ማኅበረ ኪዳነምህረት ዘ አየር ጤና

ማኅበረ ኪዳነምህረት ዘ አየር ጤና ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ ሐሳቦችን በማፍለቅ በመግባባት፣በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::

15/02/2026
ዘወረደእንኳን አደረሳችሁ!ዘወረደ ማለት "ከላይ የመጣ፣ የወረደ'' ማለት ነው።  ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን "ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማ...
15/02/2026

ዘወረደ

እንኳን አደረሳችሁ!

ዘወረደ ማለት "ከላይ የመጣ፣ የወረደ'' ማለት ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን "ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም" እያለች በሰንበት ዋዜማ ዜማውን መሐትው (መግቢያ) አድርጋ የሳምንቱን ዜማ በማስተጋባት የጌታችንን ከሰማይ መውረድ ታመሠጥርበታለች፤ ታመሰግንበታለች። (ጾመ ድጓ፥ ዘዘወረደ ዋዜማ)
ይህን ሳምንት በልዕልና በዘለዓለማዊ ቅድስና እና በማትመረመር ጥበብ ራሱን ሰውሮ የሚኖር አምላክ በገሃድ ለሰው ልጅ የተገለጠበትን፣ ዘለዓለማዊ አምላክ ሰውን ከተደበቀበት ለመፈለግ ብሎ ''ኦ አዳም አይቴ ሀሎከ- አዳም ሆይ ወዴት ነህ" እያለ በማያልቅ የፍቅር ድምፅ ፍለጋ ወደ ዱር (ወደ ዓለም) የገባበትን ሳምንት የምንዘክርበት ነው። አምላካችን እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ምን ያህል በበዛ ፍቅሩ እንደሚፈልገው፣ ከፍ ላለ ዓላማውም እንዳጨው ያሳየበት፣ ከሁሉም ደግሞ በሕሊና ሊታሰብ የማይችለውን የሰማይ አኗኗሩን ትቶ በሚታይ የአዳም ሥጋ የተገለጠበት፣ መጋረጃው እሳት፣ ዙፋኑ እሳት፣ ልብሱ እሳት የሆነው አምላክ በሚበሰብስ ሥጋ የተገለጠበት፣ በጨርቅ፣ ያንን የሚያስደነግጥ መለኮታዊ ክብሩን ስለ ሰው ልጅ መዳን ተጨንቆ በሕፃን አምሳል ተገልጦ በበረት የተገኘበትን ሳምንት እናስብበታለን። ቅዱስ አትናቴዎስ የእግዚአብሔር ልጅ ለሰው ልጅ ድኅነት ሲል መወለዱን እንዲህ በማለት ይገልጠዋል፡፡ "ለዚሁ ዓላማ (ለሰው ልጅ ድኅነት) የማይበሰብስ፣ የማይሞት አካል ያለው የእግዚአብሔር ልጅ ወደዚህ ዓለም ገባ" (On the Incarnation: Saint Athanasius page 6)
ዘወረደ ከዚህ ትርጉም ባለፈ የአዳም ሳምንት ተብሎ ይጠራል። አዳምን ከጠፋበት ሊፈልግ፣ ከወደቀበት ሊያነሣ፣ ከገባበት ሊያወጣ የትንቢቱ ጊዜ በደረሰ ሰዓት ከብላቴናይቱ ድንግል ተወልዶ ተስፋ አዳም ተፈጽሞበታልና። “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤" እንዲል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ (ገላ.፬:፬)።
ሠለስቱ ምዕት በጸሎተ ሃይማኖት "ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ" (ጸሎተ ሃይማኖት) እንዲሉ በሥጋ የአዳምን ዘር ለማዳን ሰው ሆኖ ለአዳም የገባውን ኪዳን ፈጸመ። የሥጋ ዘመዳችንም ሆነ። (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ)
ሌላኛው ይህ ሳምንት ጾመ ሕርቃል በመባል ይታወቃል። ይህም በ፮፻፲፬ ዓ.ም የፋርስ ንጉሥ ኪርዮስ ኢየሩሳሌምን ወርሮ፣ አብያተ ክርስቲያናትን ዘርፎ እና መዝብሮ ክርስቲያኖችን ማርኮ ንግሥት ዕሌኒ ካሠራችው ቤተ መቅደስ የክርስቶስን መስቀል ዲያቆናትን አሸክሞ በምርኮ ወሰደ። ከምርኮ ያመለጡ ክርስቲያኖች ወደ ሮሙ ንጉሥ ከ፲፬ ዓመት በኋላ በ፮፻፳፰ ዓ.ም ለንጉሥ ሕርቃል ጩኹታቸውን ያሰማሉ፤ እርሱም በፋርሱ ንጉሥ በኪርዮስ ላይ ድል አግኝቶ መስቀሉን መለሰላቸው። በሕገ ቤተ ክርስቲያን ‹‹ሰው የገደለ ዘመኑን ሁሉ ይጹም›› የሚል በሐዋርያት ስለተደነገገ የንጉሡን ዕድሜ ተከፋፍለው አንድ ሳምንት ደርሶባቸው ስለ ንጉሡ ጾመወለታል፤ በዚህም የእርሱ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ይህ ሳምንት ጾመ ሕርቃል በመባል ይጠራል። እኛም ይህንን ዋቢ አድርገን እንጾማለን። (ምንጭ፡- ስንክሳር ዘወርኀ መጋቢት ፲)
ዘወረደ ከአርብዓው ዕለት የሚካተት ባይሆንም ቤተ ክርስቲያን ትእዛዝ አድርጋ ከአርብዓው ዕለታት ጋር ደምራ እንድንጾም ሕግ ሠርታለታች። እኛም እንደ ፈቃድ ሳይሆን እንደ ትእዛዝ ተቀብለን እንጾማለን።

ቅዳሴ፡- ቅዳሴ እግዚእ

"ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፡፡" ወንጌል (ዮሐ.፫፥፲-፩፬)
ምስባክ ዘነግህ:- (መዝ.፪፥፲፩) "ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ"
ምስባክ ዘቅዳሴ:- (መዝ.፪፥፲፩) “ተቀነዩ ለእግዚአብሔር፤ ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ፤ አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር፤ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፤ በረዓድም ደስ ይበላችሁ፤ ጌታ እንዳይቆጣ ተግሣጹንም ተቀበሉ፡፡”
መልእክታት:-
ሠራኢ ዲያቆን ዕብ.፲፫፥፲፯
ንፍቅ ዲያቆን ያዕ. ፬፥፮- ፍጻሜው
ንፍቅ ካህን የሐዋ. ፳፭፥፲፫-ፍጻሜ

ስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን!

የቅድስት ሥላሴ ወርኃዊ ጉባኤ! #ነገ ቅዳሜ ከ 11:30 - 2:00Mahibere KidaneMihret ማኅበረ ኪዳነምህረት ዘ አየር ጤና  ከካቴድራሉ ስብከተ ወንጌል ክፍል ጋር በአንድነት!👉 ...
13/02/2026

የቅድስት ሥላሴ ወርኃዊ ጉባኤ!

#ነገ ቅዳሜ ከ 11:30 - 2:00

Mahibere KidaneMihret ማኅበረ ኪዳነምህረት ዘ አየር ጤና ከካቴድራሉ ስብከተ ወንጌል ክፍል ጋር በአንድነት!

👉 ይህንን ወርኃዊ ልዩ የቅድስት ሥላሴ ጉባኤ በየወሩ በ7 ከቤተሰብዎና ከወዳጆ ጋር በቋሚነት ይሳተፉ፣ይደግፉ!

11/02/2026

አድራሻ፦ አየር ጤና ኪዳነምሕረት ፊት ለፊት! Mahibere KidaneMihret የአየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል ሚድያ ክፍል ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ የአየርጤና አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል ፍኖተ ጽድቅ ሰንበት ትምህርት ቤት #

የድንግል ማርያም ሞትና ታሪካዊ ማስረጃዎቹድንግል ማርያም ምንም እንኳ የአምላክ እናት ብትሆንም እንደ ማንኛውም ሰው የሞትን ጽዋ ቀምሳለች። ጥንታውያን አባቶች እንደሚሉት ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ...
29/01/2026

የድንግል ማርያም ሞትና ታሪካዊ ማስረጃዎቹ

ድንግል ማርያም ምንም እንኳ የአምላክ እናት ብትሆንም እንደ ማንኛውም ሰው የሞትን ጽዋ ቀምሳለች። ጥንታውያን አባቶች እንደሚሉት ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሲል በሥጋ እንደሞተ ሁሉ እናቱም የሰው ልጅ በመሆኗ የሞትን መንገድ አልፋለች። ይህ "ተፈጥሯዊ ሞት" ይባላል።

በቤተክርስቲያን ታሪክ "ዶርሚሽን" [Dormition] ወይም መኝታ/እንቅልፍ ተብሎ ይጠራል። ይህም ሞቷ እንደ ሌላው ሰው አስፈሪ ሳይሆን፣ በልጇ እቅፍ ውስጥ የሆነ የሰላም እንቅልፍ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመጀመሪያ መታወቅ ያለበት መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ድንግል ማርያም ሞት ዝም ማለቱ በወቅቱ የነበሩ ክርስቲያኖች ትኩረታቸው በክርስቶስ ትንሳኤ እና በወንጌል መስፋፋት ላይ በመሆኑ እንዲሁም በነበረው ስደት ምክንያት የታሪክ መዝገቦችን በይፋ ለመያዝ አስቸጋሪ ስለነበር ነው። ሆኖም ግን ከመጀመሪያዎቹ መቶ ክፍለ ዘመናት ጀምሮ ጠንካራ ማስረጃዎች አሉ። የእረፍቷ (ሞቷ) ማስረጃዎችን በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ማለትም፦ በጽሑፍ [ድርሳናት]፣ በታሪክ [የአባቶች ምስክርነት] እና በአርኪኦሎጂ [ቁፋሮ] ከፋፍለን ማየት እንችላለን።

ትራንሲተስ ማሪያ [Transitus Mariae] ድርሳናት
እነዚህ ድርሳናት በብዙ ጥንታዊ ቋንቋዎች የሚገኙ ሲሆን ዋነኛውና ጥንታዊው የሲርያክ ስሪት በሚከተለው መጽሐፍ ውስጥ በዝርዝር ተተርጉሞና ተተንትኖ ይገኛል፦ ይህም፦ ድንግል ማርያም በኢየሩሳሌም በሞተች ጊዜ ሐዋርያት መገኘታቸውንና ሥጋዋን ወደ ጌቴሴማኒ ወስደው እንደቀበሩት የሚገልጹ የመጀመሪያ ምንጮች ትንታኔ።ሐዋርያት ከቆጵሮስ፣ ከኤፌሶንና ከሌሎች ቦታዎች በደመና ተጭነው መምጣታቸውን፣ ማርያም በሰላም ማረፏንና ሥጋዋን በጌቴሴማኒ በአዲስ መቃብር እንደቀበሯት የሚገልጹትን ጥንታዊ ድርሳናት በዝርዝር ያቀርባል።¹

የቤተክርስቲያን አባቶች ምስክርነት[Patristic evidence]
ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ዘሳልሚስ፦ እርሱ እንደሚለው ምንም እንኳን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ አሟሟቷ በግልጽ ባይቀመጥም ማርያም መሞቷና መቃብሯም መታወቁ የማይካድ እውነታ መሆኑን ይገልጻል። በወቅቱ "አንቲዲኮማርያናውያን" [Antidicomarianites] ተብለው የሚጠሩ ወገኖች ለድንግል ማርያም ክብር ባለመስጠታቸው ሲወቅሳቸው እርሷ ግን በክብር እንዳረፈችና እንደተቀበረች የታወቀ ታሪክ መሆኑን በምክንያትነት ይጠቅሳል።²
ኢየሩሳሌሙ ኤጲስ ቆጶስ ጁቬናል (Juvenal of Jerusalem)፦ በ451 ዓ.ም በኬልቄዶን ጉባኤ ወቅት፣ ለንጉሥ ማርክያን የሰጠው ምስክርነት ትልቅ የታሪክ ማስረጃ ነው። ማስረጃውም ንጉሡ የድንግል ማርያምን ሥጋ ፈልጎ በነበረበት ወቅት ጁቬናል "እርሷ በሐዋርያት ፊት ማረፏን፣ ነገር ግን መቃብሯ ባዶ ሆኖ መገኘቱን" በይፋ መስክሯል። ይህም በ5ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ስለ ሞቷና ትንሳኤዋ የነበረው እምነት የጸና መሆኑን ያሳያል።³

የአርኪኦሎጂ ማስረጃ [Archaeological Evidence]
የጌቴሴማኒ መቃብር በኢየሩሳሌም የሚገኘው የድንግል ማርያም መቃብር ትልቁ ቁሳዊ ማስረጃ ነው። በ1972 ዓ.ም ቤላርሚኖ ባጋቲ [Bellarmino Bagatti] የተባለ ፍራንሲስካዊ አርኪኦሎጂስት በመቃብሩ ላይ ጥናት አድርጓል። በጥናቱም መቃብሩ በ1ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የአይሁድ የቀብር ሥርዓት መሠረት የተዘጋጀ "bench tomb" መሆኑን አረጋግጧል። ይህም መቃብሩ ከጥንት ጀምሮ ለድንግል ማርያም የተለየ መታሰቢያ ሆኖ ሲያገለግል እንደነበር ያሳያል።⁴

የኢትዮጵያ ስንክሳር (ጥር 21)
ይህ የቤተክርስቲያን የታሪክ መዝገብ በዕለቱ በሚነበበው ንባብ ላይ የሚከተለውን ሐሳብ ይዟል፦ ድንግል ማርያም ጥር 21 ቀን ማረፏን፣ ጌታ ነፍሷን መቀበሉን፣ ሐዋርያትም ሥጋዋን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሊቀሙና ሊያቃጥሉ እንደሞከሩ፣ ነገር ግን በመለኮታዊ ኃይል እንደተጠበቀችና በክብር እንደተቀበረች ይተርካል።⁵

የሐዋርያት ትምህርትና ትውፊት [Apostolic Tradition]
በቤተክርስቲያን ትውፊት መሠረት፣ ሐዋርያው ዮሐንስ [ድንግል ማርያምን እንዲጠብቅ አደራ የተሰጠው] እስከ እረፍቷ ድረስ አብሯት እንደነበር ይታመናል። ይህንንም ትውፊት ተከታዮቹ የቤተክርስቲያን አባቶች [ለምሳሌ ቅዱስ ፖሊካርፐስ እና አግናጥዮስ] በቃል ሲያስተላልፉት ቆይተዋል።

ምንም እንኳን መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሞቷ ዝርዝር ባይሰጥም፣ የጥንት ክርስቲያኖች በጽሑፍ (Manuscripts)፣ በመቃብሯ ቦታ (Archaeology) እና በቤተክርስቲያን በዓላት (Liturgy) አማካኝነት ድንግል ማርያም መሞቷን ለትውልድ አስተላልፈዋል። እነዚህ ማስረጃዎች ሁሉ የሚስማሙበት ነጥብ "ድንግል ማርያም በተጨባጭ መሞቷንና የተቀበረችበትም ስፍራ በኢየሩሳሌም ጌቴሴማኒ መሆኑን" ነው።

እኔም በመጨረሻ “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐፅብ ለኲሉ - ሞትስ ለሟች ይገባዋል የማርያም ሞት ግን ለሁሉ ያስደንቃል” ብዬ ጽሁፌን ዘግቼዋለው እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ!

ዋቢ መዛግብት👇
¹ The Dormition and Assumption of the Virgin Mary
² The Panarion of Epiphanius of Salamis: De Fide. Books II and III
³ On the Dormition of Mary: Early Patristic Homilies
⁴ The Church of the Virgin Mary in Gethsemane,1975
⁵ ስንክሳር ዘወርኅ ጥር

https://t.me/orthodox_chrstianity

++ ሥርዓተ ማኅሌት ዘአስተርእዮ ማርያም +++ መልክአ ሥላሴሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፣ ተፈጸመ ተስፋ አበ...
28/01/2026

++ ሥርዓተ ማኅሌት ዘአስተርእዮ ማርያም ++

+ መልክአ ሥላሴ
ሰላም ለኲልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወጸ በሣህል፤ እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፣ ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል።

ዚቅ
ሃሌ ሉያ ለአብ፤ ሃሌ ሉያ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሥላሴ ዋህድ፤ ዕፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ፤ ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ፤ ዮሐንስ በልብሱ ከደነ ገፃ።

ወረብ
እፎኑመ እመ አምላክ በከየት ደንጊፃ በከየት እመ አምላክ/፪/
ከመ ኲሉ ሰብእ ሞት ሶበ ሐወጻ በከየት/፪/

+ ዘመንክር ጣዕሙ
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤
ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤
መሠረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤
ኪያኪ ሠናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤
እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኮት ስሙ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ መጽአ ውስተ ዓለም፤ ወዓለሙኒ ኢክህለ ፀዊሮቶ፤ ፆረቶ ወአግመረቶ ማርያም።

ነግሥ
ለምንት ይዜኃር ኃያል በኃይሉ፤
ወባዕል በብዝኃ ብዕሉ፤
ኢያድለወ ሞተ ክርስቶስ ለሥጋ አባሉ፤
ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ፤
ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ።

ዚቅ
እንበይነዝ አእምሩ በውስተ ፍትሕ ኢያደሉ፤ ትጥዓም ሞተ እሙ ወእመ ኲሉ፤ አዘዘ ወልድ በርቱዕ ቃሉ።

+ መልክአ ማርያም
ሰላም ሰላም ለዝክረ ስምኪ ሐዋዝ፤
እምነ ከልበኔ ወቊስጥ ወእምነ ሰንበልት ምዑዝ፤
ማርያም ድንግል ለባሲተ ዓቢይ ትእዛዝ፤
ይስቅየኒ ለለጽባሑ ወይነ ፍቅርኪ አዚዝ፤
ከመ ይሰቅዮ ውኂዝ ለሠናይ አርዝ።

ዚቅ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ፤ ወአግአዛ እምእኩይ ውስተ ሠናይ፤ እሞት ውስተ ሕይወት፤ ወረሰየ ይዝክሩ ስማ ውስተ ኲሉ ዓለም።

ወረብ
ለዛቲ ድንግል ሠረቀ ላዕሌሃ ብዕለ ጸጋሁ ለአብ/፪/
ወአግአዛ እምእኩይ ውስት ሠናይ እሞት ውስተ ሕይወት/፪/

+ መልክአ ማርያም
ሰላም ለእስትንፋስኪ ዘመዓዛሁ ሕይወት፤
ከመ መዓዛ ዕፅ ኅሩይ ዘውስተ ገነት፤
ማርያም ድንግል ቤተ ቅድሳት፤
ጽንሕኒ ውስተ ሠናይ ወሰውርኒ እሞት፤
በአክናፍኪ ርግብየ ኅሪት።

ዚቅ
አንጺሆ ሥጋሃ ቀዲሶ ኪያሃ፤ ኃደረ ቃል ላዕሌሃ፤ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፤ ወይቤላ ለድንግል፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ሰሎሞን ይቤላ እኅትየ መርዓት ርግብየ ሠናይት፤ ፍናወ ዚአኪ ገነት፤ እስመ ኪያኪ ኀረየ ለታዕካሁ፤ ከመ ትኩኒዮ ማኅደረ ለልዑል።

ወረብ
'አንጺሆ ሥጋሃ'/፪/ ላዕሌሃ ኃደረ/፪/
ቀዲሶ ኪያሃ 'ሃሌ ሉያ'/፪/ ይቤላ ለድንግል/፪/

+ መልክአ ማርያም
ሰላም ለገቦኪ ዘሐመልማለ ወርቅ ክዳኑ፤
በከመ ዳዊት ይዜኑ፤
ማርያም ድንግል ለያዕቆብ ሞገሰ ስኑ፤
በልኒ እግዝእትየ አፈቅረከ አኮኑ፤
እንዘ ረዳኢትከ አነ ዘይክለከ መኑ።

ዚቅ
እምሰማያት ወረደ ወገብረ መድኃኒተ በማዕከለ ምድር፤ ኖላዊ ኄር ኖላዊሆሙ ለ፳ኤል፤ ወረደ ስኖ ለያዕቆብ ዘአፍቀረ፤ ወስኑሰ ለያዕቆብ ዘይቤ ይእቲ ሥጋ እንተ ነሥአ፤ መድኅን እማርያም።

ወረብ፦
ወስኑሰ ለያዕቆብ 'ዘይቤ'/፪/ ያዕቆብ/፪/
'ይእቲ ሥጋ'/፪/ እማርያም እንተ ነሥአ መድኅን/፪/

+ መልክአ ማርያም
ሰላም ለፀአተ ነፍስኪ እንበለ ፃዕር ወፃማ፤
ለነቢር ዘልፈ በየማነ ወልድኪ ፌማ፤
ማርያም ድንግል ለባሲተ ሞገስ ወግርማ፤
አጽንዒ በረድኤትኪ ለሕይወትየ ድካማ፤
እምሕይወተ ኄራን አበው ኢታሕጽጺ ዐቅማ።

ዚቅ
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና፤ ጠሊላነ ንግሥ ሶቤሃ ከደና።

ወረብ
ጊዜ ዕረፍታ ለማርያም 'ጊዜ'/፫/ ዕረፍታ ለማርያም/፪/
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ/፪/

መልክአ ማርያም
ሰላም እብል በድነ ሥጋኪ ጽሩየ፤ ዘተመሰለ ባሕርየ፤ ማርያም ድንግል ዐጸደ ወይንየ፤ ንስቲተ ለዕበየኪ እንተ አቅረብኩ ግናየ፤ ኢይትኃደግ ዲበ ምድር ምሥጢ ሰማየ።

ዚቅ
ኦ ትቤ ማርያም እወጽእ እምዝንቱ ሥጋየ፤ ወአሐውር ውስተ ሕይወት ዘለዓለም፤ ኦ ተዘከርኬ ዮሐንስ ዘይቤለከ ሊቅ አመ ትረፍቅ ዲበ ዕንግድዓሁ።

+ መልክአ ማርያም
ሰላም ለግንዘተ ሥጋኪ በእደ ሐዋርያት አርጋብ፤ በአፈወ ዕፍረት ቅድው ዘሐሳበ ሤጡ ዕፁብ፤ ማርያም ድንግል ወለተ ኅሩያን ሕዝብ፤ ረሰይኩኪ እግዝእትየ ህየንተ እም ወአብ፤ ይሕፅነኒ ከመ ጥብ ፍቅርኪ ሐሊብ።

ዚቅ
ተጋብኡ በቅጽበት ለግንዘተ እሙ ቅድስት፤ ብፁዓን ሐዋርያት ቦኡ ኀቤሃ፤ በሰላም አምኁ ኪያሃ፤ በስብሐት ገነዙ ሥጋሃ።

+ መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለጌቴሴማኒ በመርኅባ፤ እንተ ይእቲ ለኢየሩሳሌም ቅሩባ፤ ማርያም ድንግል ለሀገረ መንግሥት ርግባ፤ ትትሜጦ ወረቀ እምአፌር ወጸበለ አፈው እምሳባ፤ ጌቴሴማኒ ለሥጋኪ ምስካባ።

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤ ዓውዳኒ ዘጽድቅ ወመርኅባኒ ዘዕንቊ፤ አንቀጸ አድኅኖ ሐዳስ ንጽቅ።

+ መልክአ ማርያም
ሰላም ለመቃብርኪ ለኢየሩሳሌም በአድያማ፤ እንተ ይእቲ ጌቴሴማኒ ስማ፤ ማርያም ሰንበት ዕረፍተ ጽዑራን እምፃማ፤ አመ ኀደረ ላዕሌኪ ፀሐየ ቅዱሳን ዘራማ፤ ኃይለ ልዑል ጸለለኪ በመንክር ግርማ።

ዚቅ
ኢይሜንንዋ ኪያሃኒ ወአድያሚሃኒ ነያ ጽዮን ቅድስት ሀገረ እግዚአብሔር።

+ ማኅሌተ ጽጌ
እግዚአብሔር ጽጌ ትንቢት ለቢሶ ሥጋኪ ሥጋ ዚአነ፤ አመ አስተርአየ በምድር ወተአምረ ለነ፤ ንዌድሰኪ እንዘ ንብል ምክሃ ዘመድነ፤ ዮም በፍሥሃ ለማርያም እምነ፤ አስተርእዮ በሰማይ ኮነ።

ዚቅ
አስተርአየ ዘኢያስተርኢ፤ ኮነ እሙነ አስተርእዮቱ ለመድኃኒነ ክርስቶስ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ እምድንግል ተወልደ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በሥጋ ረቂቅ፤ እሙነ ኮነ አስተርእዮቱ፤ በ፴ ክረምት በዮርዳኖስ ተጠምቀ፤ በበህቅ ልህቀ።

+ አንገርጋሪ
ኢኮነ ነግደ ወፈላሴ ሀገሪቶሙ ለቅዱሳን፤ ንሕነ ሰብአ ቤቱ ለእግዚአብሔር ኲልነ፤ አምላክ ኀደረ ውስተ ሥጋ ተአቊረ፤ እንዘ ኢይትጋባዕ በሙላድ፤ ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂዎ፤ ዘኪሩቤል ኢርእዮ።

አመላለስ
ዘድንግል መናሥግተ ኢያርኂሆ/፪/
ኢያርኂሆ ዘኪሩቤል ኢርእዮ ኢያርኂዎ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

ወረብ
'አምላክ ኀደረ'/፪/ ውስተ ሥጋ ተዓቊረ እንዘ ኢይትጋባዕ አምላክ ኀደረ/፪/
ዘድንግል መናሥግተ 'ኢያርኂዎ'/፪/ ኢርእዮ ዘኪሩቤል/፪/

+ እስመ ለዓለም ዘሰንበት፦
ዮም ንወድሳ ለማርያም፤ በእንተ ዘተወልደ እምኔሃ፤ መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ። ጾረቶ በከርሣ፤ ውእቱኒ ቀደሳ፤ መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ፤ እግዚአ ለሰንበት፤ ወአቡሃ ለምሕረት፤ መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ፤ አማን መላእክት ይኬልልዋ

አመላለስ፦
መንክር ግርማ ኃይለ ልዑል ጸለላ/2/
አማን መላእክት ይኬልልዋ/4/

© ማኅሌታውያን

እንኳን አደረሳችሁ ለእናታችን ዕለት 😍ያብፅሀነ አመ ከመ ዮም አሜን!!! ❤ በእውነቱ በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ታላቁ የበዓለ ጥምቀት አገልግሎት አለቀብን። የረዳንን ሥላሴን እናመሰግናለን!...
24/01/2026

እንኳን አደረሳችሁ ለእናታችን ዕለት 😍

ያብፅሀነ አመ ከመ ዮም አሜን!!!

❤ በእውነቱ በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ታላቁ የበዓለ ጥምቀት አገልግሎት አለቀብን። የረዳንን ሥላሴን እናመሰግናለን! ከፊቱ ለአገልግሎትና ለምስጋና መቆምን እንደ ቸርነቱ አልከለከለንምና፤ አልባሰ ምክኅ ለእርቃንነ ኪዳነ ምሕረት እናታችን ከኃጢአተኛ ሰው አገልግሎትና ምስጋና ለምኔ ነው አላለችንምና።

🙏 የሥራ ጊዜአችሁን በመተው አገልግሎቱ እንዲሳካ በማስተባበር የተጋችሁ፣ ምንጣፍ በመሸከም፣መዝሙር በማስጠናትና በማጥናት ብሎም በ3ቱም ቀናት በማመስገን፣ነጋሪት በመምታትና መለከት በመንፋት፣ ሰረገላ በመግፋት፣ሠንደቅ ዓላማዎችን በመስቀል፣አስፓልት በማጠብ ለዚህ በዓል የለፋችሁ የደከማችሁ እንዲሁም ደከመኝ ሳትሉ ጥሩ ጥሩ የአገልግሎት ማስታወሻ ፎቶዎችን ያነሳችሁንን የሚዲያ ክፍል አባላቶች ጨምሮ ሁላችሁም ሥላሴ ድካማችሁን ይቁጠርላችሁ።

➡️ የማኅበሩና የአገልግሎቱ የጀርባ አጥንቶች በጎ አድራጊ ምእመናን

➡️ ከካቴድራላችን ሰበካ ጉባኤ አንስቶ---ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ፍኖተ ጽድቅ ሰ/ት/ቤት፣ማኅበረ ሙሴ ጸሊምና ናታኒም፣ የኪዳነ ምሕረት፣ የመስኪድ እና የደብረ አባይ ሰፈር ወጣቶች

➡️ የየሦስቱም አጥቢያ ሰበካ ጉባኤ፣ሰ/ት/ቤቶች፣ማኅበራትና ወጣቶችና ማኅበረ ቅዱሳን

ሁሉን አንስተን አንጨርስምና በየፊናው ያገለገልነውን በሙሉ ከከንቱ ውዳሴ ጠብቆ ሰማያዊ ዋጋ ያድርግልን።

በመምራት፣በመናገርና በአገልግሎት ሳናስበው ያስቀየምነውን ሁሉ ይቅርታችሁን አትንፈጉን🙏

በቅርቡ የምስጋናና የግማሽ ዓመት ጠቅላላ ጉባኤ የምናደርግ ሲሆን ሁላችንም ተዘጋጅተን ስለነበረንና ወደፊት ስለሚኖረን አገልግሎት እንመካከራለን። ቀኑን የምናሳውቅ ይሆናል።

"አገልግሎት ስላለን አንታክትም" ፪ኛ ቆሮ. ፬:፩

"የተጠመቃችሁባትን ቀን አስቡ" ቅ.ዮሐ.አፈ.ተግ

ማኅበረ ኪዳነ ምሕረት ዘ አየር ጤና!

23/01/2026

😍 ታናሿ ሙሽራ 😍

https://www.tiktok.com/
ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ Mahibere KidaneMihret @

Address

Ayertena
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ማኅበረ ኪዳነምህረት ዘ አየር ጤና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share