New Creation Zion King's

New Creation Zion King's “Therefore, if anyone is in Christ, he is a new creation; the old has gone, the new has come!”
— 2Cor 5፥17 (NIV)

የእውነት ድምፅ"በሰላም አረፈ/ች" የምንለው ለሁሉም ሰው አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ  የዘላለም ሰላም የሚገኘው በክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ እንደሆነ ይናገራል።የዮሐንስ ወንጌል 14፤2714፤27 ሰላ...
28/12/2025

የእውነት ድምፅ
"በሰላም አረፈ/ች" የምንለው ለሁሉም ሰው አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ የዘላለም ሰላም የሚገኘው በክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ እንደሆነ ይናገራል።
የዮሐንስ ወንጌል 14፤27
14፤27 ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።

ለመዳን
• ንስሐ መግባት፦ ከኃጢአት መንገድ ዞር ብሎ ወደ እግዚአብሔር መመለስ።
• ማመን፦ ኢየሱስ ስለ እኛ ኃጢአት እንደሞተና በሦስተኛው ቀን እንደተነሳ በልብ አምኖ በአፍ መናገር።
ወደ ሮሜ ሰዎች 10፤10
10፤10 ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
• መቀበል፦ ኢየሱስን የግል ጌታና መድኃኒት አድርጎ መቀበል።
የዮሐንስ ወንጌል 1፤12-13
1፤12 ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤
1፤13 እነርሱም ከእግዚአብሔር ተወለዱ እንጂ ከደም ወይም ከሥጋ ፈቃድ ወይም ከወንድ ፈቃድ አልተወለዱም።
ስለዚህ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።
ወደ ዕብራውያን 4፤7
4፤7 ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ .......።

የድነት (የመዳን) ጸሎት
ይህን ጸሎት አሁን ከጸለይክ/ሽ ከጨለማ ወደ ብርሃን የምትሻገሩበት ድልድይ ነው፦
"ጌታ ኢየሱስ ሆይ፤ እኔ ኃጢአተኛ እንደሆንኩ አውቃለሁ። ዛሬ ግን ንስሐ ገብቼ ወደ አንተ እመጣለሁ። ስለ እኔ በመስቀል ላይ የፈሰሰው ደምህ ከኃጢአት ሁሉ ያነጻኛል። በሞትህና በትንሳኤህ አምናለሁ። ዛሬ የሕይወቴ ጌታና መድኃኒት አድርጌ እቀበልሃለሁ። በሕይወት መዝገብ ላይ ስሜን ጻፍልኝ። በአንተ ዘንድ ለዘላለም እንድኖር አዲስ ፍጥረት አድርገኝ። ስለተቀበልከኝ አመሰግንሀለሁ በኢየሱስ ስም አሜን!"

24/08/2022
12/07/2022

ታላቅ የቤተክርስቲያን ተከላ ኮንፍረንስ በሻሸመኔ
እሁድ ሃምሌ 10 ከ 9:00 ሰአት ጀምሮ

17/04/2022

ምሳሌ 8
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በውኑ ጥበብ አትጮኽምን? ማስተዋልስ ድምፅዋን አትሰጥምን?
² በኮረብታ ላይ በመንገድ አጠገብ በጎዳና መካከል ትቆማለች።
³ በበሩ አጠገብ በከተማይቱም መግቢያ፥ በደጁ መግቢያ ትጮኻለች፦
⁴ እናንተ ሰዎች፥ እናንተን እጠራለሁ፥ ድምፄም ወደ ሰዎች ልጆች ነው።
⁵ እናንተ አላዋቂዎች፥ ብልሃትን አስተውሉ፤ እናንተም ሰነፎች ጥበብን በልባችሁ ያዙ።
⁶ የከበረች ነገርን እናገራለሁና ስሙ፤ ከንፈሮቼም ቅን ነገርን ለመናገር ይከፈታሉ።
⁷ አፌ እውነትን ይናገራልና፥ ከንፈሮቼም ክፋትን ይጸየፋሉ።
⁸ የአፌ ቃላት ሁሉ ጽድቅ ናቸው፤ ጠማማ ዘወርዋራም አይደሉም።
⁹ እነርሱ በሚያስተውሉ ዘንድ የቀኑ ናቸው፥ እውቀትንም ካገኙአት ሰዎች ጋር የተስማሙ ናቸው።
¹⁰ ተግሣጼን እንጂ ብርን አትቀበሉ፥ ከምዝምዝ ወርቅም ይልቅ እውቀትን ተቀበሉ።
¹¹ ጥበብ ከቀይ ዕንቍ ትበልጣለችና፤ የከበረ ነገር ሁሉ አይተካከላትም።
¹² እኔ ጥበብ በብልሃት ተቀምጫለሁ፥ እውቀትንም ጥንቃቄንም አግኝቻለሁ።
¹³ እግዚአብሔርን መፍራት ክፋትን ይጠላል፤ ትዕቢትንና እብሪትን ክፉንም መንገድ ጠማማውንም አፍ እጠላለሁ።
¹⁴ ምክርና መልካም ጥበብ የእኔ ነው፤ ማስተዋል እኔ ነኝ፥ ብርታትም አለኝ።
¹⁵ ነገሥታት በእኔ ይነግሣሉ፥ ሹማምቶችም የቀናውን ነገር ይደነግጋሉ።
¹⁶ አለቆች በእኔ ያዝዛሉ፥ ክቡራንና የምድር ፈራጆችም ሁሉ።
¹⁷ እኔ የሚወድዱኝን እወድዳለሁ፥ ተግተው የሚሹኝም ያገኙኛል።
¹⁸ ብልጥግናና ክብር በእኔ ዘንድ ነው፥ ብዙ ሀብትና ጽድቅም።
¹⁹ ፍሬዬም ከምዝምዝ ወርቅ ይሻላል፥ ቡቃያዬም ከተመረጠች ብር።
²⁰ እኔ በጽድቅ መንገድ እሄዳለሁ፥ በፍርድም ጎዳና መካከል፥
²¹ ለሚወድዱኝ ርስት አወርሳቸው ዘንድ ቤተ መዛግብታቸውንም እሞላ ዘንድ።
²² እግዚአብሔር የመንገዱ መጀመሪያ አደረገኝ፥ በቀድሞ ሥራው መጀመሪያ።
²³ ከጥንቱ ከዘላለም ጀምሮ ተሾምሁ ምድር ከመፈጠርዋ አስቀድሞ።
²⁴ ቀላያት ገና ሳይኖሩ እኔ ተወለድሁ፥ የውኃ ምንጮች ገና ሳይፈልቁ።
²⁵ ተራሮች ገና ሳይመሠረቱ፥ ከኮረብቶች በፊት እኔ ተወለድሁ፥
²⁶ ምድሪቱንና ሜዳውን ገና ሳይፈጥር የመጀመሪያውንም የዓለም አፈር።
²⁷ ሰማዮችን በዘረጋ ጊዜ አብሬ ነበርሁ፥ በቀላያት ፊት ክበብን በደነገገ ጊዜ፥
²⁸ ደመናትን በላይ ባዘጋጀ ጊዜ፥ የቀላይን ምንጮች ባጸና ጊዜ፥
²⁹ ለባሕርም ዳርቻን በወሰነ ጊዜ ውኃ ከትእዛዙ እንዳያልፍ፥ የምድርን መሠረት በመሠረተ ጊዜ፥
³⁰ የዚያን ጊዜ እኔ በእርሱ ዘንድ ዋና ሠራተኛ ነበርሁ፤ ዕለት ዕለት ደስ አሰኘው ነበርሁ፥ በፊቱም ሁልጊዜ ደስ ይለኝ ነበርሁ፥
³¹ ደስታዬም በምድሩ ተድላዬም በሰው ልጆች ነበረ።
³² አሁንም ልጆቼ ሆይ፥ ስሙኝ፤ መንገዴንም የሚጠብቁ ምስጉኖች ናቸው።
³³ ትምህርቴን ስሙ፥ ጠቢባንም ሁኑ፥ ቸል አትበሉትም።
³⁴ የሚሰማኝ ሰው ምስጉን ነው ዕለት ዕለት በቤቴ መግቢያ የሚተጋ፥ የደጄንም መድረክ የሚጠብቅ።
³⁵ እኔን ያገኘ ሕይወትን ያገኛልና፥ ከእግዚአብሔርም ሞገስን ያገኛልና።
³⁶ እኔን ያጣ ግን ራሱን ይጐዳል፤ የሚጠሉኝ ሁሉ ሞትን ይወድዳሉ።

18/03/2022

2ኛ ተሰሎንቄ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ እኛ ግን፥ በጌታ የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ እግዚአብሔርን ልናመሰግን ግድ አለብን፥ እግዚአብሔር በመንፈስ መቀደስ እውነትንም በማመን ለመዳን እንደ በኵራት መርጦአችኋልና፤
¹⁴ ለዚህም የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር ለማግኘት በወንጌላችን ጠራችሁ።
¹⁵ እንግዲያስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ጸንታችሁ ቁሙ፥ በቃላችንም ቢሆን ወይም በመልእክታችን የተማራችሁትን ወግ ያዙ።
¹⁶-¹⁷ ራሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስና የወደደን በጸጋም የዘላለምን መጽናናት በጎንም ተስፋ የሰጠን እግዚአብሔር አባታችን ልባችሁን ያጽናኑት በበጎም ሥራና በቃል ሁሉ ያጽኑአችሁ።

ሉቃስ 12 (አዲሱ መ.ት)¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯⁴² ጌታም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “እንግዲህ፣ ምግባቸውን በተገቢው ጊዜ እንዲሰጣቸው ጌታው በቤተ ሰዎቹ ላይ የሚሾመው ታማኝና ብልህ መጋቢ ማነው?⁴³ ጌ...
17/05/2021

ሉቃስ 12 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴² ጌታም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “እንግዲህ፣ ምግባቸውን በተገቢው ጊዜ እንዲሰጣቸው ጌታው በቤተ ሰዎቹ ላይ የሚሾመው ታማኝና ብልህ መጋቢ ማነው?
⁴³ ጌታው ሲመለስ እንዲህ ሲያደርግ የሚያገኘው አገልጋይ እርሱ ብፁዕ ነው።

03/02/2021
27/12/2020

“እግዚአብሔር (ያህዌ) ራሱ በፊትህ ይሄዳል፤ ከአንተም ጋር ይሆናል፤ ፈጽሞ አይለይህም፤ አይተውህምም፤ አትፍራ፤ ተስፋም አትቍረጥ።””
— ዘዳግም 31፥8 (አዲሱ መ.ት)
“The Lord himself goes before you and will be with you; he will never leave you nor forsake you. Do not be afraid; do not be discouraged."”
— Deu 31፥8 (NIV)

22/12/2020

“በእርሱ በመታመናችሁ የተስፋ አምላክ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ፤ ይኸውም በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ተስፋ ተትረፍርፎ እንዲፈስላችሁ ነው።”
— ሮሜ 15፥13 (አዲሱ መ.ት)
“May the God of hope fill you with all joy and peace as you trust in him, so that you may overflow with hope by the power of the Holy Spirit.”
— Rom 15፥13 (NIV)

25/11/2020

“You have not handed me over to the enemy but have set my feet in a spacious place.”
— Ps 31፥8 (NIV)

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New Creation Zion King's posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share