Daregot Media

Daregot Media የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ከ ዶግማዋን ፣ ቀኖናዋንና ትውፊቷን መሠረት ያደረጉ መንፈሳዊ ጽሑፎች እና ምስሎች ይቀረቡበታል።

ዳረጎት ከራት በኋላ እንደጭማሪ፣ እንደማጠንከርያ የሚቀመስ ቀለል ያለ መብል ነው፡፡ እናንተም ዋናውን መንፈሳዊ መብል ከሊቃውንት አባቶቻችን አንደበት፣ ከመጻሕፍት ምስክርነት፣ ከደጋግ አበው ሕይወት፣ ከቤ/ክ ተጋድሎዋና ድሏ እየተማራችሁ ይህችን የኛን ዳረጎት ቅመሱልን፡፡
JOIN OUR TELEGRAM CHANNEL
http://t.me/daregot

10/09/2021
ፍካሬ እንስሳትፍካሬ እንስሳት ከመጋቤ ምሥጢር ነባር ሥራዎች (Original Works) አንዱ ነው። ጹሑፉ በ1992 ዓ.ም ተጽፎ በ25 ገጽ ከተቀነበበው ጥራዝ በጥቂቱ የተወሰደ ነው። ወንድማች...
31/07/2021

ፍካሬ እንስሳት

ፍካሬ እንስሳት ከመጋቤ ምሥጢር ነባር ሥራዎች (Original Works) አንዱ ነው። ጹሑፉ በ1992 ዓ.ም ተጽፎ በ25 ገጽ ከተቀነበበው ጥራዝ በጥቂቱ የተወሰደ ነው። ወንድማችን ዲ/ን ዶ/ር ከሳቴብርሃን ገ/ኢየሱስ እንዲህ አዘጋጅቶታል።

ሙሉ ጹሑፉን ሊንኩን ተጭነው ያንብቡ https://telegra.ph/ፍካሬ-እንስሳት-07-31

15/07/2021

ዛሬ በአቢላክ የቴሌቪዥን መርሐግብር

አቢላክ የቴሌቪዥን መርሐግብር ከዳረጎት ሚዲያ ጋር በመተባበር የአባታችን የመጋቤ ምሥጢር አለቃ መሰረት ተሰማ ፶ቀን መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀውን ዘጋቢ ትዕይንት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቴሌቪዥን ጣቢያ (EOTC TV) እያቀረቡ ይገኛሉ።

- ክፍል አንድ ዘጋቢ ትዕይንቱ ባለፈው ሐሙስ የቀረበ ሲሆን ላመለጣችሁ ከታች አያይዘንላችኋል።

- ክፍል ኹለት ዘጋቢ ትዕይንቱ ዛሬ ሐሙስ በEOTC TV ላይ በአቢላክ የቴሌቪዥን መርሐግብር ላይ ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ መከታተል ትችላላችሁ።

ዜና ሕይወቱ ለመጋቤ ምሥጢር“ዜና ሕይወቱ ለመጋቤ ምሥጢር” የተሰኘው ይህ ጹሑፍ ለመጽሔት ኅትመት እንዲመች መጠነኛ ጭማሪና ማሻሻያ ከመደረጉ ውጭ ሙሉ በሙሉ በዕለተ ቀብራቸው የተነበበው የሕይወ...
14/07/2021

ዜና ሕይወቱ ለመጋቤ ምሥጢር

“ዜና ሕይወቱ ለመጋቤ ምሥጢር” የተሰኘው ይህ ጹሑፍ ለመጽሔት ኅትመት እንዲመች መጠነኛ ጭማሪና ማሻሻያ ከመደረጉ ውጭ ሙሉ በሙሉ በዕለተ ቀብራቸው የተነበበው የሕይወት ታሪክ ግልባጭ ነው። ሙሉ ጹሑፉን ሊንኩን ተጭነው ያንብቡ https://telegra.ph/ዜና-ሕይወቱ-ለመጋቤ-ምሥጢር-07-14

07/07/2021

ከመኖሪያ እስከ ጉባኤ ቤታቸው

ዳረጎት ሚዲያ ከአሰላ ደ/መ/መ/ቤ/ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት ጋር በመተባበር ለሦስት ቀናት ለምዕመናንን ክፍት የነበረው ዝክረ መጋቢ አውደርእይ በአካል ተገኝታችሁ መታደም ላልቻላችሁ እነሆ ይዘንላችሁ ቀርበናል።

ፎቶ: የዝክረ መጋቤ ምሥጢር አለቃ መሰረት ተሰማ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ በዕለተ መድኃኔዓለም በልዩ ልዩ መርኃግብራት ሲከናወን ቆይቶ ማምሻውን ተጠናቋል። ወረብ፤ ትርዒቶች ዝማሬዎችና በእሳቸው ህ...
05/07/2021

ፎቶ: የዝክረ መጋቤ ምሥጢር አለቃ መሰረት ተሰማ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ በዕለተ መድኃኔዓለም በልዩ ልዩ መርኃግብራት ሲከናወን ቆይቶ ማምሻውን ተጠናቋል። ወረብ፤ ትርዒቶች ዝማሬዎችና በእሳቸው ህይወት ላይ ያተኮረ አውደርእይ ተካሂዷል። ዳረጎት ሚዲያም ለዚህ ጉባኤ መሳካት የየድርሻቸውን የተወጡትን በሙሉ ማመስገን ይወዳል።

(እሁድ 27/10/2013 አሰላ)


https://t.me/daregot

''አለቃ መሠረት''''አለቃ መሠረት'' የተሰኘውና የታላቁን አባት መጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማን የሕይወት ታሪክ፤ የጿፏቸውን የሥነ-ጹሑፍ ሥራዎች፤ የተደረሱላቸውን ቅኔያት፤ የልጆቻቸውን ምስክ...
03/07/2021

''አለቃ መሠረት''

''አለቃ መሠረት'' የተሰኘውና የታላቁን አባት መጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማን የሕይወት ታሪክ፤ የጿፏቸውን የሥነ-ጹሑፍ ሥራዎች፤ የተደረሱላቸውን ቅኔያት፤ የልጆቻቸውን ምስክርነትን የያዘው መጽሔት ቅዳሜ 26/10/2013 በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቻቸው በተገኙበት በተዘጋጀው ትልቅ ጉባኤ ላይ በይፋ ተመርቋል። በዕለቱ ከዳረጎት ሚዲያ ለቤተሰቦቻቸው የልዩ ዕትሙ የፊት ገጽ በማስታወሻነት ተበርክቷል። ጉባኤው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል።


https://t.me/daregot

የፎቶ ዘገባ📸: በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የአባታችን የመጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማ የ፵ ቀን መታሰቢያን አስመልክቶ የተዘጋጀው ጉባኤ ዛሬ ተጀምሯል። ጉባኤው በቀጣይ ቀ...
02/07/2021

የፎቶ ዘገባ📸: በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የአባታችን የመጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማ የ፵ ቀን መታሰቢያን አስመልክቶ የተዘጋጀው ጉባኤ ዛሬ ተጀምሯል። ጉባኤው በቀጣይ ቀናት ሰፊ መርኃግብራትን አካቶ የሚቀጥል ይሆናል።

የመጀመሪያው የዳረጎት ዘተዋሕዶ የወረቀት ህትመት መጽሔት ለአንባቢዎች ሊቀርብ ነው።''አለቃ መሠረት'' የተሰኘውና የዳረጎት ሚዲያ አባላትን ጨምሮ በርካቶችን በማስተማር መሠረት በሆኑት መጋቤ ...
30/06/2021

የመጀመሪያው የዳረጎት ዘተዋሕዶ የወረቀት ህትመት መጽሔት ለአንባቢዎች ሊቀርብ ነው።

''አለቃ መሠረት'' የተሰኘውና የዳረጎት ሚዲያ አባላትን ጨምሮ በርካቶችን በማስተማር መሠረት በሆኑት መጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማ የሕይወት ታሪክ፤ የጿፏቸውን የሥነ-ጹሑፍ ሥራዎች፤ የተደረሱላቸውን ቅኔያት፤ የልጆቻቸውን ምስክርነትን የያዘ መጽሔት ተዘጋጅቶ ለአንባቢያን ሊቀርብ ነው።

በመጽሔቱ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መንበረ ፓትርያሪክ ጠ/ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊና የአርሲና የምሥራቅ ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ያሬድ ጨምሮ የሀገረስብከቱ ከፍተኛ አመራሮችና አባቶች መልዕክት አስተላልፈዋል።

በ48 ገጾች የተዘጋጀው የዳረጎት ዘተዋህዶ መጽሔት ልዩ ዕትም ስለ መጋቤ ምሥጢር አለቃ መሰረት ተሰማ ተነግረው የማይጠገቡና ለጆሮ አዲስ የሆኑ ታሪኮችን በውስጡ አካቷል።

በጽሔቱ በ700 ቅጂ ለህትመት የሚበቃ ሲሆን ከፊታችን አርብ ጀምሮ በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን የአባታችንን የ፵ ቀን መታሰቢያ አስመልክቶ በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ በይፋ ተመርቆ ለአንባቢያን ይቀርባል።

በዚህ የመታሰቢያ ጉባኤ ላይ ታላላቅ መምህራነ ወንጌልና ዘማሪያን እንዲሁም ተማሪዎቻቸው ይገኛሉ። በህይወት ታሪካቸው ላይ ያተኮረ አጭር ዶክመንተሪም ለዕይታ ይበቃል። ዳረጎት ሚዲያ በአሰላ ከተማና አከባቢዋ ለሚገኙ ቤተሰቦቹ በዚህ ትልቅ ጉባኤ ላይ ተገኝተው የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀርባል።

የፎቶ ዘገባ፦ ከ28 ዓመት በላይ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ቤ/ክ በስብከተ ወንጌል ኃላፊነት እንዲሁም በትርጓሜ መጻሕፍት መምህርነት ያገለገሉት ሊቁ አባታችን መጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማ አርፈዋ...
28/05/2021

የፎቶ ዘገባ፦ ከ28 ዓመት በላይ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ቤ/ክ በስብከተ ወንጌል ኃላፊነት እንዲሁም በትርጓሜ መጻሕፍት መምህርነት ያገለገሉት ሊቁ አባታችን መጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማ አርፈዋል።

የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ታላላቅ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ ዘመድ ወዳጆቻቸው የሥጋና የመንፈስ ልጆቻቸው በተገኙበት ግንቦት 19 ቀን ባገለገሉበት ደብር ተፈጽሟል።

የዳረጎት ጸሐፍትን ያፈሩና ያስተማሩ የሚዲያው መመሥረት ምክንያት እንደመሆናቸው ዝርዝር ጥንቅር በቀጣይ ጊዜ ይዘን እንቀርባለን።

የአበባ መንፈሳዊ ምስጢርና ምሣሌነት፩ኛ፡- የምሥራችና የመልካም ዜና መግለጫ ነው፡ ለዚህ ኹለት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላቸን ታሪኮች እንጥቀስ፡፡ የመጀመርያው በዘመነ ኖኅ የተፈጸመው የጥፋት...
11/10/2020

የአበባ መንፈሳዊ ምስጢርና ምሣሌነት

፩ኛ፡- የምሥራችና የመልካም ዜና መግለጫ ነው፡

ለዚህ ኹለት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላቸን ታሪኮች እንጥቀስ፡፡ የመጀመርያው በዘመነ ኖኅ የተፈጸመው የጥፋት ውኃ ታሪክ ነው፡፡ በኦሪት ዘፍጥረት ከምዕ.፮ ጀምሮ ተጽፎ እንደምናገኘው፦ የሥጋ ለባሽ የኃጢአትና የክፋት ቁልል ከቀርሜሎስ ተራራ ገዝፎ፣ ሰማያትን አልፎ የእግዚአብሔር ትዕግስት ፍጻሜን ሲነካው ንፍር ውኃ ከበደል ጽዋ ተቀድታ እንድትፈስ አምላካዊ ትዕዛዝ ወጣች፡፡ ለ ፵ ቀን ያኽል ያለማቋረጥ ቀንና ሌሊት በዘነበው ዝናም ከኖኅና ከ፯ ቤተሰቦቹ እንዲሁም በመርከቢቱ ውስጥ ከነበሩት እንስሳት በቀር ኹሉም ጠፋ፡፡

ከ፻፶ ቀን የማየ አይኅ ሙላት በኋላ ግን እግዚአብሔር ኖኅና በመርከቢቱ ውስጥ ያሉትን አሰበና ነፋስን በምድር ላይ እንዲነፍስ፤ ውኃውም መጉደል እንዲጀምር አደረገ፡፡ እንደ ቅዱሳት መጻሕፍት ምሥክርነት ይኽ የኾነው በሰኔ ወር ውስጥ ነው፡፡ ውኃው ፍጹም ጎድሎ ኖኅ ከቤተሰቡና ከፍጥረቱ ጋር ከመርከቢቱ የወጣው ግን ከ፫ ወር በኋላ በወርኃ መስከረም ነው፡፡ ኖኅ ርግብን በመላክ የምድርን መድረቅ ከማረጋገጡ በተጨማሪ እግዚአብሔር ለምሥክርነት የላከለት ፍጥረት አለ፡፡ አበባ! የመስከረም ወር የአበባ መብቀያ ወር በመኾኑ በጥፋት ውኃ መጉደል ሰበብ ተራሮች አናት ላይ አበቦች ችምችም ብለው በቅለው ስፍራውን መልተው ኖኅ ተመለከተ፡፡ በዚህም ኖኅ እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ኹሉ ጋር ያጠፋ ውን አበባን መልሶ በማብቀል ስላሳየው፤ የሰውን ዘር እንደገና በምድር ላይ የሚያበዛበት ከመርከቢቱ የመውጫ ሰዓት እንደኾነ በዚህ ተረዳ፡፡

ተስፋና የምሥራች የኾነውን የውኃውን መጉደል ዜና ከርግቢቱ የወይራ ዝንጣፊ በተጨማሪ የምድር አበቦች ምሥክርነት አጸናው ማለት ነው፡፡ በሐዲስ ኪዳንም እንዲሁ፦ ቅዱስ ገብርኤል አዳም ከነልጆቹ ለ ፭ሺህ ፭፻ ዘመን ሲጠባበቀው የነበረውን የተስፋውን ቃል ፍጻሜ፣ የአምላክን ከርሷ መጸነስና መወለድ ለድንግልማርያም ያበሠራት የመልካም ዜና መግለጫ የሚኾን አበባ ይዞ ነው፡፡ አንድም የአምላክ እናቱ የምትኾኝ ደስ ይበልሽ ሲል፤ በሌላም በኩል የምሥራች የሆነ የእግዚአብሔርን ሰው መኾን የሰውን ልጅን ድኅነት ጅማሬ ስለነገራት፡፡

ለዚህ ነው ጌታችን በተወለደባት ሌሊት ይኼው ታላቅ መልአክ ለእረኞች ዜና ልደቱን ሲነግራቸው ‹‹ለሕዝቡ ኹሉ የሚኾን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁ፡፡›› ያላቸው፡፡ ባይወለድ ኖሮ አይጠመቅም፤ ተሰቅም ድኅነትን አናገኝምና በጨለማና በሞት ጥላ ይኖር ለነበረ የሰው ዘር የመዳኑ ነገር እርግጥ የኾነበት በጎ ዜና ነው የአምላክ ሰው መኾን፡፡ በብዙ “የብሥራተ ቅዱስ ገብርኤል” ሥዕላት ላይ መልዓኩ አበባ ይዞ የሚሳለው በዚሁ ትውፊት መነሻነት ነው፡፡

ይቆየን!

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Daregot Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Daregot Media:

Share