Abenezer Teklu Diyakon

Abenezer Teklu  Diyakon Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Abenezer Teklu Diyakon, Convent and monastery, addis abeba, Addis Ababa.

"... ሴናተር ምን እያልክ እንደ ኾነ አላውቅም፤ ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ባለኝ እምነት አላፍርም። እናም በዚህ ልታሳፍረኝ ከፈለግህ ቀጥልበት ..." ይህን ንግግር የተናገረው የአሜሪካው...
01/05/2026

"... ሴናተር ምን እያልክ እንደ ኾነ አላውቅም፤ ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ባለኝ እምነት አላፍርም። እናም በዚህ ልታሳፍረኝ ከፈለግህ ቀጥልበት ..."

ይህን ንግግር የተናገረው የአሜሪካው Secretary of War (የጦርነት አውድማ "አመቻች") Pete Hegseth ነው። ንግግሩ ለአንድ እውነተኛ ክርስቲያን ድንቅ ምስክር ነው። ዘወትር ግን ጥያቄ የሚኾንብኝ፣ ጦርነት ወዳድ መሪዎች ለምን ከክርስትና ጋር ሄደው እንደሚጣበቁ አይገባኝም። ክርስትና የጦር'ነት ጠ'ላት፤ ጦርነት ደግሞ የሰው ልጅ ዐመ'ፅ ውጤት እንደ ኾነ ይዘነጉታል ልበል?!

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek

“በወንጌል ሕይወታችን ኾነ” “በወንጌል ሕይወታችን ኾነ” በሚል መሪ ቃል፣ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገር አቀፍ የወንጌል ቀን ለሦስተኛ ጊዜ ባለፉት ኹለት ቀናት አክብራ አሳልፋለ...
30/04/2026

“በወንጌል ሕይወታችን ኾነ”


“በወንጌል ሕይወታችን ኾነ” በሚል መሪ ቃል፣ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አገር አቀፍ የወንጌል ቀን ለሦስተኛ ጊዜ ባለፉት ኹለት ቀናት አክብራ አሳልፋለች። ይህም በዋናነት ትኵረት ያደረገው፣ የወንጌልን ትምህርት በቋንቋ ተደራሽ ለማድረግ ከቀደሙት ዓመታት ይልቅ በተለየ ኹኔታ በማሰብ እንደ ኾነ ተገልጦአል። የቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ እንዳሉትም፣ “የቤተ ክርስቲያን መሠረታዊ ዓላማ ምዕመናንን በቃለ እግዚአብሔር ወንጌል አንፆ ለክርስቶስ ዳግም ምጽአት ማዘጋጀት እንደ መኾኑ መጠን፣ ሰባክያን ምሳሌ ባለው ሕይወት ሊያገለግሉ ይገባል።” ብለዋል። ተያያዥነት ባለው መልኩ፣ በተለይም ወንጌል ለሚያገለግሉ ሰባክያን ልዩ ትኵረት እንዲሰጥና፣ ሰባክያኑም አገልግሎታቸው “ተልእኮ ተኰር” እንዲኾን ከታዳሚው በተደጋጋሚ ተጠቅሶአል።

ሐዋርያዊ ተልእኮ ከተደራሽነት አንጻርም ብዙ ክፍተቶችና ጉድለቶች ያሉበት በመኾኑ፣ እንደ መፍትሔና የአቋም መግለጫ፣ በብዙ ቋንቋ፣ ከከተማ ይልቅ ወደ ገጠር በማድላትና ዓለም ዓቀፍ ይዘት እንዲኖረውም በሚያሳስቡ መልእክቶች ታጅቦ ቀኑ ተከብሮ ወይም ታስቦ ውሎአል። በመርሐ ግብሩ መጨረሻ ላይም፣ ለረጅም ዓመታት ቤተክርስቲያንን በታማኝነት ላገለገሉና አርአያ የሚሆን ተግባር ለፈጸሙ አባቶችና አገልጋዮች የተለያዩ ሽልማቶችን በማበርከት ጉባኤው ተጠናቅቆአል።

በዚህ ጉባኤ ላይ ያለኝን አድናቆትና ትዝብት ላጋራ፣

1. “በወንጌል ሕይወታችን ኾነ” በሚል መሪ ቃል ይህ መርሐ ግብር መዘጋጀቱ በራሱ፣ እጅግ ይበል የሚያሰኝ ነው፤ ምክንያቱም ያለ ወንጌል ሕይወት ሊኾን ጨርሶ አይችልምና። ጌታችን ኢየሱስ “ሕይወት እኔ ነኝ” አለ (ዮሐ. 11፥25)፤ ርሱ የሚሰጠን የዘላለም ሕይወት ደግሞ ለዘላለም የማይጠፋ ነው (ዮሐ. 10፥28)፤ ላመኑት ደቀ መዛሙርትም፣ “እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።” (ዮሐ. 10፥10) በማለቱ፣ ክርስቶስ የተትረፈረፈ ሕይወት መኾኑን ነገረን። በርግጥ አማናዊው ወንጌል ክርስቶስ ሕይወታችን ኾኖአል። ክብር ይኹንለት።
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይህ “ሕይወት በዚህ ልክ” መታሰቡ፤ በእምነት መነገሩ፤ መሪ ቃል መኾኑ፣ ሰዎች ስለዚህ ሕይወት ብቻ በማናቸውም መንገድ ሲወያዩ ማየት ከልብ ያረካል። ዛሬም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ርቱዕ በኾነ መንገድ “በወንጌል ብቻ ሕይወት እንዲኾን” ከልብ እንመኛለን፤ እንጸልያለን፤ እጅግ በጣም እንናፍቃለን!

2. “ለረጅም ዓመታት ቤተክርስቲያንን በታማኝነት ላገለገሉና አርአያ የሚሆን ተግባር ለፈጸሙ” በሚለው መርኅ ውስጥ ከተካተቱት አንዷ ፋንቱ ወልዴ ናት። ትዝብቴ ከርሷ መመረጥ ይጀምራል። ፋንቱ ከተወሰኑ ዓመታት በፊት “ስሟ ከወንጌል ነቀፋ ጋር” ሲነሳ ነበር። ነገር ግን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ “ስለ ወንጌልና ስለ ክርስቶስ ብቻ” የሚዘምሩ ወንድሞችና እህቶችን በማሳደ'ድ፤ በማስ'ኮብለል፣ ወደ ኋላ እንዲያፈገፍጉ በማድረግ፣ ብሎም በዓውደ ምሕረት ጭምር በአደባባይ በማሸ'ማቀቅ የተጠመደች ሴት ናት። ከዚህ የተነሳ እውነት ለመናገር “ታማኝነትና አርዓያነት” ከርሷ ይታያል ብሎ መጠቀሱ ለትዝብት ይዳርጋል። ከርሷ እጅግ በተሻለ ይህ መስፈርት “የሚገባቸው” አሉና ይህ ለወደፊቱ ቢስተካከል ብዬ አምናለኹ።
ከዚህ በዘለለ ስለ ወንጌል ሕይወትነት በማናቸውም መንገድ መነገሩ እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነው፤ ጌታ እግዚአብሔር ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን “ለሕይወትና ለመዳን በሚኾን ወንጌል ያጥለቅልቃት”፤ አሜን።

Telegram link - https://t.me/ebenezertek
Blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2026/04/blog-post_29.html

ወንጌል በመንፈስ ለደኸዩ ከእግዚአብሔር የተሰጠች መንፈሳዊ ብልጥግና ናት!አሜን።
29/04/2026

ወንጌል በመንፈስ ለደኸዩ ከእግዚአብሔር የተሰጠች መንፈሳዊ ብልጥግና ናት!
አሜን።

መሪዎች ከአገራቸው ለሚሰደዱ ወይም ለተሰደዱ፣ ለድኾች እንባና ሰቆቃ ሩቅ ናቸው።  ምክንያቱም የሚያወሩት ከስብራታችን ጋር አይገጥምም። ለአገሬ እናቶች ለመንደር ዕንቦቃቅላዎች የቀዬው ሰላም፣ ...
27/04/2026

መሪዎች ከአገራቸው ለሚሰደዱ ወይም ለተሰደዱ፣ ለድኾች እንባና ሰቆቃ ሩቅ ናቸው። ምክንያቱም የሚያወሩት ከስብራታችን ጋር አይገጥምም። ለአገሬ እናቶች ለመንደር ዕንቦቃቅላዎች የቀዬው ሰላም፣ የማሳው ሰብል ሲጠበቅላቸው ብቻ ነው ነገን የማይሰጉትና በሰቀቀን የማይሰደዱት። አልያ ግን እንዲህ ያለ "ዕጣ ፈንታ አይገጥምም" ማለት ዘበት ነው። ቤተሰብን በተለይ ሕፃናትን የዘነጋ መንግሥትና ማኅበረ ሰብ፣ በምድር ላይ ጨካኝና እጅጉን አስፈሪ ነው ብል ግነት የለበትም። እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ብቻ ለፍጥረቱ በርኅራኄ መጋቢ ነህ። አሜን።
የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek

ግፍን የሚደግፍ ቀድሞውኑ "ዘማሪ" ነው ወይ? ዘፈንና ዘፋኝነትን ማጋፈር ከተፈለገ፣ የማይገባ ንጽጽር ማቅረብ ለምን ያስፈልጋል?!  እውነትንስ ዘፋኝ መንደር አውርዶ ማልኮስ'ኮስ የተገባ ነውን...
24/04/2026

ግፍን የሚደግፍ ቀድሞውኑ "ዘማሪ" ነው ወይ? ዘፈንና ዘፋኝነትን ማጋፈር ከተፈለገ፣ የማይገባ ንጽጽር ማቅረብ ለምን ያስፈልጋል?! እውነትንስ ዘፋኝ መንደር አውርዶ ማልኮስ'ኮስ የተገባ ነውን?!

“በመንፈስ ተመላለሱ” (ገላ. 5፥16) ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፣ “የሥጋ ምኞት በመንፈስ ላይ፣ መንፈስም በሥጋ ላይ ነውና፤ ልታደርጉ የምትወዱትን እንዳታደርጉ እነዚህ እርስ በርሳቸው ይቃረናሉ...
24/04/2026

“በመንፈስ ተመላለሱ” (ገላ. 5፥16)


ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ፣ “የሥጋ ምኞት በመንፈስ ላይ፣ መንፈስም በሥጋ ላይ ነውና፤ ልታደርጉ የምትወዱትን እንዳታደርጉ እነዚህ እርስ በርሳቸው ይቃረናሉ” ይላል። በዚህ በወደቀው ዓለም ውስጥ ስንመላለስ፣ ምንም እንኳ በክርስቶስ ኢየሱስ በደሙ ቤዝወት ከኩነኔና ከዘላለም ሞት ድነን፣ “በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ የታጠብን፣ የተቀደስን፣ የጸደቅን" (1ቆሮ. 6፥11) ብንኾንም፣ በውስጣችን ግን የእግዚአብሔር በኾነውና በኀጢአት መገኘት ምክንያት ታላቅ ጦርነት አለ። በአንድ ማንነት ውስጥ ያሉ፣ ርስ በርሳቸው ደግሞ የሚቀዋወሙ ባላንጣዎች! የሥጋ ምኞታችን በማናቸውም መንገድ ለእግዚአብሔር አይታዘዜና እንዳንገዛ ከልካይ ነው።

የሥጋ ምኞት ዘወትር በመንፈሳዊ ነገራችን ላይ መሰልጠን ይፈልጋል፤ ሳያቋርጥም ይመኛል። በዚህም የምንወደውን እንዳናደርግ ይከላከላል። ከሕግ በታችም ገዝቶ ሊይዘንም ይጥራል። ቅዱስ ጳውሎስ እኒህ የሥጋ ምኞቶች ወይም ሥራዎች በስፋት ዘርዝሮአቸዋል፤ በነዚህ የሥጋ ምኞቶች መመላለስ ከመንፈስ ወደ ኋላ ይስበናል፤ ለዚህም ሐዋርያው፣ “በመንፈስ ተመላለሱ” ይለናል። ሰው ከሥጋ ምኞት ጋር በመጋደል ከተመላለሰና የመንፈስን ነገር ዘወትር አጥብቀን ከያዝን መንፈሳዊ ፍሬዎችን እንደምናፈራ ይመክረናል።

በሌላ ንግግር ቅዱስ ጳውሎስ አብዝተን የምንመገበውን ያንኑ ፍሬ እንደምናፈራ ይነግረናል፤ በሥጋ ምኞት የሚመላለሱ፣ የሥጋ ሥራዎች ይበዛላቸዋል፤ በመንፈስ የሚመላለሱ ደግሞ የመንፈስ ፍሬዎችን በጽድቅ ያፈራሉ። የምንመገበው ያው ምግብ ሰውነታችንን ይገነባዋል፤ የምመላለስበት ያው ጎዳና ፍጻሜያችንን ይተልመዋል፤ ሰውነታችንን በምን እያጐለመስን፣ ደግሞ ምን መግበን እየገነባን ነው?

“የማይደክም” ባላጋራ፤ “የማይታክት” ባላንጣ፤ “ካልጣለ የማይለቅ” የክፋት አበጋዝ፤ የኀጢአት አባት “የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ‘በዙሪያችን’ የሚዞር” (1ጴጥ. 5፥8)፤ ከኋላችን የማይታጣ (ማቴ. 16፥23) በጐአችንን የማይሻ ጥንተ ጠላት አለብን። ርሱን መርታት የሚቻለን፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ስንመላለስ ብቻ ነው፤ ለዚህ ነው ሐዋርያው “በመንፈስ ተመላለሱ” የሚለን። በመሲሑ ደም፤ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነጻ ከወጣን ወዲያ፣ አርነታችንን ለሥጋ ዕድል መጠቀምም የለብንምና።

በመንፈስ ለመመላለስ ነጻነት ተሰጥቶናል፤ ነጻነታችንን እንዴት እየተጠቀምነው ነው? ታላቁን ጦርነት በድል የሚያጠናቅቁት በመንፈስ የሚመላለሱት ብቻ ናቸውና። ተዋግቶልንም፤ ድል ነሥቶልንም ከሚያኖረን ጋር የክብር ፍጻሜ እንዲኖረን ጸንቶ መቆም፤ በመንፈሱ መዓዛ ፍጹም መታዘዝና መመላለስ ይኹንልን፤ አሜን።

“ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወዱ ኹሉ ጸጋ ይኹን፤ አሜን” (ኤፌ. 6፥24)።

My telegram link - https://t.me/ebenezertek
My blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2026/04/516.html

23/04/2026

ተቃርኖ!

ኢየሱስ፦ "ነቢይ በገዛ አገሩ አይከብርም" ብሎአል። ስላልተከበረም ከከተማ ውጭ በውርደት ተሰቅሎ ምሳሌ ኾነን።

የኛ ዘመን "ነቢያት" ግን፦ ከኢየሱስ በተቃራኒ "በአገራችንና[በከተማችንና] በጊዜያችን እኛ ያልከበርን ማን ይከብራል?!" የሚሉ ይመስላል።

የቴሌግራም አድራሻ -

https://abenezerteklu.blogspot.com/2026/04/blog-post_20.html
21/04/2026

https://abenezerteklu.blogspot.com/2026/04/blog-post_20.html

  Please read in PDF “ያለ እውነት፥ የእውነት ቃል አገልግሎት!?” በሚል ርዕስ፣ ስለ “እውነት ቃል አገልግሎት” ማኅበር ከታሪካዊ ዳራቸው ጀምሮ፣ ትምህርቶቻቸውን የሚያስቃኘው መጽሐፌ ታትሞ .....

20/04/2026

ትልቁ የሰማይና የምድር ደስታ ክርስቶስን በመፈለግና በማግኘት ውስጥ ያለው ብቻ ነው!

በመካከላችን እናትም እህትም ኾና በጽድቅና በቅድስና፤ በተመሰከረለት የትዳር ሕይወት ያገለገለችኝ ናት፤ ጥሩዬ። ስናጣሽ ጎድለሽብን አዝነናል፤ ወደ ሚበልጠው ጌታ መሄድሽን ስናስብ ደግሞ እጅግ ...
19/04/2026

በመካከላችን እናትም እህትም ኾና በጽድቅና በቅድስና፤ በተመሰከረለት የትዳር ሕይወት ያገለገለችኝ ናት፤ ጥሩዬ። ስናጣሽ ጎድለሽብን አዝነናል፤ ወደ ሚበልጠው ጌታ መሄድሽን ስናስብ ደግሞ እጅግ በጣም ደስ ብሎናል። ለጥሩዬ ቤተሰብ ፍጹም መጽናናትን እንዲሰጥ እንመኛለን።

"ጻድቅ ይሞታል፤ ይህን ግን ማንም ልብ አይልም፤ ለእግዚአብሔር ያደሩ ሰዎች ይወሰዳሉ፤ ጻድቃን ከክፉ ይድኑ ዘንድ፣ መወሰዳቸውን፣ ማንም አያስተውልም። በቅንነት የሚሄዱ፣ ሰላም ይሆንላቸዋል፤ መኝታቸው ላይ ያርፋሉ።" (ኢሳ. 57፥1-2)

19/04/2026

ኢየሱስ ክርስቶስ
የእንደገና አምላክ!

18/04/2026

ለነተክለ ሃይማኖትና አርሴማ "ሲዘመር" እየኰሰኰሰው፣ ስለ ኢትዮጵያና ተፈጥሮ በዘፈን ሲመ'ለክ ደስ የሚለው እንዴት ሰመረለት?!

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Telephone

+251920893099

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abenezer Teklu Diyakon posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share