ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ - Orthodox tewahdo page

ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ - Orthodox tewahdo page የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ እና ቅኖና የጠበቁ ስብከቶች፣መዝሙሮች፣ወረቦች፣ስርዓተ ማህሌት በዚህ ገፅ ይተላለፋሉ

  ፩  ርዕሰ ዓውደ ዓመት ማለት የበዓላት ሁሉ የበላይ፣ ራስ ማለት ነው፡፡ በዓመቱ ውስጥ የሚውሉት በዓላትና አጽዋማት የሚወጡት መስከረም አንድን መነሻ አድርጎ ስለሆነ ርዕሰ አውደ ዓመት ተባ...
10/09/2025



ርዕሰ ዓውደ ዓመት ማለት የበዓላት ሁሉ የበላይ፣ ራስ ማለት ነው፡፡ በዓመቱ ውስጥ የሚውሉት በዓላትና አጽዋማት የሚወጡት መስከረም አንድን መነሻ አድርጎ ስለሆነ ርዕሰ አውደ ዓመት ተባለ።
ዓውደ ዓመት በግእዝ ሲሆን በአማርኛ የዘመን መለወጫ/ ቅዱስ ዮሐንስ፣ ዕንቁጣጣሽ እየተባለም ይጠራል፡፡
?
ዘመነ ማቴዎስም፣ ዘመነ ማርቆስም፣ ዘመነ ሉቃስም ሆነ ዘመነ ዮሐንስ በአራቱም ዘመናት አስቀድሞ ርእሰ ዓውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ ይዘከራል፡፡ ዮሐንስ የስሙ ትርጉም «ጸጋ እግዚአብሔር» ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ማርቆስ ወንጌሉን ሲጽፍ «የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ እነሆ መንገድህን የሚጠርግ መልእከተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጅ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ» ተብሎ በኢሳይያስ እንደ ተነገረ የነቢዩ ዘካርያስ ልጅ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዘመነ ብሉይ መጨረሻና በዘመነ ሐዲስ መጀመሪያ ላይ ተነሥቶ «መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ» እያለ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት እየመሰከረ በምድረ በዳ የንስሐን ጥምቀት እያጠመቀ ለኃጢአት ሥርየት እየሰበከ መጣ ብሎ በዘመነ ወንጌል የመጀመሪያ ምዕራፍ ገልጾታል፡፡ /ማር.1.40፤ኢሳ.40.3-4/፡፡
#የመጥምቁ ዮሐንስ ተግባር ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ ሆኖ መገኘቱን በመረዳት የቤተክርስቲያን አበው የበዓላቱን ድንጋጌ በወሰኑበት ጊዜ የመጥምቁ ዮሐንስ መታሰቢያ በዓል የኢትዮጵያ ርዕሰ ዓውደ ዓመት በሚሆን መስከረም አንድ ቀን እንዲከበር በየዓመቱ የዘመኑ መጀመሪያ በእርሱ ስም እንዲጠራ አባቶች ደንግገዋል፡፡ / ድርሳነ ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 1ጠ 3/
#ይህንን በአል መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በሰማዕትነት ያረፈበት ቀን ሆኖ ግን አይደለም፡፡

መስከረም ወር ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ዘመን መለወጫ እንደሆነ እንዲህ በማለት ያትታሉ፡፡ ሲያትቱም ብርሃናት/ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ያን ጊዜ ሌሊቱም ከቀኑ ጋር ይተካከላል፡፡ ዓመቱንም ጠንቀቀው ቢቆጥሩት 364 ቀናት ይሆናል፡፡ ለዘመን መታወቂያ ይሆን ዘንድ ፀሐይና ጨረቃ ከዋክብትን ፈጠረ ይላልና /ሔኖክ.21.49/፡፡ በሌላ በኩልም በዘመነ ኖኅ ዓለምን ውኃ አጥለቅልቋት ከቆየ በኋላ ዳግመኛ ከነበረው ውኃ የተገለጠችበት ወር «በመጀመሪያም ወር በምድር ታየች የንፍር ውኃው ከምድር ደረቀ» የሚለውን መሠረት አድረገው የአቡሻኽር ሊቃውንት የዘመን መለወጫን ታሪካዊ አመጣጥ ያስረዳሉ፡፡/ኩፋ.7.1/በመሠረቱ ዘመን ተለወጠ ሲባል የሚለወጡት ወራቱ ብቻ አይደሉም፡፡ በወቅቱ የሚከሰቱት/የተከሰቱት/ መልካምም ሆነ ክፉ ነገር /ገጠመኝ/ ሲሆን ወራቶቹ ግን ያው በየዓመቱ እየተፈራረቁ ይመጣሉ፡፡ ዘመን መለወጫ ላይ የሰው ልጆች ሕይወት ሊለወጥ ይገባል፡፡ ተማሪው ተምሮ ወደቀጣዩ ክፍል /ደረጃ/ የሚለወጥበት፣ ገበሬው የክረምቱን ወራት በሚገባ ተጠቅሞ የሚቀጥለውን የበጋ ወራት የሚቀበልበት፣ ሠራተኛው የክረምቱን ዝናብ ታግሶ የፀሐይን ወራት የሚቀበልበት ሌላውም እንደዚያ ሆነው ወራቶቹ በዚያ ዘመን ያለው የተፈጥሮ ክስተቶች የሚለወጥበት ዘመን ተለወጠ እየተባለ ይነገራል፡፡
#እንቁጣጣሽ
ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንደሚያስረዱት እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜው አመጣጥ ወይመ ጥንተ ታሪክ
#በመጀመሪያ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ አህጉራትን በዕጣ ሲያካፍላቸው አፍሪካ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪካ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ

እ  በዓለ  ጽንሰት በሰላም አደረሳቹ::አቡነ ሀብተማርያም ፠፠በማዕጠንታቸው የታወቁ፤፠፠በጽድቅ ሥራቸው የተደነቁ፤፠፠5ት መቅሰፍቶችን የሚያርቁ ታለቅ አባታችን ናቸው፡፡፡፨፠ታላቁ ጻድቅ አባታች...
01/09/2025

እ በዓለ ጽንሰት በሰላም አደረሳቹ::

አቡነ ሀብተማርያም

፠፠በማዕጠንታቸው የታወቁ፤
፠፠በጽድቅ ሥራቸው የተደነቁ፤
፠፠5ት መቅሰፍቶችን የሚያርቁ ታለቅ አባታችን ናቸው፡፡፡፨

፠ታላቁ ጻድቅ አባታችን የተወለዱት በመንዝ አውራጃ ልዩ ስሙ የራዊ በተባለ ቦታ ሲሆን የአባታቸው ስም ፍሬ ብሩክ የእናታቸው ስም ዮስቴና ይባላል፡፡ ሁለቱም በሕግ ጋብቻ ጸንተው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው ምግባር ቱሩፋት ሰርተው በንጽህና በቅድስና ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ልጅ አለነበራቸውም፡፡ በዚህ ሁኔታ ያዘኑ ቅድስት ዮስቴና ማለት እናታቸው መንነው በአከባቢያቸው ከሚገኝ ጫካ ውስጥ ዋሻ ፈልገው ገብተው ዘጉ፡፡ በዚያም አንድ መናኝ መነኩሴ አግኝተዋቸው እግዚአብሔር በቅድስቲቱ ያለው ድብቅ ነገር ስለገለጠላቸው አንቺ ለምንኩስና የተፈቀደልሽ አይደለሽም ወደ ቤትሽ ግቢ ጸሎቱ ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ሰው ሁሉ የሚማጸነው ስሙ፣ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የሚነገርለት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ አሏቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተዓምር የሰሙ ቅድስት ዮስቴናም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤቸው ተመለሱ፡፡

የተናገረውን የማያስቀር አምላክ በቸርነቱ ጎበኛቸውና ነሐሴ 26 ቀን ጸነሱ፡፡ ግንቦት 26 ቀንም ደም ግባታቸው እንደ ንጋት ኮከብ ያማሩ ሃብተማርያም ተወለዱ፡፡ እናታቸውም ጻድቁን ወልዳ በጽድቅ ኑሮ ኑራ ተቀብላ በክብር አርፋለች፡፡

፠አቡነ ሀብተማርያም በሕፃንነታቸው ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ ‹‹እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ›› ሲባል ይሰማሉ፤ በሕፃን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ ‹‹ማረን እባክህን›› እያሉ ይሰግዱ ነበር፡፡ ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ፡፡ ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል፤ ጓደኞቻቸው የሌላ ሰው እሸት እየነቀሉ ሲበሉ እርሳቸው ግን አይበሉም ነበር፡፡ የፈጣሪውን ስም ያቃለለውን አንድ እረኛም በአየር ላይ ሰቅለው አውለውታል፡፡

፠ወደ ት/ቤት ገብተው ትምህርትን ከቀሰሙ በኋላ ለአካለ መጠን ሲደርሱ ቤተ ሰቦቻቸው ሚስት አጩለት፤ እርሱ ግን ወደ አፋር ከአባ ሳሙኤል ዘንድ ሂዶ ለ12 ዓመታት ረድዕ ሆኖ ተቀመጠ፡፡ ከአፋርም ወደ ምኔት ወደሚባል ቦታ መጥቶ በታላቁ አባት በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሰ፤ ከአፋር ወደ ይነውፋ፥ ከይነውፋ ወደ ጉሐርብ ወደሚባል ሃገር ሂዶ ምናኔን፣ ትሩፋትንና ተጋድሎን ሠራ፡፡
ለአብነትም፤
ባሕር ውስጥ ሰጥሞ 500 ጊዜ ይሰግዳል፤
በየቀኑ 4ቱን ወንጌልንና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያል፤
በ40 ቀናት ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባል፤
ምግቡ ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው፤
በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋል፤
ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላል፥ ክቡር ደሙን ይጠጣል፤
በልቡ ውስጥ በፍጹም ቂምን፣ መከፋትን አያሳድርም፡፡
የብረት ሰንሰለት በወገቡ ታጥቆ ይሰግዳል ይጸልያልም፡፡
"ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሀብተ ማርያም" የተባለላቸው ታላቅ አባታችን ናቸው ፡፡

፠ዲቁናን ከጳጳሱ አቡነ ይስሐቅ ዘንድ ተቀበሎ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡
፠ኋላ ቆይቶም እንደገና ከአቡነ ይስሐቅ ዘንድ ቅስናን ተቀበለ፡፡ ወደ ጓና ወደ ምትባል ሀገርም ሂዶ ተቀመጠ፡፡ ቀጥሎም ጐላጐት ወደ ምትባል አገር ሂዶ ተቀመጠ፡፡
*የአፄ ናዖድ የንስሐ አባት ነበረና ንጉሡን ያስተምረውና ይገስጸውም ነበር፡፡
፠ጌታችንም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቶት በዚያ እየበረረ ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ተለያዩ ቦታዎች ይሔድ ነበር፡፡ ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በኋላም የክብር ባለቤት መድኀኒታችን ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ እንዲህ አላቸው::

"*ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ: *ስለ ምናኔሕ: *ስለ ተባረከ ምንኩስናህ: *ስለ ንጹሕ ድንግልናህ: *ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ: *ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ: *ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"

"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን: 500 የዕንቊ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ: በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ በርእስየ' ብዬሃለሁ" አላቸው::

+ቅዱሳን መላእክትም "ሀብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: መላእክትም ዝማሬም ወሰዷት::

 ከተሰጣቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ አምስት መቅሰፍቶች የማስወገድ ሥልጣን ተሰጧቸዋል፡፡ እነርሱም፤
፩ኛ. #መብረቅ፣
፪ኛ. #ቸነፈር፣
፫ኛ. #ረሃብ፣
፬ኛ. #ወረርሽኝ፣
፭ኛ. #የእሳት ቃጠሎ ናቸው፡፡

፨በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ቦታውን ሲባርክ ሦስት አጋንንት በጸሎቱ ሥልጣን የታሠሩለት ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡
በግንቦት 26 ተወልዶ፤ በ1490 ዓ.ም. በወርኀ ኅዳር 26 ባረፈ ጊዜም፤ ካህናት በመልካም ልብስ ገንዘው በዝማሬ በማኅሌት ከቅዱስ አባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት አጽም ጋር በደብረ ሊባኖስ ቀበሩት፡፡
(ከወርቅ ንፁህ ከብርም የጠራ ከሁሉ የሚበልጥ የተመረጠ ሀብተማርያም መልአክ ዘበምድር ነው መልካሙ ዜናው እስከ አጽናፍ ተሰማ፡፡)

✞✞✞✞✞
#አቡነ #ተክለሃይማኖት አና #አቡነ #ሀብተማርያም


#ያን ጊዜ ክቡር የሆነ ጠርቶኝ ልጄ ሆይ ፈጣሪየ እግዚአብሔር ስለ ወደደህ ብዙ ምህርኮ እንደአገኝህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል አለኝ ፤
#ነገር ግን የሞለምንክ አንድ ነገር አለና እሽ በለኝ ቢለኝ አቤቱ ጌታዩ ምንድን ነው ነገሩ አልሁት ፣
#ክቡር አባታችን አባ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀብር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለኝ፤
ይንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትለምነኛለህ ብየ ብመልስለት፣ እነሆ በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስ መቅሰፍቶች አሉና ስለዚህ ነው ፤ እሊሁም አንዱ መብረቅ ነው ፣ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ፤ ሦስተኛው የረኃብ ጦር ነው ፣ አራተኛ ወረርሽኝ ነው ፡፡ አምስተኛ የእሳት ቃጠሎ ነው ፤ የአንተ አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደ ሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገር ከእንዚህ መቅስፍታት ትድናለች፣
#……ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሄር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው አለኝ ፣ ይልቁንስ እንዳልኩክ በተቀበርኩበት ቦታ እንተቀበርልኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ መላልሶ ማለደኝ.
ገድለ አቡነ ሃብተ ማርያም

በቃል ኪዳናቸው ሀገራችንን ከአምስቱ መቅሰፍታት ይጠብቁልን አሜን !

  ​​​​​​እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓልና የጾመ ፍልሰታ ፍቺ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ!  እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር የ...
22/08/2025




​​​​​​እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓልና የጾመ ፍልሰታ ፍቺ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ!



እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር የኖረችው ስልሳ አራት ዓመት ነው፡፡ እነዚህ ዓመታት ሲተነተኑ ሦስት ዓመት በወላጆቿ ሐናና ኢያቄም ቤት፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት በቤተ መቅደስ፣ ሠላሣ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር አሥራ አምስት ዓመት ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር ነው፡፡

ያረፈችውም ጥር 21 ቀን በ50 ዓ.ም ነው፡፡ ባረፈችበት ወቅት ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡር ሥጋዋን ለማሳረፍ ወደ ጌቴ ሴማኒ ሲሔዱ አይሁድ "ቀድሞ ልጇ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፤ በአርባኛውም ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ፤ ተመልሶም ይህን ዓለምን ለማሳለፍ ይመጣል እያሉ በማስተማር ሕዝባችንን ወስደውብናል፡፡ አሁን ደግሞ ዝም ብለን ብንተዋት እርሷም እንደ ልጇ ተነሳች እያሉ በማስተማር ሊያውኩን አይደለምን? ኑ! ተሰብስበን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ክፉ ምክር ተማከሩ፡፡

ከመካከላቸውም ብርቱ ሰው የሆነው #ታውፋንያ የተባለ ቅድስት ሥጋዋን ከሐዋርያት ነጥቆ ለማስቀረት ክቡር ሥጋዋ ያለበትን የአልጋ ሸንኮር ሲይዝ በመልአከ እግዚአብሔር እጁ ተቆርጣ ከአልጋው ላይ ተንጠልጥላ ቀረች፤ ከዚህ የጥፋቱ ሥራው ተምሮ እመቤታችንን በመለመኑ እመቤታችን የተቆረጠች እጁን መልሳለታለች፡፡

ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የተቀደሰ ሥጋዋን ጌታችን ይወደው የነበረ ተብሎ የተነገረለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ይዞ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም የሆነውን ሁሉ ለወንድሞቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ነገራቸው፡፡ እነሱም የእመቤታችን ሥጋ በክብር ለማሳረፍ ካላቸው ጉጉት የተነሣ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምሮ ሱባኤ ገቡ፡፡

ከሁለተኛ ሱባኤ ቆይታቸው በኋላ በአሥራ አራተኛ ቀናቸው ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ ሥጋ ሰጣቸው፡፡ ሐዋርያትም በዝማሬና በታላቅ ምስጋና በጌቴ ሴማኔ ቀበሯት፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት› › ተብሎ ትንቢት የተናገረውን ሲተረጉሙት ‹‹ፈጣሪያችን እግዚአብሔር ሆይ፥ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታሳርፈው የመቅደስህ ታቦት የሆነችውን ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ›› ብለው ያመሰጥሩታል፡፡ /መዝ. 131፥8/፡፡

የእመቤታችንን ቅድስት ሥጋዋን ሐዋርያት ሲቀብሯት በሀገረ ስብከቱ ሕንድ የነበረው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ ሲመለስ እመቤታችን ስታርግ ያገኛታል ለምልክት እንዲሆነው ሰበኗን (የመግነዟን ጨርቅ) ተቀብሏት ይለያያሉ፡፡ ለወንድሞቹ ሐዋርያት ያየውን ይነግራቸዋል፡፡

ለበረከት የሰጠችውንም ሰበን ያካፍላቸዋል፤ ሐዋርያት ‹ ‹ዕርገቷን እንዴት እሱ ብቻ ተመልክቶ ለምን እኛ ይቀርብናል› › ብለው በዓመቱ ነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ገቡ፡፡ ነሐሴ 16 ቀን የልባቸው መሻት ተፈጸመላቸው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን መንበር፣ ቅዱስ ጴጥሮስን ንፍቀ (ረዳት) ቄስ፣ ቀዳሚ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ገባሬ ሰናይ (ዋና ዲያቆን) አድርጎ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡

በትኅትና የያዙት ሱባኤም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገቷን ለማየት አበቃቸው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን መሠረት አድርጋ ከነሐሴ 1-16 በማለት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ አድርገን እንድንጠቀምበት ሥርዐት ሠራችልን፡፡

በነቢያና በሐዋርያት መሠረት ላይ የታነጽን ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆ

ሐምሌ 26በዚህች ቀን የእመቤታችን ጠባቂ፤ የስደት የመከራዋ ተካፋይ የነበረው ጻድቁ ዮሴፍ አረጋዊ አረፈ፤ ይህ ጻድቅ በመዲናችን አዲስ አበባ በስሙ በታነጸለት ቤተክርስቲያን በደማቁ ተከብሮ ይ...
02/08/2025

ሐምሌ 26
በዚህች ቀን የእመቤታችን ጠባቂ፤ የስደት የመከራዋ ተካፋይ የነበረው ጻድቁ ዮሴፍ አረጋዊ አረፈ፤

ይህ ጻድቅ በመዲናችን አዲስ አበባ በስሙ በታነጸለት ቤተክርስቲያን በደማቁ ተከብሮ ይውላል

፤ አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ትዉልዱ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 1፡15-16 ላይ እንደተገለጸዉ ፡- አዛርያ ማትያንና ቅስራን ይወልዳል፡፡ ማታንም ያዕቆብን ወለደ ፡፡ ያዕቆብ ክርስቶስ የተባለዉን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ፡፡ ቅስራ ደግሞ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያም አባተ እያቄምን ወለደ፡፡ እያቄም ድንግል ማርያምን ወለደ፡፡ በዚህ ትዉልድ ሐረግ መሰረት እመቤታችን ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ በሦስት ቤት ዘመዳማቾች ናቸዉ ፡፡ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌሉን ሲጽፍ በእመቤታችን ትዉልድ ያልቆጠረበት ምክንያት በአይሁድ ህግ ሴት ልጅ በዘር ሐረግ ስለማትቆጠር እመቤታችን እንዳትቀርበት ፈልጎ በእጮኛዋ በዮሴፍ በኩል ቆጥሯታል፡፡

ቅዱስ ዮሴፍ ለእመቤታችን የታጨበት ምክንያት

1-ኃይል አርያማዊት እንዳትባል (በመንፈስ ቅዱስ ስለጸለሰች )ኢሳ ፡1፡10
2-ፅንሱን ከአጋንት ለመሰወር (አጋንት ቢያዉቁ ብዙ ፅንስ ባበላሹ ነበርና)
3-ከርስት ገብቶ ሊቆጠርላት (በአይሁድ ህግ ዘር የሚቆጠረዉ በወንድ ነዉና) ማቴ 1፡16 ፣ ሉቃ 2፤4
4-በስደቷ ግዜ ሊላላካት ሊጠብቃት
5-ከዉግረት ሊያድናት (ባል የሌላት ሴት በኦሪት ህግ ፀንሳ ከተገኘች ትወገር ነበርና ዮሴፍ ባይኖር በድንጋይ ወግረን እንግደላት ይሉ ነበርና፡) በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር ባወቀ ቅዱስ ዮሴፍ ታጨላት፡፡ ዘሁ 5፡19

በማቴዎስ ወንጌል 1፡18-20‹‹ እመቤታችን ለዮሴፍ በታጨች ግዜ ሳይገናኙ በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች፡፡እጮኛዋ ዮሴፍ ጻድቆ ሆኖ ሊገልጣት ስላልወደደ በስዉር ሊተዋት አሰበ››፡፡ ቅዱስ ዮሴፍ ጻድቅ ስለነበር ከማን ፀነስሽ ብሎ ቢጠይቃት በመንፈስ ቅዱስ ብላዋለች ፡፡መልአኩም በህልም ቢነግረዉ ቢረቅበት ግር ቢለዉ ነብያት ትንቢት የተናግሩለት ጌታ እንደ ፀነሰች፣ድንግልም የተባለች እሷእንደሆነች ስላላወቀ ሐዋርያዉ ሲጽፍ ‹‹የበኩር ልጅዋን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም አለ›› ማቴ 1፡25 ፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ‹‹‹ እስከ ›››የሚለዉ ቃል መጨረሻ የሌለዉ እስከ ነዉ ፡፡ዘፍ 8፡7 ‹‹ቁራ ዉኃዉ እስኪድርቅ ድረስ….››ከደረቀም በኃላ አልተመለሰም ፡፡ 1ኛ ሳሙ 6፡23 ‹‹ሜልኮም እስከሞተችበት ቀን ድረስ ልጅ አልወለደችም ››ይላል ከሞተች በኃላ ልጅ ወለደች ማለቱ እንዳልሆነ ሁሉ ቃሉ የሚያስረዳዉ መጨረሻ የሌለዉ እስከ ነዉ፡፡ቅዱስ ዮሴፍ በኃላ ግን በቤተልሔም አምስት ነገር አይቶ አምኗል ትንቢቱም እንደተፈጸመ አዉቋል፡፡ እምስቱ ነገርም

1- የእግዚአብሔር ክብሩን ብርሃኑን በቤተልሔም አይቶ ፣

2-ኮከብ ከምስራቅ ወጥቶ ወደ መስብ በመሄዱ ፣

3-የሰብአ ሰገል በክብር በስጦታ ከሩቅ ሀገር መጥተዉ ሲገብሩለተት በማየቱ ፣

4- የእረኞች መፍራት መደንገጥ ሲመለከት ፣

5-ቅዳሴ መላእክት ምስጋና ስብሐተ እግዚአብሔር ሰዉና መላእክት በአንድላይ ሲዘምሩ በማየቱ ቅዱስ ዮሴፍ እመቤታችንን የአምላክ እናት እንደሆነች አወቀ፡፡ ፡፡ይቆየነ የቅዱስ ዮሴፍ በረከቱ ረድኤቱ ይደርበን አሜን፡፡

 #ሐምሌ 15 ስንክሳር - ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ +++ስንክሳሩ እንደሚለው ቅዱስ ኤፍሬም ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች ሀገር ነው፣ አባቱም የጣዖት ካህን ነበር፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም የተወለደው በ3...
22/07/2025

#ሐምሌ 15 ስንክሳር - ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
+++
ስንክሳሩ እንደሚለው ቅዱስ ኤፍሬም ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች ሀገር ነው፣ አባቱም የጣዖት ካህን ነበር፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም የተወለደው በ306 ዓ.ም ገደማ “በሜሶፖታሚያ” ውስጥ በምትገኝ “ንጽቢን” በተባለች ቦታ ነው፡፡ (ንጽቢን በደቡባዊ ቱርክ እና በምዕራባዊ ሶርያ መካከል የምትገኝ ቦታ ናት፡፡) ይህቺም ቦታ ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ የነበረው የቅዱስ ያዕቆብ ሀገረ ሰብከቱ የነበረች ናት፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ተወልዶ ባደገባት ሀገረ ንጽቢን ዽዽስናን የተሾመ ቅዱስ ያዕቆብ የሚባል ታላቅ ሰው ነበር፡፡ እርሱም የሰማዕትነት፣ የሐዋርያነት፣ የጻድቅነትና የሊቅነት ግብር ያለው አባት ነው፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ይሄ አባት ሁልጊዜ ሲያስተምር ይሰማው ነበርና በስብከቱ ተማረከ፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ አመላክቶት ወደ ቅዱስ ያዕቆብ ሄዶ ትምህርተ ክርስትናን ተምሮ የተጠመቀ ሲሆን ከወላጆቹ ጋር የኖረው እስከ አሥር ዓመቱ ብቻ ነው፡፡ በትምህርተ ክርስትና አምኖ ከተጠመቀ በኋላ ግን በቅዱስ ያዕቆብ ዘንድ በብሕትውና ተወስኖ በመማርና በማስተማር ኖረ፡፡ ከዚህም በኋላ በጾም በጸሎት እየተጋደለ ሲኖር የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት፡፡ አሕዛብንም ተከራክሮና አስተምሮ ይረታቸው ጀመር፡፡
በ325 ዓ.ም 318ቱ ኤጲስቆጶሳት ቢሆንላቸው አርዮስን አስተምረው መክረው ከክህደቱ ለመመለስ እሺ ባይላቸው ግን አውግዘውት ለመመለስ በኒቅያ ሲሰበሰቡ ቅዱስ ኤፍሬም ከአባ ያዕቆብ ጋር አብሮ በጉባኤው ተገኝቶ ነበር፡፡ አርዮስንም አውግዘው ከለዩት በኋላ ቅዱስ ኤፍሬም በዚያች ሌሊት ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ አየ፡፡ የዚህንም ራእይ ምሥጢር ይረዳ ዘንድ ወደ ጌታችን ጸለየ፡፡ ‹‹ይህ የቂሣው ሊቀ ጳጳሳት ብፁዕ ባስልዮስ ነው›› የሚል ቃል ከሰማይ ወደእርሱ መጣ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ያየው ዘንድ ወዶ ቂሣርያ ሀገር ተጓዘ፡፡ በደረሰም ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ ቅዱስ ባሰልዮስን ከወርቅ የተሠራ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ ወንጌልን ሲያነብ አየው፡፡ ሦስት ምልክቶችንም እስኪያይ ድረስ በልቡ ተጠራጠረ፡፡ ይኸውም በመጀመሪያ ነጭ ርግብ መጥታ በቅዱስ ባስልዮስ ላይ አረፈች፡፡ ቀጥሎም በልብሱ ላይ የሚያርፉ ተሕዋሲያን ይቃጠሉና ይረግፉ ነበር፡፡ ሦስተኛም ከአፉ የእሳት ነበልባል እየወጣ ምእመናን ላይ ሲያርፍ ተመለከተ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ቅዱስ ኤፍሬምን በስሙ ጠርቶት ሰላምታ ተሰጣጡና በአስተርጓሚ መነጋገር ጀመሩ፡፡ ምሥጢር በአስተርጓሚ አይሆንም የአንዳቸው ቋንቋ ለአንዳቸው ይገለጥላቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ቢጸልዩ የአንዳቸው ቋንቋ ለአንዳቸው ተገልጦላቸው ሁለቱም ነገረ እግዚአብሔርን ሲነጋገሩ አደሩ፡፡
ከዚህም በኋላ አባ ባስልዮስ ቅዱስ ኤፍሬምን ዲቁና ሾመው፡፡ ከጥቂት ወራትም በኋላ ቅስና ሾመው፡፡ ከዚህም በኋላ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ አበራ፡፡ አንዲት በወገን የከበረች ባለጸጋ ሴት ነበረች፡፡ እርሷም ራሷን ለካህን ለማስመርመር ታፍር ነበር፡፡ ከታናሽነቷ ጀምራ የሠራችውን ኃጢአቷን ሁሉ በዝርዝር ጽፋ በክርስታስ አሽጋ እንዲጸልይላትና ኃጢአቷን ይደመስስላት ዘንድ ቅዱስ ባስልዮስን ለመነችው፡፡ እርሱም ‹‹ይሁን እንዳልሽው ይሁንልሽ›› ብሎ ጸልዮላት ከአንዲት ኃጢአቷ በቀር ሁሉንም በጸሎቱ ደመሰሰላት፡፡ እርሷም ክርታሱን በገለጠችው ጊዜ ከአንዲቷ ኃጢአት በቀር ሌሎቹ ሁሉም ተደምስሰው ጠፍተው አገኘች፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ስለ አንዲቱም ኃጢአቷ ወደ ቅዱስ ኤፍሬም እንዲትሄድ አዘዛት፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ‹‹ፈጥነሽ ወደ ቅዱስ ባስልዮስ ሂጂ ነገር ግን ሞቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱት ታገኚዋለሽ ሳትጠራጠሪም ይህችን ክርታስ በላዩ ጣይ ይደመስስልሻል›› ብሎ መልሶ ላካት፡፡ በተመለሰችም ጊዜ ቅዱስ ባስልዮስ ዐርፎ ሊቀብሩት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲወስዱት አገኘችው፡፡ እርሷም መሪር ልቅሶን ካለቀሰች በኋላ ቅዱስ ኤፍሬም እንዳዘዛት በእምነት ሆና ያንን ክርስታስ በቅዱስ ባስልዮስ አስክሬን ላይ ጣለችው፡፡ ወዲያውኑም ያች የቀረች ኃጢአቷ ተደመሰሰችላት፡፡ ክርታሱም ምንም ጽሕፈት የሌለበት ባዶ ሆነ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ሌሎች እጅግ ብዙ ተአምራትን አድርጓል፣ መናፍቃንን ተከራክሮ እረቷል፡፡
ቅዱስ ኤፍሬም ከታላቁ ባስልዮስ ከተማረ በሁዋላ ሃገረ ስብከት ተሰጥቶት ያስተምር ጀመረ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ክርስትናን በሚገባ ሲመረምር የእመቤታችን ፍቅር ይበዛለት ጀመር፡፡ እንደ ዛሬው የእመቤታችን ምስጋና በአንደበት እንጂ በመጽሐፍ አይገኝም ነበርና ቅዱስ ኤፍሬም ግን ከወንጌለ ከሉቃስ ወንጌል በስድስተኛው ወርን (ይዌድስዋን) እና ጸሎተ ማርያምን አውጥቶ በየዕለቱ በዕድሜዋ ልክ 64 ጊዜ ያመሰግናት ነበር፡፡ እመቤታችንን ከልብ ከመውደዱ የተነሳ ‹‹የእመቤታችን ምስጋናዋ እንደ ሰማይ ኮከብ እንደ ባህር ሸዋ በዝቶልኝ እንደ ልብስ ለብሼው እንደ ምግብ ተመግቤው እንደ ውኃ ጠጥቼው ረክቸው›› እያለ ሲመኝ ይኖር ነበር፡፡ የሻቱትን መስጠት ለመንፈስ ቅዱስ ልማዱ ነውና ቅዱስ ኤፍሬም የፈለገውን ገልጦለታል፡፡ አምላክን የወለደች እመ ብርሃንም በገሃድ ተገልጣለት የልቡን ፈቃድ ፈጸመችለት፡፡ ዛሬ እየጸለይነው ጸጋ በረከት የምናገኝበትን ውዳሴ ማርያምን ደረሰላት፡፡ ውዳሴዋን ሲደርስላትም እርሷ አእላፍ ቅዱሳን መላእክትን ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላ ወርዳ በፊቱ ትቀመጣለች፤ እርሱም ባጭር ታጥቆ በፊቷ ቆሞ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ነው፡፡ ዕለቱ ሰኑይ ነግህ ነው እንዲህም ሆነ፡- የነግህ ተግባሩን አድርሶ ከመካነ ግብሩ ተቀምጦ ሳለ እመቤታችን ትመጣለች፡፡ የብርሃን ምንጻፍ ይነጠፋል፣ የብርሃን ድባብ ይዘረጋል፣ ከዚያ ላይ ሁና ‹‹ሰላም ለከ ኦ ፍቁርየ ወፍቁረ ወልድየ ኤፍሬም›› ትለዋለች፡፡ እርሱም ታጥቆ እጅ ነሥቶ ይቆማል፡፡ ‹‹ወድሰኒ›› ትለዋለች›› እርሱም ‹‹ሰማያውያን መላእክት ምድራውያን ጻድቃን ሰማዕታት አንቺን ማመስገን የማይቻላቸው ለእኔ እንደምን ይቻለኛል?›› አላት፡፡ እመቤታችንም ‹‹መንፈስ ቅዱስ እንዳቀበለህ ተናገር›› አለችው፡፡ ‹‹ባርክኒ›› ይላታል፡፡ እርሷም ‹‹በረከተ ወልድየ ወአቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ ይኅድር በላዕሌክ›› ትለዋለች፡፡ ጥዑመ ልሳን ቅዱስ ኤፍሬምም ተባርኮ መንፈስ ቅዱስ እንዳጸናው ቀለም ሰተት አድርጐ አመስግኗል፤ ስታስደርሰውም በሰባት ከፍላ አስደርሳዋለች፡፡ ምስጋናዋም የሰባቱ ዕለታት ውዳሴ ማርያም ነው፡፡ የእመቤታችንን ውዳሴዋን በ7 ቀናት ከደረሰላት በኋላ በብርሃን መስቀል ባርካው ምሥጢር ገልጣለት ዐረገች፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ከዚህ በኋላ ‹‹አቤቱ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ›› እስከሚል ድረስ ከእመቤታችን ውዳሴ ሌላ 14 ሺህ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደርሷል፡፡ ብዙውን ድርሰቱን መላእክት ደብቀውታል፣ ወስደውም ለምስጋና ተጠቅመውበታል፡፡ መልካም የሆነ ገድሉንም በፈጸመ ጊዜ ጌታችን እመቤታችንንና ቅዱሳንን ሰማዕታትን ሁሉ አስከትሎ ተገልጦለት ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ቅድስት ነፍሱን በክብር ተቀብሏታል፡፡

ቅዱስ ኤፍሬም የደረሳቸውን የእነዚህንም የሰባቱን ዕለታት የውዳሴ ማርያም ዜማቸውን ቅዱስ ያሬድ ደርሶታል፡፡ አክሱም ጽዮን እየተሳለማት ሳለ የብርሃን እናት እመቤታችን ተገልጣለት ቅዱስ ኤፍሬምንና ቅዱስ አባ ሕርያቆስን በአካለ ነፍስ አምጥታ ድርሰታቸውንና ቅዳሴያቸውን ያሰሙታል፡፡ ቅዱስ ያሬድም በመልክ በመልኩ እያደረገ ዜማውን ደረሰው፡፡ ቅዱስ ያሬድም ዜማውን ሲጨርስ የብርሃን እናቱ እመ አምላክ በያዘችው የብርሃን ባርካው ተስፋውን ነግራው ዐርጋለች፡፡ ለቅዱስ ኤፍሬም የተለመነች የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ ለእኛም ትለመነን!

 #ሚካኤል
19/07/2025

#ሚካኤል

በሕይወት ውስጥ ሁልጊዜ ደስተኛ ለመሆን የሚረዱ መንገዶችበሕይወት ውስጥ ሁልጊዜ ደስተኛ ለመሆን እንዴት እንደሚቻል የሚያሳይ መመሪያ እነሆ።ችግሮችን ተቀበል: ችግር የሌለበት ሰው የለም፤ በዚህ...
15/06/2025

በሕይወት ውስጥ ሁልጊዜ ደስተኛ ለመሆን የሚረዱ መንገዶች

በሕይወት ውስጥ ሁልጊዜ ደስተኛ ለመሆን እንዴት እንደሚቻል የሚያሳይ መመሪያ እነሆ።

ችግሮችን ተቀበል: ችግር የሌለበት ሰው የለም፤ በዚህም አንተ የተለየህ አይደለህም። ሁሉም ሰው ከባድ ጊዜያትን ያሳልፋል። በሕይወት እስካለህ ድረስ ፈተናዎች እና ውጣ ውረዶች መኖራቸው አይቀርም።

መፍትሄን ፈልግ: እያንዳንዱ ችግር መፍትሄ አለው። የተሻለ ስሜት እንዲሰማህ የሚያደርጉ መንገዶችም ሁልጊዜ አሉ። ተስፋ የሚቆረጥበት ምክንያት የለም፤ መውጫ መንገድ ሁሌም ይኖራል።

ለራስህ ጥሩ አመለካከት ይኑርህ: ስለራስህ የምታስበው ነገር በደስታህ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ አለው። ልዩ እና ጠቃሚ እንደሆንክ እመን። አሉታዊ ሀሳቦች እንዲቆጣጠሩህ አትፍቀድላቸው።

የሰዎችን አስተያየት ችላ በል: ሌሎች በሚሉት ነገር አትጨነቅ። አንዳንድ ሰዎች አንተን ለመጉዳት አስበው መጥፎ ነገር ሊናገሩ ይችላሉ። የሰዎችን ሀሜትና አሉታዊ አስተያየት ችላ ማለት ተማር።

አዎንታዊ ሰዎችን ምረጥ: ደስተኛ ከሚያደርጉህና አዎንታዊ አመለካከት ካላቸው ሰዎች ጋር ጊዜህን አሳልፍ። በአንተ ወይም በውጣ ውረዶችህ ላይ ከሚሳለቁ ወይም ከሚያሳዝኑህ ሰዎች ራቅ።

ትርፍ ጊዜህን ተጠቀም: የትርፍ ጊዜህን እንደ ስፖርት፣ ጨዋታዎች፣ ፊልም መመልከት ወይም ኢንተርኔት ማሰስ ለመሳሰሉ የሚያዝናኑህና አእምሮህን የሚያድሱ ነገሮች ተጠቀምበት።

የቁሳቁስ ነገርን አትፍራ: ገንዘብ ወይም የቅንጦት ዕቃዎች እንዲያስፈራሩህ አትፍቀድ። የቁሳቁስ ነገር የሕይወት መለኪያ አይደለም፤ የዛሬ ሁኔታ ነገ ላይቀጥል ይችላል ምክንያቱም ለውጥ ሁልጊዜ የሚከሰት ነገር ነው።

ተስፋ አትቁረጥ: ሁኔታዎች የቱንም ያህል ቢከብዱ ተስፋ አትቁረጥ። በሕይወት እስካለህ ድረስ ተስፋ አለ፤ እስትንፋስ እስካለ ድረስ መፍትሔና የተሻለ ቀን አለ።

ጸልይ: አዘውትረህ ጸልይ። ከፈጣሪ ጋር ያለህ ግንኙነት ውስጣዊ ሰላምና በረከትን ሊያመጣልህ ይችላል፤ እንዲሁም መልካም ነገሮች በፍጥነት ወደ አንተ እንዲመጡ ሊያግዝ ይችላል።

ደፋር ሁን እና ራስህን ሁን: ደፋር ሁንና የምትፈልገውን ነገር ተከተል። ሕይወት አደጋዎችን መጋፈጥን ይጠይቃል። እድሎችን ካልሞከርክ ወይም አደጋዎችን ካልወሰድክ የምትፈልገውን ነገር ላታገኝ ትችላለህ። ለራስህ ታማኝ ሁን፤ አንተ የምታደርገውን ነገር ከአንተ በተሻለ ማንም ሊያደርገው አይችልም። አንተ ግሩም ነህ! ስለዚህ ሁሌም ራስህን ሁን። መልካም ሕይወት ይኑርህ!

18/04/2025

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ - Orthodox tewahdo page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share