አሜን - Amen

አሜን - Amen የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን መልቲሚዲያ አገልግሎት

ሰላም ቅዱሳን! የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በየስፍራው ለምትጠሩ ሁሉ ቅዱሳን ሁሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን! የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮ ቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል "አልወ...
20/12/2024

ሰላም ቅዱሳን!

የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በየስፍራው ለምትጠሩ ሁሉ ቅዱሳን ሁሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን!

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮ ቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል "አልወርድም!" የተሰኘውን በዘማሪ አበበ ተስፋዬ የተዘጋጀውን ቁጥር-፩ የዝማሬ አልበም ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው።

ዝማሬዎቹን ለማውረድ የምትጠቀሙበትን ኮድ በቴሌግራም ቦት ላይ ማግኘት እንደምትችሉ እንገልፃለን።

🖍 የወንድማማችነት ፍቅር  ክፍል አንድ[1]                         🖍 By አሜን - Amen🖍እግዚአብሔር እያንዳንዱ ነገር በአሠራሩ ስሠራ ለአሁኑ እና ለምመጣውም ጭምር ነው, ...
13/12/2024

🖍 የወንድማማችነት ፍቅር ክፍል አንድ[1]
🖍 By አሜን - Amen
🖍እግዚአብሔር እያንዳንዱ ነገር በአሠራሩ ስሠራ ለአሁኑ እና ለምመጣውም ጭምር ነው, በመጀመሪያ ሰውን ስፈጠር ከ 12 ብልት ጋር ፈጠሮ አንድ አካል አደረገ ።
🖍በአድስ ክዳን በሥጋ ተገልጦ ቤተክርስቲያን እየመሠረት 12 ሐዋርያት መርጦ አንድ አካል ናቸው አለ። ከ 12ቱ አንዱ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ ነው እርሱም በወደቀ ግዜ መልሶ በእርሱ ቦታ መተካት ሥራ ተሰራ ማቲያስ ተመረጠ, ለምን ይመስላችኋል ? ከ 11 ሐዋርያት ጋር መሠራት አልቀጠለም ?።
🖍አካል ማለት የ 12 ብልት ስብስብ እንጂ የ 11 ብልት አይደለም , ለምሳሌ አንድ ሰው ኮላሊት ከታመመ አውጥቶ ሌላ መተካት ሥራ ይሠራል ምክንያቱም ኮላሊት ከለል ሰው መኖር አይችልም ኮላሊት የራሱ ሥራ አለው ሌላ ብልት መሠራት የማይችለው።
🖍በመንፈሳዊ እይታ አሥራ ሁለቱም ብልት ናቸው አንዱ የምያይ(ዓይን ) ነው, አንዱ የምተነፈስ(አፊንጫ) ነው, አንደ ማዳመጫ(ጆሮ) ነው, አንዱ ደግሞ ለሁሉ ትዕዛዝ የምሰጥ ( አዕምሮ ወይም Brain ) ነው።
🖍እግሩን እሾህ ብወጋ እጁ ያወጣል ምን አጋባኝ እግሩ ያውጣ አይልም ህመሙ ለ እጅም ነው በአካሉ ስለሆነ ነው።
🖍እኔ ለራሴ እኖራለሁ ማለት አይሠራም በአካል ከሆንክ የግድ ከእጅህ , እግርህ , ከዓይንህ ጋር ሳትስማማ መኖር አትችልም። በሆነ አጋጣሚ አዳጋ አንድ ሰው እግሩ ተሰብሮ ከአካል ብወጣ ያ እግሩ አያድግም የራሱን መልክ ለቅቆ ደሮቆ አጥንት 🦴 ብቻ ይቀራል ምክንያቱም በአካሉ ስሆን የተለያዩ ንጥረ ነገሮች በ System circulation ይደረሳል ከአካል ከተናጠል ምንም ነገር ስለማይደረስ ይደርቃል ።
🖍ልክ እንደዛው በቤተክርስቲያን ውስጥ ከአካል ተነጥሎ , አንዱ ከአንዱ ብልት ጋር ተሰማምቶ ካልኖረ ሰው ይደርቃል ምክንያቱም በሽታ አለው ከአካሉ የምወጡ ትምህርት መንፈሳዊ ምክር የተለያዩ ነገሮች ስለማይደርሱ። እንደዚህ ዓይነት በሽታ Science እንደዚህ ይላል Autoimmune Disease .
🖍ስለዚህ ከ Autoimmune Disease ራሳችሁን ጠብቁ ጤናማነት ያለው መንፈሳዊ ህይወት ኖራችሁ ኢየሱስን በዓይናችሁ እስክታዩ ድረስ።
አመሰግናቸዋለሁ የአንድ አምላክ ቤተሰቦቼ 🤲
ክፍል ሁለት ይቀጥላል ....

በየስፍራው ላላችሁ ቅዱሳን ሰላም ለእናንተ ይሁን!ቀደም ባሉት ጊዜያት ስለ ኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን አመሰራረት፣ ስለ ቀደምት መሪዎቿ ጥሪና መስዋዕትነት እንዲሁም እግዚአብሔር ወንጌሉ...
03/07/2024

በየስፍራው ላላችሁ ቅዱሳን ሰላም ለእናንተ ይሁን!

ቀደም ባሉት ጊዜያት ስለ ኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን አመሰራረት፣ ስለ ቀደምት መሪዎቿ ጥሪና መስዋዕትነት እንዲሁም እግዚአብሔር ወንጌሉን ያሰፋበትን የድንቅና ተአምራት መንገዶች በተለያዩ አቀራረቦች “Unseen Hands”, “Then came the Glory”, “Acts of God in Ethiopia” የተሰኙ መጻሕፍት መዘጋጀታቸው ይታወቃል። በቅርቡም “የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን አመሰራረትና እድገት” በሚል ርዕስ በቢሾፕ በቀለ ፈዬ የተዘጋጀ መጽሐፍ ለአንባቢያን ቀርቧል።

አሁን ደግሞ ዝርዝር መረጃዎችን በማሰባሰብና የተሰበሰበውን መረጃ በማቀናጀትና በማረም የመዳን ወንጌል በኢትዮጵያ የተስፋፋበት መንገድ በአጭሩ የሚተርክ “የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ጥቅል ታሪክ” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ታትሞ እጃችሁ ላይ ሊደርስ ቀናት ቀርተውታል።

የዚህ መጽሐፍ ዝግጅት ዋና አላማ እግዚአብሔር በመላው ኢትዮጵያ የሰራቸውን ዝርዝር ታሪኮች ለአንባቢ እስኪቀርቡ ድረስ የሐዋርያት ወንጌል በኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫ የተስፋፋበት መንገድን በአጭሩ ለማስቀመጥ ሲሆን ይህንን ታሪክ የሚያነቡ ቅዱሳን ወንጌል እንዴት በድንቅና በተአምራት እንደሰፋ፣ ይህም ሆኖ ሳለ ያልተወረሰ ገና ብዙ ህዝብ እንዳለ በማወቅ የወንጌል ሸክም እንዲኖራቸው ማበረታትና ማነቃቃት ነው።

አንብባችሁ እንደምትባረኩበት ሙሉ እምነታችን ነው!

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮ ቪዥዋልና ስነ-ጽሁፍ ክፍል!!

ዘፍጥረት 22¹⁶ እንዲህም አለው፦ እግዚአብሔር፦ በራሴ ማልሁ ይላል፤ ይህን ነገር አድርገሃልና፥ አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና¹⁷ በእውነት በረከትን እባርክሃለሁ፥ ዘርህንም እንደ ሰማይ ከዋ...
08/06/2024

ዘፍጥረት 22
¹⁶ እንዲህም አለው፦ እግዚአብሔር፦ በራሴ ማልሁ ይላል፤ ይህን ነገር አድርገሃልና፥ አንድ ልጅህንም አልከለከልህምና
¹⁷ በእውነት በረከትን እባርክሃለሁ፥ ዘርህንም እንደ ሰማይ ከዋክብትና በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ አበዛዋለሁ፤ ዘርህም የጠላቶችን ደጅ ይወርሳል፤
¹⁸ የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ፥ ቃሌን ሰምተሃልና።

“ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን...”   1ኛ ዮሐንስ 1፥2    "ኢየሱስ"“(For the life was manifested, and we have seen it, and bear wit...
04/06/2024

“ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን...”
1ኛ ዮሐንስ 1፥2
"ኢየሱስ"

“(For the life was manifested, and we have seen it, and bear witness..."
1 John 1:2

"Jesus"

በስፍራው ሁሉ ላላችሁ የቤተክርስቲያን ልጆች ሰላም ለእናንተ ይሁን!አዲሱን አመት በልባችን ለጌታ እየተቀኘንና እየዘመርን ለመጀመር የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ...
29/04/2024

በስፍራው ሁሉ ላላችሁ የቤተክርስቲያን ልጆች ሰላም ለእናንተ ይሁን!

አዲሱን አመት በልባችን ለጌታ እየተቀኘንና እየዘመርን ለመጀመር የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በዘማሪት ዮርዳኖስ መለስ የተዘጋጀውን አዲስ የዝማሬ ሰንዱቅ (Album) ለመታነጽና ለበረከት እንዲሆንላችሁ ወደ እናንተ ሲያደርስ በታላቅ ደስታ ነው።

ይህንን አልበም አዘጋጅታ ለእግዚአብሔር ክብርና ለቤተክርስቲያን መታነጽ ያበረከተችውን እህት ዮርዳኖስንና በዝግጅቱ የተሳተፉትን ሁሉ እግዚአብሔር በማያልቀው በረከቱ እንዲባርካቸው እየጸለይን ጌታችን ቢፈቅድ ብንኖር አልበሙ በጥቂት ቀናት ውስጥ እጃችሁ ባለው ስልክ ላይ በሚገኘው የአፖስቶሊክ ሶንግስ መተግበሪያ ላይ ዝግጁ ይሆናል።

የኦዲዮ ቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
ከጥቂት ቀን በኃላ Code ሲለቀቅ ከኛ ማገኘት ትችላላችሁ

ሚያዚያ 2016 ዓ.ም

“አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።”  — ሮሜ 8፥15
23/04/2024

“አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።”
— ሮሜ 8፥15

 #እንኳን ወደ ኢትዮጵያ ሐዋርያት ቤተክርስቲያን መልቲሚድያ አጌልግሎት የፈስቡክ ቻናል በደህና መጡ!
19/04/2024

#እንኳን ወደ ኢትዮጵያ ሐዋርያት ቤተክርስቲያን መልቲሚድያ አጌልግሎት የፈስቡክ ቻናል በደህና መጡ!

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አሜን - Amen posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share