27/05/2026
🔔 የአቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ቤተሰቦች በሙሉ የተላለፈ ታላቅ የጥሪ ማስታወቂያ! 🔔
የ ሰኔ ሚካኤል ደረሰልን 💣💥
"የሰጠ ምስጉን ነው፤ ከተቀባይም ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው" (የሐዋ. ሥራ 20፥35)
ውድና የተከበራችሁ የአቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ ቤተሰቦች፤
በእግዚአብሔር ፈቃድና በቅዱሳኑ ጥበቃ በዓመት ሁለት ጊዜ የምናደርገው የጥቅምት መድኃኔዓለም እና የሰኔ ቅዱስ ሚካኤል የጋራ የዝክር መርሐግብራችን ዘንድሮ ለ3ኛ ተከታታይ ዓመት በታላቅ በረከት ሊካሄድ ዝግጅቱን ጀምሯል።
ይህ በጋራ የምንሰበስበውና ለነዳያን የምናደርሰው የፍቅር ስጦታ፣ በገጻችን ስም የምናበረክተው ትልቅ መንፈሳዊ ፍሬያችን ነው።
🍲 የዘንድሮው የሰኔ 12 መርሐግብር
እንደሚታወቀው መርሐግብሩ የሚውለው በሰኔ ጾም (በሐዋርያት ጾም) ወቅት በመሆኑ፣ እንደተለመደው የጾም ምግብ አዘጋጅተን ወገኖቻችንን የምንዘክርበት ይሆናል።
በዚህም መሠረት ለምግብ ማዘጋጃ የሚሆኑ የቁሳቁስ ድጋፎችን መሰብሰብ መጀመራችንን እናበስራለን፦
* 🛢️ ዘይት
* 🌶️ በርበሬ
* 🧆 ምስር እና የመሳሰሉትን የጥራጥሬ አይነቶች
🤝 እንዴት መሳተፍ ይችላሉ?
የዚህ የበረከት ድርሻ ተሳታፊ በመሆን በጸሎት፣ በሃሳብ፣ ቁሳቁስ በማበርከት እንዲሁም ይህንን መልእክት ለሌሎች Share በማድረግ አብረውን እንዲቆሙ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።
> "ምጽዋት ከሞት ታድናለች፥ ከኃጢአትም ሁሉ ታነጻለች።" (መጽሐፈ ጦቢት 4፥10) >
📍 ማሳሰቢያ፦ የእርዳታ ማስተባበሪያ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ አካውንት
ንግድ ባንክ 1000145090176
አቢሲኒያ 47056497
ቴሌብር 0933143133
ለበለጠ መረጃና በዋትሳፕ ለማውራት +251933143133 ይደውሉ ይጻፉ
የቅዱሳን አማላጅነትና ጸሎት አይለየን!
አቤኔዘር ዘተዋሕዶ ገፅ