25/12/2025
1⃣. ፨ይህን ፎቶ የምትመለከቱ በሀገር ውስጥም በመላውም ዓለም ያላችሁ ኢትዮጵያውያን ፦
፨ይህ ቦታ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በሞላሌ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኝ የጫ ደብረ ፀሃይ አቡነ ሀብተማርያም ቤ/ክ ነው ።
፨አድራሻ ፦ መነሻችሁን ከመላው የሀገሪቱ ክፍል አድርጋችሁ ወደ 👇
ዘብር ቅ/ገብርኤል
እመጓ ኡራኤልና
አርብሃራ መድኀኔዓለም ቤ/ክ ለምትጓዙ መዳረሻ ከሆነችው ሞላሌ ከተማ በ 1.8 ኪ.ሜ በቅርብ ርቀት የሚገኝ ቦታ ነው።
2⃣. #በዚህ ቦታ_ብዙ_ዓይነት እንዲሁም #ተዓምራት በፃዲቁ አቡነ ሀብተማርያም ፀበል ተደርጓል።
፨ፀበሉን ጠጥተውና ተጠምቀው፦ ከራስ ህመም ፥ ከወገብ ህመም ፣ ከሆድ ህመም እንዲሁም ከጨጓራ ህመምና ከደም ግፊት ድነዋል።
በተጨማሪም ለረጅም ጊዜ በዊልቸር የነበረ ድህነትን አግኝቶ ቆሞ ለመሄድ ችሏል።
3⃣. ይህ ቤ/ክ እንደምትመለከቱት ምንም ዓይነት ግንባታ ያልተደረገለት በመሆኑ ይህንን ፈዋሽ የሆነ ፀበል ጥራቱን የጠበቀ ፀበል ቤት ለማሰራትና ቤ/ክርስቲያኑን ለመገንባት በመታሰቡ በሀገር ውስጥም በመላውም ዓለም ያላችሁ ኢትዮጵያውያን፦
፨በፀሎታችሁ ፥ በሀሳባችሁ ፥ በጥሬ-ዕቃ እንዲሁም በገንዘባችሁና በጉልበታችሁ ቤ/ክርስቲያኑን ትረዱ ዘንድ በፃዲቁ ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
4⃣. ቤ/ክርስቲያኑ በራሱ ስም የተከፈተ የኢትዮያ ንግድ ባንክ እንዲሁም የአባይ ባንክ አካውንት ያለው በመሆኑ በተከፈተው የአካውንት ቁጥር በማስገባት ቤ/ክርስቲያኑን መርዳትና የበረከቱ ተካፋይ መሆን እንደምትችሉ ለማሳወቅ እንወዳለን።
#⃣. ✍ በተጨማሪም ቤ/ክርስቲያኑ
https://t.me/Yecha_Debre_Tsehay_26
የሚል የቴሌግራም ግሩፕ ያለው በመሆኑ ማንኛውንም ሀሳብ ለመስጠትና መረጃ ለማግኘትና እርዳታ ማድረግ ለምትፈልጉ በሙሉ በተለጠፈው የቤ/ክርስቲያኑ አስተዳዳሪና የአስተባባሪዎች ስልክ ላይ በመደወል ማናገር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
ወለወላዲቱ ድንግል!
ወለመስቀሉ ክቡር!
አሜን።