝያ 9/2009 እስከ ሚያዝያ 9/2018 ዓ.ም.
​ባለፉት 9 ዓመታት የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነታችንን እሴቶች ለማካፈል ስናደርግ የነበረው ጉዞ በስኬት ቀጥሏል።
"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው።" ማቴ.17:4
ወትቀውም ንግስት በየማንከ በአልባሰ ወርቅ

🔔 የአቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ቤተሰቦች በሙሉ የተላለፈ ታላቅ የጥሪ ማስታወቂያ! 🔔የ ሰኔ ሚካኤል ደረሰልን 💣💥"የሰጠ ምስጉን ነው፤ ከተቀባይም ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" (የሐዋ. ሥራ 20፥3...
27/05/2026

🔔 የአቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ቤተሰቦች በሙሉ የተላለፈ ታላቅ የጥሪ ማስታወቂያ! 🔔

የ ሰኔ ሚካኤል ደረሰልን 💣💥

"የሰጠ ምስጉን ነው፤ ከተቀባይም ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" (የሐዋ. ሥራ 20፥35)
ውድና የተከበራችሁ የአቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ቤተሰቦች፤
በእግዚአብሔር ፈቃድና በቅዱሳኑ ጥበቃ በዓመት ሁለት ጊዜ የምናደርገው የጥቅምት መድኃኔዓለም እና የሰኔ ቅዱስ ሚካኤል የጋራ የዝክር መርሐግብራችን ዘንድሮ ለ3ኛ ተከታታይ ዓመት በታላቅ በረከት ሊካሄድ ዝግጅቱን ጀምሯል።

ይህ በጋራ የምንሰበስበውና ለነዳያን የምናደርሰው የፍቅር ስጦታ፣ በገጻችን ስም የምናበረክተው ትልቅ መንፈሳዊ ፍሬያችን ነው።

🍲 የዘንድሮው የሰኔ 12 መርሐግብር
እንደሚታወቀው መርሐግብሩ የሚውለው በሰኔ ጾም (በሐዋርያት ጾም) ወቅት በመሆኑ፣ እንደተለመደው የጾም ምግብ አዘጋጅተን ወገኖቻችንን የምንዘክርበት ይሆናል።

በዚህም መሠረት ለምግብ ማዘጋጃ የሚሆኑ የቁሳቁስ ድጋፎችን መሰብሰብ መጀመራችንን እናበስራለን፦
* 🛢️ ዘይት
* 🌶️ በርበሬ
* 🧆 ምስር እና የመሳሰሉትን የጥራጥሬ አይነቶች

🤝 እንዴት መሳተፍ ይችላሉ?
የዚህ የበረከት ድርሻ ተሳታፊ በመሆን በጸሎት፣ በሃሳብ፣ ቁሳቁስ በማበርከት እንዲሁም ይህንን መልእክት ለሌሎች Share በማድረግ አብረውን እንዲቆሙ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

> "ምጽዋት ከሞት ታድናለች፥ ከኃጢአትም ሁሉ ታነጻለች።" (መጽሐፈ ጦቢት 4፥10) >

📍 ማሳሰቢያ፦ የእርዳታ ማስተባበሪያ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ አካውንት
ንግድ ባንክ 1000145090176
አቢሲኒያ 47056497
ቴሌብር 0933143133

ለበለጠ መረጃና በዋትሳፕ ለማውራት +251933143133 ይደውሉ ይጻፉ

የቅዱሳን አማላጅነትና ጸሎት አይለየን!

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

አሁን የብስራታዊው መልአክ የቅዱስ ገብርኤልን መልክ እናደርሳለን። ከፊታችሁ አንድ ብርጭቆ ውኃ አስቀምጣችሁ ጸልዩበትና ስትጨርሱ ሰውነታችሁን ተቀባቡት ጠጡት ።😍🙏መልክአ፡ ገብርኤል።፩.  ሰላ...
27/05/2026

አሁን የብስራታዊው መልአክ የቅዱስ ገብርኤልን መልክ እናደርሳለን።

ከፊታችሁ አንድ ብርጭቆ ውኃ አስቀምጣችሁ ጸልዩበትና ስትጨርሱ ሰውነታችሁን ተቀባቡት ጠጡት ።😍🙏

መልክአ፡ ገብርኤል።

፩. ሰላመ ፡ ገብርኤል ፡ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ ስለ ፡ ማርያም ፡ ክብር ፡ የቀረበውን ፡ የገብርኤልን ፡ ሰላምታ ፡ አምልቼ ፡ አጉልቼ ፡ ያይደለ ፡ በችሎታዬ ፡ መጠን ፡ እናገር ፡ ዘንድ ፡ የማስተዋል ፡ መጽሐፍ ፡ ልቡና ፡ ስጠኝ። ፈጣሪዬ ፡ ሆይ ፡ አንደበቴ ፡ ሙሴ ፡ መናገር ፡ የማይችል ፡ ኮልታፋ ፡ እንኳ ፡ ቢሆን ፡ ጥበብን ፡ የሚገልጽ ፡ ምሥጢርን ፡ የሚያስተረጉም ፡ ጰራቅሊጦስ ፡ አሮን ፡አንአንደበት ፡ ይሁነኝ።

፪. ለተፈጥሮትከ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ የስሙ ፡ ትርጓሜ ፡ የማይመረመር፡ ካለመኖር ፡ ማለት ፡ ከኢምንት ፡ ግብር ፡ በቀዳማይ ፡ የእሑድ ፡ ሰዓተ ፡ ሌሊት ፡ ለተከናወነ ፡ ሥነ ፡ ተፈጥሮህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ማሕተሙ ፡ የአይሁድ ፡ ንጉሥ ፡ ይህ ፡ ነው ፡ የሚል ፡ የሕፃኑ ፡ ኢየሱስና ፡ የእናቱ ፡ የማርያም ፡ መልክአ ፡ ሥዕል ፡ የተሣለብህ ፡ የበለዓም ፡ የራእዩ ፡ ኮከብ ፡ የልደት ፡ ሐዋርያ ፡ አንተ ፡ ነህና።

፫. ለዝክረ ፡ ስምከ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ተመራምሮ ፡ ለማይደረስበት ፡ ስም ፡ አጠራርህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ ፡ ነገር ፡ ግን ፡ አምላክ ፡ ሰው ፡ ሆነ ፡ ሰው ፡ አምላክ ፡ ሆነ ፡ ማለት ፡ ይመስላል።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ የአንበሳ ፡ የገጸ ፡ ላህምና ፡ የንስር ፡ ሥነ ፡ ገጽ ፡ ካላቸው ፡ ኪሩቤል ፡ ጋር ፡ የእግዚአብሔር ፡ ዙፋን ፡ ተሸክመህ ፡ በከበረ ፡ የሰው ፡ ሥነ ፡ አምሳል ፡ ሕዝቅኤል ፡ ያየህ ፡ ከኪሩቤል ፡ አንዱ ፡ አንተ ፡ ነህ።

፬. ለስእርተ ፡ ርእስከ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ እግዚአብሔር ፡ ልዩ ፡ የሆነ ፡ የምስጋና ፡ ዘውድ ፡ ላቀዳጀው ፡ ራስህና ፡ ስእርተ ፡ ርእስህ ፡ እጅ ፡ እየነሣሁ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ የቃልህ ፡ ብርሃን ፡ ከጽንፍ ፡ እስከ ፡ ጽንፍ ፡ የሚደርስ ፡ ሥነ ፡ ጸደሉም ፡ በዓረቱ ፡ ማዕዘነ ፡ ዓለም ፡ የመላ ፡ አንተ ፡ ከምሥራቅ ፡ የወጣህ ፡ ፀሐይ ፡ ነህ።

፭. ለገጽከ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ እጅግ ፡ የሚያስፈራ ፡ እሳት ፡ ነበልባል ፡ መካከል ፡ የነነዌ ፡ ንጉሥ ፡ ያየው ፡ ከመላእክት ፡ ገጽ ፡ የደስታ ፡ መልክ ፡ ላለው ፡ ገጽህ ፡ ሰላ ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡በንጽሕና ፡ ልብሰ ፡ ተክህኖ ፡ የተሰየምክ ፡ አንተ ፡ በፍርድ ፡ ያይደለ ፡ በክርስቶስ ፡ ቸርነት ፡ እድን ፡ ዘንድ ፡ የነግሁንና ፡ የሠርኩን ፡ መሥዋዕት ፡ በምታሣርግበት ፡ ጊዜ ፡ የኔን ፡ የኃጥኡን ፡ ኃጢአት ፡ አስተሥርይ።

፮. ለቀራንብቲከ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ዕንቅልፍ ፡ ለማይፈታተናቸው ፡ ለዓይኖችህ ፡ ቀራንብትና ፡ ዓለምን ፡ በብርሃናችው ፡ ለሚያገለግሉ ፡ ከዋክብት ፡ ዓይኖችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ አንተም ፡ እንጂ ፡ የሰላም ፡ ዕረፍ ፡ ትሰጠን ፡ ዘንድ ፡ ትጋ። ቅዱስ ፡ሚካኤል ፡ ለሙሴ ፡ ጠባቂ ፡ ሆኖ ፡ በተሸመ ፡ ጊዜ ፡ ታላቁን ፡ የኤርትራን ፡ ባሕር ፡ ከፍሎ ፡ አሻግሮታልና።

፯. ለአእዛኒከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ የአብ ፡ አካላዊ ፡ ቃል ፡ መሳክወ ፡ ብርሃን ፡ ለሚሆኑ ፡ ጆሮችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። የውበታቸው ፡ ጸዳል ፡ የበረኃ ፡ አበባ ፡ ለሚመስለውም ፡ ጉንጮችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ከጭንቅና ፡ ከመከራ ፡ ለማውጠት ፡ የተላክህ ፡ መልአክ ፡ ነህና። ሠለስቱ ፡ ደቂቅ ፡ በእሳት ፡ ጉድጓድ ፡ በተጣሉ ፡ ጊዜ ፡ ሁለቱ ፡ ክንፎችህን ፡ ጋርደህ ፡ ከመቃጠል ፡ እንዳዳንሃቸው ፡ እኔምንም ፡ አገልጋይህን ፡ በረድኤትህ ፡ ኃይል ፡ አድነኝ።

፰. ለአእናፊከ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ በጎ ፡ መዓዛ ፡ ያለው ፡ ሽቱ ፡ መመንጫ ፡ ለሆኑ ፡ አፍንጮችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። የንጽና ፡ የቅድስና ፡ መገኛ ፡ ለሆኑ ፡ ከንፈሮችህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ለሐና ፡ ልጅ ፡ ለማርያም ፡ ደስ ፡ የሚያሰኝ ፡ ምሥራች ፡ እንዳበሠርካት። ለኔም ፡ የምጸድቅበትን ፡ የምድንበትን ፡ የምሥራች ፡ አብሥረኝ። የመልካም ፡ ምሥራች ፡ መብሠር ፡ ለአንተ ፡ ክፍልህ ፡ ነውና።

፱. ለአፍከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ተጠራጣሪው ፡ ዘካሪያስን ፡ ለገሠፀው ፡ አፍህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ ፡ ደስታንና ፡ ፈገግታን ፡ ለሚያሳዩ ፡ የዕንቁ ፡ ባህርይ ፡ ላላቸው ፡ ጥርሶችህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ባሕርይህ ፡ ከኢዮብ ፡ መንፈስ ፡ ባሕር ፡ የተመሳሰለ ፡ የዝምታ ፡ መልአክ ፡ ነህና ፡ ዓመፃን ፡ እንዳይናገር ፡ ለአፌ ፡ ጠባቂ ፡ ሁነው ፡ ለከንፈሬም ፡ የትዕግስት ፡ መዝጊያ ፡ አብጅለት።

፲. ለልሳንከ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ማኅተመ ፡ ባሕርዩ ፡ ቃልህ ፡ ለሚሆን ፡ አንደበትህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። የባቢሎንን ፡ የእሳት ፡ ውዕየት ፡ ወደቀዝቃዛነት ፡ የለወጠ ፡ የእስትንፋስህ ፡ ጠልም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ጻድቃኖችን ፡ ሁሉ ፡ ለመርዳት ፡ የታመንክ ፡ ነህና ፡ አስቀድሞ ፡ ቂርቆስንና ፡ እናቱ ፡ ኢየሉጣን ፡ እንዳዳንካቸው ፡ እኔንም ፡ የመከራ ፡ ቁስል ፡ፐእንዳይጠዘጥዘኝ ፡ እንዳነዘንዘኝ ፡ ከእሳት ፡ ነበልባል ፡ አድነኝ።

፲፩. ለጉርኤከ ። የሚሰደስት ፡ጣዕመ ፡ ዜማ ፡ መፍለቂያ ፡ ለሆነው ፡ ጉረሮህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ዳግመኛም ፡ በንጽሕና ፡ ሐብል ፡ በአጌጠ ፡ አንገትህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ከላይ ፡ ከሰማይ ፡ ተልከህ ፡ ወደ ፡ ማርያም ፡ በወረድህ ፡ ጊዜ ፡ የእግዚአብሔር ፡ ቃል ፡ ያለድካምና ፡ ያለ ፡ ችግር ፡ ከሥጋዋ ፡ ሥጋ ፡ ከነፍሷ ፡ ነፍስ ፡ ነስቶ ፡ በመኅፀኗ ፡ አደረ ። የልዑልም ፡ ኃይል ፡ በሚያስደንቅ ፡ ግርማ ፡ ጠበቃት ፡ ጋረዳት።

፲፪. ለመትከፍትከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ የቅድስናን ፡ ልብሰ ፡ ተክህኖ ፡ ለተጎናጸፈ ፡ ትከሻህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ ። ረቂቅ ፡ የሚሆን ፡ የብርህን ፡ ሞጣሕት ፡ ለደረበ ፡ ዘባንህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ በጎ ፡ ነገር ፡ ለመናገር ፡ ለመጻፍ ፡ እችል ፡ ዘንድ ፡ የድርሰት ፡ መንፈስ ፡ አሳድርብኝ። ዕዝራ ፡ ዑራኤልን ፡ አጥብቆ ፡ በለመው ፡ ጊዜ ፡ ምሥጢርን ፡ የሚገልጽ ፡ መንፈስ ፡ በእሳት ፡ ጽዋ ፡ ግቶታልና ።

፲፫. ለእንግድዓከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሥነ ፡ ባሕርዩ ፡ ለማይመረመር ፡ ደረትህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ጻድቃኖች ፡ ሚጠለሉበት ፡ ለክንድህ ፡ ስፋትም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ፤ እግዚአብሔር ፡ ብቻውን ፡ ቢያውቅ ፡ እንጂ ፡ ስለ ፡ አንተ ፡ ተፈጥሮ ፡ ማንም ፡ ሆነ ፡ ማን ፡ አስቦ ፡ የሚደርስብህ ፡ የለም ፡ ባሕርይህም ፡ እንዴት ፡ እንደሆነ ፡ መርምሮ ፡ የሚያውቅ ፡ የለም።

፲፬. ለአእዳዊከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ እግዚአብሔር ፡ በመለኮታዊ ፡ ችሎታ ፡ አስተባብሮ ፡ለፈጠራቸው ፡ እጆችህና ፡ ለሁለቱ ፡ ረቂቃን ፡ ወርቾችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ የክርስቶስንና ፡ የወላጅ ፡ እናቱ ፡ ሐዋርያ ፡ አንተ ፡ ነህና ። እሳቱ ፡ ከማይጠፋ ፡ ትሉ ፡ ከማያቀላፋ ፡ የኩነኔ ፡ ጉድጓድ ፡ መንጥቀህ ፡ አውጣኝ።

፲፭. ለርናዕከ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ከዳራና ፡ ከቂሮስ ፡ እስከ ፡ ክርስቶስ ፡ መወለድ ፡ ያለውን ፡ ዘመን ፡ መጥኖ ፡ የከነዳ ፡ ክንድህና ፡ እደ ፡ ኩርናእህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ያዘኑትን ፡ የምታረገጋጋ ፡ ጸድቃንን ፡ የምትጎበኛቸው ፡ አንተ ፡ ስለሆንክ። ኀዘንን ፡ የሚያስረሳ ፡ የደስታ ፡ ወይን ፡ አጠጣኝ። ላዘኑ ፡ ለተከዙ ፡ ወይን ፡ ያጠጣቸው ፡ ዘንድ ፡ ሕግ ፡ ተሠርቷልና።

፲፮. ለእራኅከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ቡሩክ ፡ ጸጋን ፡ ለሚለግስ ፡ መጻፍህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ ። የክቡር ፡ መልአክ ፡ ጣቶች ፡ ለሚሆኑ ፡ ነበልባላዊ ፡ ጣቶችህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ወደእውነተኛው ፡ አምላክ ፡ አደራ ፡ አሰጠብቀኝ። በዚህ ፡ ዓለም ፡ ጧት ፡ ተናገረውን ፡ ማታ ፡ የሚደግም ፡ ዘመድ ፡ ወይም ፡ ወዳጅ ፡ አይገኝምና።

፲፯. ለአጽራረ ፡ አዲክ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ብርሃናትን ፡ ለተጎነጸፉ ፡ ለጣቶችህ ፡ ጽፍር ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። በሁለት ፡ እሳታውያን ፡ አክናፍ ፡ ለአሸበረቁ ፡ ጎኖችህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ስለኔ ፡ ሕይወቱን ፡ አሳልፎ ፡ የሰጠውን ፡ ፈጣሪ ፡ በአርአያህና ፡ በአምሳልህ ፡ የፈጠርከውን ፡ እንዴት ፡ ታጠፋዋለህ ፡ አሳምረህ ፡ ያነፅከውንስ ፡ ሕንፃ ፡ ሰለምን ፡ ታፈርሰዋለህ ፡ እያልክ ፡ ማልድልኝ።

፲፰. ለከርሥከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ምግቡ ፡ የምስጋና ፡ ጣዕመ ፡ ኅብስት ፡ ለሆነ ፡ ሆድህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። የሦቱ ፡ ሕዋሳት ፡ አካል ፡ መሥዋት ፡ ለሆነው ፡ ጽሩይ ፡ ልቡናህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ስለዚህም ፡ አንተ ፡ የህያዋን ፡ ሕያው ፡ ነህ። ሰው ፡ ግን ፡ ይሞታል ፡ ወደ ፡ መሬትነቱም ፡ የመለሳል። ሕይወቱም እንደ ፡ ጢስ ፡ ብን ፡ ብላ ፡ ትጠፋለችና ።

፲፱. ለሕሊናከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ምስጋናን ፡ በዝማሬ ፡ ድምጽ ፡ ለሚያሰማ ፡ ለሚያመሰግን ፡ ኃሊናህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። የሥጋዊ ፡ ባህርይ ፡ ከፍለ ፡ አካል ፡ ግን ፡ በባህርህ ፡ የሌለ ፡ ነው። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ የደኅንነት ፡ መልአክ ፡ ነህና ፡ እኔን ፡ አገልጋይህን ፡ ከችግር ፡ አውጣኝ ። ይልቁንም ፡ ጠላቴ ፡ ሰይጣን ፡ የመቅሠፍት ፡ እሳት ፡ ወላፈኑን ፡ በኔ ፡ ላይ ፡ በነዛ ፡ ጊዜ ፡ ፈጥነህ ፡ በክንፎችህ ፡ ጋርደኝ።

፳. ለአማዑቲከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ለሚጠሩት ፡ ፈጥኖ ፡ የሚሰማ ፡ ርኅሩህ ፡ እሳታዊ ፡ ነበልባላዊ ፡ አንጀትህን ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ አንተ ፡ በሁሉ ፡ ዘንድ ፡ አሸናፊ ፡ ነህ ። አንተ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ዘንድ ፡ መሥዋዕትን ፡ የሚያሣርጉ ፡ የካህናተ ፡ ሰማይ ፡ ሱራፌል ፡ ጓደኛ ፡ ነህ ፡ ምናልባት ፡ ቅዱስ ሚካኤል ፡ ቢተካከልህ ፡ እንጂ ፡ እንዳንተ ፡ ማን ፡ አለ።

፳፩. ለሕንብርትከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ሥነ ፡ ባሕርዩ ፡ ረቂቅ ፡ ለሆነ ፡ ሕንብርትህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። በብሩህ ፡ መብረቅ ፡ የተሸለመ ፡ ነበልባላዊ ፡ ወገብህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ እኔ ፡ ልበ ፡ ክፉ ፡ አፈ ፡ ጻድቅ ፡ ስሆን ፡ ንስሐ ፡ ሳልገባ ፡ በከንቱ ፡ እሞት ፡ ይሆን። እባክህ ፡ ቁርጡን ፡ ንገረኝ።

፳፪. ለአቁያጺከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ በሰማያዊ ፡ አምላክ ፡ ፊት ፡ ዘወትር ፡ ተንበርክከው ፡ ለሚሰግዱ ፡ ጉልበቶችህና ፡ አቁያጾችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ስንፍናን ፡ የምታወግዝ ፡ የዕውቀት ፡ ባለቤት ፡ እንደመሆንህ ፡ በዘመንህ ፡ ጥበብ ፡ በሰነፎች ፡ ልቡና ፡ አዳራሽ ፡ ሠራች ። ለአዳራሿም ፡ ሰባት ፡ አእማድ ፡ አቆመችላት።

፳፫. ለአእጋርከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ተውላጠ ፡ ስሙ ፡ ብልጣሶር ፡ ለሚባል ፡ በነቢዩ ፡ በዳንኤል ፡ ፊት ፡ በመገለጽ፡ በኤፍራጥስ ፡ ወንዝ ፡ ዳርቻ ፡ ለቆመ ፡ እግሮችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ከቀድሞ ፡ ጀምሮ ፡ ያዘኑትን ፡ የምታረጋጋ ፡ አንተ ፡ ነህና ። በመከራና ፡ በጭንቀት ፡ በባቢሎን ፡ የሚኖሩ ፡ የእስራኤልን ፡ ከምርኮ ፡ መመለስ። ለዚሁ ፡ ነቢይ ፡ በሕልሙ ፡ ነገረከው።

፳፬. ለሰኮናከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ በዚያ ፡ ድብልቅልቅና ፡ ሽብር ፡ በሆነበት ፡ ዕለት። ከጌታ ፡ እግረ ፡ መሰቀል ፡ ሥር ፡ ለቆሙት ፡ ተረከዞችህና ፡ ጫማዎችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ የጌታን ፡ ትዕግሥት ፡ የኤሁድን ፡ ግፍ ፡ ተመልክተህ ፡ በታላቅ ፡ አደባባ ፡ ላይ ፡ ሰይፈ ፡ ቁጣህን ፡ አምዘገግኸው። ቅዱሳት ፡ እንስት ፡ ግን ፡ ክርስቶስ ፡ ተነሥቷል ፡ ስላልካቸው ፡ የትንሣኤውን ፡ ምሥራች ፡ ይነግሩ ፡ ዘንድ ፡ ወደ ፡ ሐዋርያት ፡ ሔዱ።

፳፭፡ ለእጸብዒከ ። ገብርኤል ፡ሆይ፤ በእግሮችህ ፡ ላይ ፡ ለሚያበሩ ፡ ዓሥሩ ፡ ጣቶችህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። በብርሃንነትና ፡ በነጸብራቅነት ፡ ለሚተባበሩ ፡ ጥፍሮችህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ ሆይ፤ የትሕትናና ፡ የጽድቅ ፡ መምህር ፡ እንደመሆንህ ፡ መጠን ፡ በየዕለቱ ፡ በጎ ፡ በጎ ፡ ነገር ፡ አስተምረኝ። በኃላፊ ፡ ንብረቱ ፡ የሚመካና ፡ በሀብቱ ፡ ብዛት ፡ የሚተማመን ፡ የሰው ፡ ዘመድ (ወገን)፡ ሁሉ ፡ ሐሰተኛ ፡ ነውና።

፳፮. ለቆምከ ። ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ የማረጋገትን ፡ የደስታ ፡ መገኛ ፡ ለሆነው ፡ አካለ ፡ ቆምህ ፡ ሰላም ፡ እላለሁ። ከፍጥረተ ፡ ዓለም ፡ ለእስከዛሬው ፡ በሕያውነት ፡ ላለው ፡ ሥነ ፡ መልክእህም ፡ ሰላም ፡ እላለሁ።
ገብርኤል ፡ሆይ ፤ በየጊዜው ፡ የዘመኑን ፡ መድረስ ፡ አስረዳኝ። ልቡናዬ ፡ እስራኤል ፡ ከፋርስ ፡ ምርኮኝነት ፡ ነፃ ፡ እስከሚወጣበት ፡ ድረስ። ዳግመኛ ፡ ምድረ ፡ ርስት ፡ የምገባው ፡ መቼ ፡ ነው። እያኩ ፡ አስባለሁና።

፳፯. አልቦ ፡ እምሰብእ ። ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ከሰው ፡ ወገን ፡ ከቶ ፡ ጠዋትና ፡ ማታ ፡ እንደኔ ፡ ኀዘንና ፡ ትካዜ ፡ የሚበዛበት ፡ የለም። ከመላእክትም ፡ ወገን ፡ እንዳንተ ፡ ያዘኑትን ፡ የሚያረጋጋ ፡ የለም።
ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ስለዚህ ፡ እኔም ፡ አውቄና ፡ አንተን ፡ አምኜ። ይህን ፡ ያቀረብኩልህን ፡ ጸሎት ፡ እንደትልቅ ፡ ዋጋ ፡ ቆጥረህ ፡ የማረጋጋት ፡ ቃለህን ፡ አሰማኝ።

፳፰. የመላዕክት ፡ አለቃ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን። የጥንቱን ፡ የመዳን ፡ ተስፋ ፡ በመስበክ ፡ አዲስ ፡ የምሥራች ፡ ዜና ፡ ለመናገር ፡ በክብር ፡ ወደ ፡ ድንግል ፡ ማርያም ፡ ተላክህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ እልሃለሁ።

፳፱. የኤልሳቤጥ ፡ ልጅ ፡ ዮሐንስ ፡ ከተፀነሰ ፡ በኋላ ፡ ለዳዊት ፡ ልጅ ፡ ምስራች ፡ ትነግር ፡ ዘንድ ፡ ወደ ፡ ገሊላ ፡ ምድር ፡ የተላክህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ እልሃለሁ።

፴. ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን ፡ ድንግል ፡ ማርያምን ፡ ቃልህ ፡ ሰላም ፡ ላንቺ ፡ ይሁን ፡ ባላት ፡ ጊዜ ፡ ከሥጋዋ ፡ ሥጋ ፡ ከነፍሷ ፡ ነፍስ ፡ ነሥቶ ፡ ያን ፡ ጊዜ ፡ መለኮት ፡ ከሷ ፡ ሰው ፡ ሆነ።

፴፩. ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ፤ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁንና ፡ ድንግል ፡ ማርያምን ፡ ተፈሥሒ ፡ ደስ ፡ ይበልሽ ፡ ባልካት ፡ ጊዜ ፡ መንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ ሥጋዋን ፡ አነጻ ፡ የልዑል ፡ ኃይልም ፡ ጋረዳት ። ድንግል ፡ ማርያምና ፡ ሕፃኑ ፡ ልጅዋ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ክርስቶስ ፡ ካሉበት ፡ ምድረ ፡ ይሁዳ ፡ እስኪደርሱ ፡ ድረስ ፡ ሰብአ ፡ ሰገልን ፡ በኮከብ ፡ ምልክት ፡ የመራኻቸው ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ሰላም ፡ እልሃሁ።

፳፫. ገብርኤል ፡ ሆይ ፤ ለድንግል ፡ ደስታን ፡ በተመላ ፡ ቃል ፡ ሰላም ፡ ባልካት ፡ ጊዜ ፡ መለኮት ፡ ከሥጋዋ ፡ ሥጋ ፡ ከነፍሷ ፡ ነፍስ ፡ ነሥቶ ፡ ሰው ፡ ሆነ። ስለዚህም ፡ ምሐረትንና ፡ ፍርድን ፡ ታሰጠኛለህ ፡ በማለት ፡ እየተቀኘሁና ፡ ንጹሕ ፡ ዝማሬንም ፡ እየዘመርኩ ፡ ሰላም ፡ እልህ ፡ ዘንድ ፡ አቤቱ ፡ ተገለጽልኝ።

፴፬. በነደ ፡ እሳት ፡ ለተፈጠረክ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ እልሃለሁ። የብርሃን ፡ ራስ ፡ ወርቅ ፡ የተቀዳጀህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ እልሃለሁ።

፴፭. የአሸናፊና ፡ የኃይል ፡ መልአክ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ እልሃለሁ። ከፍጹም ፡ ጥፋት ፡ እድን ፡ ዘንድ ፡ ክንፍህን ፡ ጋርድልኝ።

፴፮. ወደ ፡ ድንግል ፡ የተላክህ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን። የደስታ ፡ ምሥራች ፡ ተናጋሪ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ፤ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ሁን። ነበልባላዊ ፡ ዖፈ ፡ ሰማይ ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን ። ደስታን ፡ አብሣሪ ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ሁን። የአካላዊ ፡ ቃልን ፡ የመጸነስ ፡ ብሥራት ፡ በማኅፀነ ፡ ማርያም ፡ ላሳደርክ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን።

፴፯. በመልአከ ፡ ሞት ፡ ከመውደቅ ፡ የምትታደግ ፡ ገብርኤል ፡ ሆይ ፡ ሰላም ፡ ላንተ ፡ ይሁን። አማላጅነትህን ፡ በመታመን ፡ ተስፋ ፡ እናደርጋለንና ፡ በመዓልትም ፡ በሌሊትም ፡ አንተ ፡ ጠብቀን ፡ አሜን።
አቡነ ዘበሰማያት
በሰላመ ገብርኤል

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

 # # # 🌟 ታላቅ የመንፈሳዊ ንግስ ጉዞ ጥሪ ወደ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም 🌟ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳኑ በረከት ለመሳተፍ፣ ነፍስን የሚያድስ እና እረፍት የሚሰጥ ታላቅ...
26/05/2026

# # # 🌟 ታላቅ የመንፈሳዊ ንግስ ጉዞ ጥሪ ወደ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም 🌟
ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳኑ በረከት ለመሳተፍ፣ ነፍስን የሚያድስ እና እረፍት የሚሰጥ ታላቅ የመንፈሳዊ ንግስ ጉዞ ተዘጋጅቶልዎታል።
በአንድነት ዘምረን፣ በጋራ ጸልየን በረከትን የምናፍስበት ልዩ መርሃ-ግብር፤ እርሶም ከነቤተሰብዎ ተመዝግበው የዚህ ድንቅ በረከት ተሳታፊ ይሁኑ!
# # # 📅 የጉዞ አማራጮች እና ዋጋ (ከሙሉ መስተንግዶ ጋር)
| የጉዞ ዓይነት | የጉዞ ዋጋ | መስተንግዶ |
|---|---|---|
| 🔄 የደርሶ መልስ ጉዞ | 2,100 ብር | ሙሉ መስተንግዶን ያጠቃልላል |
| ⛺ የአዳር ጉዞ | 2,400 ብር | ሙሉ መስተንግዶን ያጠቃልላል |
# # # 📍 የመነሻ ቦታዎች
* መስቀል አደባባይ
* መገናኛ
* ጣፎ
# # # 📞 ለበለጠ መረጃ እና ለምዝገባ
የቦታው ብዛት ውስን በመሆኑ ቀድመው በመደወል ቦታዎን ያስጠብቁ፦
📱 0933143133
> 📜 *"የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።"* (ያዕ 5:16)
> በረከቱ እንዳያመልጥዎ!

አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

26/05/2026

መድኃኔዓለም አብሮን ያለ ሰው ሲያልፍለት በስኬቱ ቀንተን ጥቁር ዶሮ ይዞ ጠንቋይ ቤት የሚሄድ ሳይሆን በጓደኛችን ስኬት ተደስተን አበባ ይዘን እንጦጦ ኪዳነምህረት እንድንሄድ የሚያደርግ ቀና ልብ ይስጠን።

25/05/2026

ጉዞ ወደ ቋራ በርሜል ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠበል
መነሻ ግንቦት 29 መመለሻ ሰኔ 10
መነሻ ቦታ፦ አዲስአበባ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ።
0933143133 ይደውሉ።

ትናንት በቅድስት ኪዳነምህረት ወርሃዊ በዓል ብጹዕ አቡነ ማርቆስ የተገኙበት የበረከት ቀን በጎሮ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን።  አገልግሎቱ ዘወትር ረቡዕ አርብ እና እሁድ በ ቀሲስ መ/ር ሄኖክ...
25/05/2026

ትናንት በቅድስት ኪዳነምህረት ወርሃዊ በዓል ብጹዕ አቡነ ማርቆስ የተገኙበት የበረከት ቀን በጎሮ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን።

አገልግሎቱ ዘወትር ረቡዕ አርብ እና እሁድ በ ቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም ይሰጣል።

❤ ፦

❤ ከየትኛውም አቅጣጫ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፤ ከጎሮ አደባባይ ወደ ኮዬ በሚወስደው አስፖልት ትንሽ ዝቅ እንዳላችሁ አስፓልቱ አጠገብ በስተ ግራ በኩል ቤተ ክርስትያኗ ትገኛለች።

❤ ከመገናኛ በቀጥታ ጎሮ ብለው ተሳፍራችሁ፣ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ወደ ኮዬ በሚወስደው አስፖልት ትንሽ ዝቅ እንዳላችሁ ቤተ ክርስቲያኗ ትገኛለች!

❤ ከመገናኛ 113 ቁጥር ይዘው ጎሮ አደባባይ ወርደው ትንሽ ዝቅ እንዳሉ ቤተ ክርስቲያኗ ትገኛለች!

❤ ከፒያሳ ከእሳት አደጋው ዝቅ ብሎ ኮዬ ፈጬ በሚለው 131 ቁጥር ባስ ይዘው ጎሮ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያኑ ጋር ይወርዳሉ!

❤ ከሜክሲኮ ሸበሌ ጋር 29 ቁጥር ባስ ይዘው ጎሮ አደባባይ ወርደው ትንሽ ዝቅ እንዳሉ ቤተ ክርስቲያና ትገኛለች!

❤ ከሲኤምሲ፣ ከአያት፣ ከሰሚት የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ወደ ኮዬ በሚወስደው አስፖልት ትንሽ ዝቅ እንዳላችሁ አስፖልቱ ጫፍ ትገኛለች!

❤ ከቃሊቲ፣ ከቱሉ፣ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጩ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ሳትደርሱ ወርዳችሁ ቤተ ክርስቲያኗ በስተቀኝ አስፖልቱ ዳር ትገኛለች፡፡

25/05/2026

ግንቦት 21 የንግስ ጉዞ ወደ ጻድቃኔ ማርያም
ደርሶ መልስ 2100 ብር፥ አዳር 2400 ብር ከመስተንግዶ ጋር።
0933143133
1000145090176 አቤኔዘር ገዛኸኝ

24/05/2026

እኛ የኦ/ተ/ቤ/ክ እምነት ተከታዮች ከሌሎች እምነቶች ጋር በጋራ የምናመልከውና በጋራ የምንጸልይለት አምላክ የለንም። "የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ። እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን" (ኢያ.24:15)

ምሽታችንን በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነምህረት ገዳም ❤ኪዳነምህረት በያለንበት የልባችንን መሻት ትፈጽምልን።  አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ
24/05/2026

ምሽታችንን በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነምህረት ገዳም ❤
ኪዳነምህረት በያለንበት የልባችንን መሻት ትፈጽምልን።
አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

24/05/2026

ጾመ ሐዋርያት የሚገባው ግንቦት 24 ሲሆን
ጾመ ድኅነት (ረቡዕ እና አርብ) ደግሞ ግንቦት 26 ይጀምራል።
አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ

መዓዛሽ ያውዳል ስምሽ ይጣፍጣልእመቤቴ ማርያም አንቺን ማን ይመስላልአዝ...የበላዔ ሰብ እመቤት ነሽ እና የቅዱሳን መንደር መኖሪያ ነሽናአሁንም ላነሳሳሽ እመቤቴ ብዬስምሽን እጠራለሁ ይሻለኛል ...
24/05/2026

መዓዛሽ ያውዳል ስምሽ ይጣፍጣል
እመቤቴ ማርያም አንቺን ማን ይመስላል
አዝ...

የበላዔ ሰብ እመቤት ነሽ እና
የቅዱሳን መንደር መኖሪያ ነሽና
አሁንም ላነሳሳሽ እመቤቴ ብዬ
ስምሽን እጠራለሁ ይሻለኛል ብዬ
ስምሽን እጠራለሁ ይሻለኛል ብዬ
አዝ...

ከቤተ መቅደሱ ከእጣኑ ሽታ
መዓዛሽ አወደኝ ድንግል የእኔ አለኝታ
ሁሉም ይደሰታል ሰዓሊለነ ሲባል
ለአፍም ይጣፍጣል ማርያም ማርያም ሲባል
ለአፍም ይጣፍጣል ማርያም ማርያም ሲባል
አዝ...

የህይወት መቅረዝ ነሽ የብርሃን እናት
ከሁሉ የምትበልጪ ድንግል የእኛ እመቤት
አልሻም ለመኖር ከአንቺ ተለይቼ
እኖራለሁ እና ፀጋን ተመልቼ
እኖራለሁ እና ፀጋን ተመልቼ
አዝ...

ከቅዱሳት አንስት አንቺ ትበልጫለሽ
ከሴቶች መካከል ድንግል ትለያለሽ
ወልድን በመውለድሽ የዓለም እናት ተባልሽ
ስለዚህ ድንግል ሆይ ማን ነው የሚመስልሽ
ስለዚህ እመቤቴ ማን ነው የሚመስልሽ
አዝ...

መዓዛሽ ያውዳል ስምሽ ይጣፍጣል
እመቤቴ ማርያም አንቺን ማን ይመስላል

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ:

Share