Servant Adisu ute

Servant Adisu ute "ኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ትናንትና፡ዛሬ፡እስከ፡ለዘላለም፡ያው፡ነው;"(ዕብራውያን13፥8)

24/01/2026

ቁ-2 እንድለቀቅ በአክብሮት እንጠይቃለን ። ይድረስ በጣም ለምንወዳት ለዘማሪት #ሰላም በቁ-1 አልበም ብዙ ተባርከናልና እባክሽ ቁ-2 የመዝሙር አልበም ቶሎ ብለቀቅ🙏 👉 ምንም ጣዕም በሌላቸው እና ከዘፈን በማይሻሉ መዝሙሮች ታፊኔን ልንሞት ነው ።

07/01/2026

! ውድ አንባቢዎቼ ዛሬ ስለታላቅ የምስራች ብናወራ የማይሰለች ብንሰማ ለጆሮ የማይቆረቁር ታላቅ ወሬ (የምስራች) ላወጋችሁ ወደድኩ!! የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ "የዘመናት መከፈያ" (BC እና AD) ተብሎ የሚታወቅ፣ ሰማይና ምድርን ያናወጠ ክስተት ነው። ይህ ልደት ከማንኛውም ሰው ልደት የሚለይበትን ምክንያት፣ በጨለማው መንግሥት ላይ የፈጠረውን ድንጋጤና የስጦታዎቹን ምሥጢር እንደሚከተለው በዝርዝር እንመልከት።

1. የክርስቶስን ልደት ከሌሎች ሰዎች ልደት የተለየ የሚያደርገው ምንድን ነው?

በምድር ላይ ቢሊዮን ሕዝብ ተወልዷል፤ ነገር ግን የክርስቶስ ልደት ልዩ የሆነው በሚከተሉት ነጥቦች ነው፦
(Incarnation)፦ ሌሎች ሰዎች ሁሉ ሕይወታቸው የሚጀምረው ሲጸነሱ ነው። ክርስቶስ ግን ዓለም ሳይፈጠር የነበረ፣ ዘላለማዊ አምላክ ሆኖ ሳለ ለእኛ ሲል ሰው ሆኖ መጣ። "ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ" (ዮሐንስ 1፡14)።
፦ የሰው ልጅ ሁሉ በሥጋዊ ግንኙነትና በኃጢአት ባሕርይ ይወለዳል። ክርስቶስ ግን ያለ ወንድ ዘር በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከድንግል ማርያም ተወለደ (ማቴዎስ 1፡18-23)። ይህም ከኃጢአት ነፃ የሆነ "ቅዱስ" አዳኝ እንዲሆን አድርጎታል።
፦ ክርስቶስ ከመወለዱ በመቶዎችና በሺዎች ከሚቆጠሩ ዓመታት በፊት የት፣ እንዴትና ከማን እንደሚወለድ በዝርዝር ተነግሮለት ነበር። ለምሳሌ በቤተልሔም እንደሚወለድ (ሚክያስ 5፡2) እና ከድንግል እንደሚወለድ (ኢሳይያስ 7፡14) ተነግሯል።

2. በምድር ነገሥታትና በጨለማው መንግሥት ላይ የፈጠረው "ትኩሳት"

የክርስቶስ መወለድ ለድሆችና ለትሑታን "የምሥራች" ሲሆን፣ ለጨለማው መንግሥትና ለምድር ትዕቢተኛ ነገሥታት ግን ታላቅ ድንጋጤ ነበር።
፦ ሰብአ ሰገል "የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው?" ብለው ሲጠይቁ፣ ንጉሥ ሄሮድስና መላው ኢየሩሳሌም ደነገጡ (ማቴዎስ 2፡3)። ሄሮድስ ሥልጣኑን የሚቀማው መስሎት በታላቅ ቁጣ ተሞልቶ በቤተልሔም ያሉ ሕፃናትን አስጨረሰ። ይህ በምድር ነገሥታት ዘንድ የፈጠረው ትልቅ "ትኩሳት" ነበር።
፦ የክርስቶስ ልደት ሰይጣን በሰው ልጅ ላይ ያለውን የኃጢአትና የሞት አገዛዝ ለማፍረስ የተደረገ "የሰማይ ወረራ" ነው። ቅዱስ ቃሉ እንደሚለው "የእግዚአብሔር ልጅ የተገለጠው የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ ነው" (1 ዮሐንስ 3፡8)።
፦ ክርስቶስ የተወለደው ሊሞት ነው፤ በመሞቱ ግን "በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን ዲያብሎስን በሞቱ እንዲሽር" ተወለደ (ዕብራውያን 2፡14)። ስለዚህ ልደቱ የሰይጣን ሽንፈት መጀመሪያ ነበር።

3. የሰብአ ሰገል ስጦታዎችና ትንቢታዊ ትርጉማቸው

ሰብአ ሰገል ለሕፃኑ የሰገዱት እንደ ተራ ሕፃን ሳይሆን እንደ አምላክና ንጉሥ ነው። ያቀረቧቸው ስጦታዎችም የሚከተሉት ትርጉሞች አሏቸው፦

✍️ወርቅ፦ ወርቅ የክብርና የንግሥና ምልክት ነው። ይህም ኢየሱስ ክርስቶስ የነገሥታት ንጉሥ መሆኑንና መንግሥቱም የዘላለም መሆኑን ለማወጅ የቀረበ ስጦታ ነው (መዝሙር 72፡15)።
✍️ዕጣን፦ ዕጣን ለአምልኮና ለክህነት አገልግሎት የሚውል ነው። ይህም ኢየሱስ እውነተኛ አምላክና በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የሚቆም ሊቀ ካህናት መሆኑን ያሳያል (ሚልክያስ 1፡11)።
✍️ከርቤ፦ ከርቤ ለመድኃኒትነትና ለሙታን መገነዣነት ያገለግላል። ይህ ስጦታ ኢየሱስ ስለ ዓለም ኃጢአት የሚሞት አዳኝ መሆኑን ያመለክታል። ገና በልደቱ ቀን ሞቱና ቤዛነቱ የታወጀበት ስጦታ ነው (ዮሐንስ 19፡39)።

4. የዛሬው ወንጌል አማኝ ሊረዳው የሚገባው እውነት

አንድ አማኝ ከልደት ታሪክ ሊማራቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች፦
ሀ. የእግዚአብሔር ታማኝነት፦ እግዚአብሔር በገነት ለሰው ልጅ የገባውን የተስፋ ቃል (ዘፍጥረት 3፡15) ሳይረሳ በጊዜው መፈጸሙን አይተን፣ ዛሬም በገባልን ቃል ላይ እንድንታመን ያስተምረናል።

ለ. እውነተኛ አምልኮ፦ ሰብአ ሰገል ንብረታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን መስዋዕት አድርገው ጌታን ፍለጋ ሄደዋል። እኛም ጌታን በመፈለግና ምርጥ ስጦታችንን (ሕይወታችንን) ለእርሱ በመስጠት ልንመላለስ ይገባል።

ሐ. የክርስቶስ በውስጣችን መኖር፦ ታላቁ ምሥጢር ክርስቶስ በቤተልሔም መወለዱ ብቻ ሳይሆን፣ በእኛ ውስጥ መኖሩ ነው። "ክርስቶስ በእናንተ ዘንድ መሆኑ የክብር ተስፋ ነው" (ቆላስይስ 1፡27)።

መ. ከፍርሃት ነፃ መውጣት፦ ሄሮድስና ጨለማው ቢደነግጡም፣ አማኝ ግን "አትፍሩ፣ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁ" የሚለውን የመላእክት ቃል መያዝ አለበት።
#ማጠቃለያ፦ የክርስቶስ ልደት የሰላም፣ የፍቅርና የድል አዋጅ ነው። ዛሬ የምናከብረው በዓል ስለ ጌጥና ስለ ግብዣ ሳይሆን፣ በጨለማ ውስጥ ለነበርን ለእኛ "ታላቅ ብርሃን" ስለወጣልን ሊሆን ይገባል (ኢሳይያስ 9፡2)

🙏ውድ አንባቢዎቼ ይህንን ጥልቅ ጥናት አብራችሁኝ ስላጠናችሁ እግዚአብሔር ይባርካችሁ! እስኪ ልጠይቃችሁ ሳትዋሹ አንብባችሁ የጨረሳችሁ በትምህርቱ ምን እንደተጠቀማችሁ አስረዱኝ! በብዙ ድካም ወደእናንተ ትምህርቶችን እያዘጋጀሁ እንደማቀርብ አትርሱ! ሁል ጊዜ በሁሉ ከጎኔ ስለምትሆኑ እግዚአብሔር ይባርካችሁ እላለሁ!!
✍️ወንድማችሁ Desta WendimuJoy Official ነኝ! መልእክቴን ከወደዳችሁና ጠቃሚ እንደሆነ ካመናችሁ ለሌሎች እንዲደርስ በቅንነት ሼር አድርጉ እንጂ Coppy Peste በማድረግ በራሳችሁ አትለጥፉ ከለጠፋችሁም ምንጭ ጥቀሱ!! ደግሞም ሀሳባችሁን በComment section ላይ በማስቀመጥ አብራችሁኝ አገልግሉ!! ማድረጋችሁንም አትርሱ ተባረኩ! Wha.App number 091 380 2310

05/01/2026

🌱 #የእድገት አመለካከት (Growth Mindset)፦ "ገና" የሚለው ቃል ኃይል! ✨

#አእምሮህ እንደ ጡንቻ ሊያድግና ሊጠነክር እንደሚችል ያውቃሉ?

ብዙዎቻችን ራሳችንን በገነባነው "አልችልም" በሚል አጥር ውስጥ ታስረናል። ነገር ግን ይህንን አጥር ሰብሮ ለመውጣት የሚረዳ አንድ ድንቅ የአስተሳሰብ ሚስጥር አለ...

"ችሎታ የማይለወጥ ቋሚ ነገር አይደለም፤ ልክ እንደ ጡንቻ በጥረትና በትምህርት ሊያድግ የሚችል ነው!"

ብዙዎቻችን ስኬት የተሰጥኦ ወይም የዕድል ጉዳይ ብቻ ይመስለናል። ነገር ግን እውነተኛው ስኬት የሚወሰነው በአስተሳሰባችን ነው። በዓለም ላይ ሁለት ዓይነት ሰዎች አሉ፦

1.ቋሚ አመለካከት (Fixed Mindset) ያላቸው፦ "ተሰጥኦ የለኝም፣ ስለዚህ አልችልም" ብለው ተስፋ የሚቆርጡ።

2.የእድገት አመለካከት (Growth Mindset) ያላቸው፦ "አሁን ባልችልም፣ በልምምድና በጥረት ማሳካት እችላለሁ" ብለው የሚያምኑ።

የእድገት አመለካከትን ለማዳበር እነዚህን 3 ነጥቦች ተለማመድ፦

1. "ገና" የሚለውን ቃል ተጠቀም (The Power of Yet)

አንድን ነገር ሳታሳካ ስትቀር "አልቻልኩም" አትበል። ይልቁንም "ገና አልቻልኩም" በል። ይህች "ገና" የምትል ቃል አእምሮህ መፍትሔ እንዲፈልግና ጥረቱን እንዲቀጥል በር ትከፍትለታለች። ውድቀት የመንገዱ መጨረሻ ሳይሆን የመማሪያ ክፍልህ ነው።

2. ፈተናዎችን እንደ ዕድል እያቸው (Embrace Challenges)

አስቸጋሪ ሁኔታዎች ሲገጥሙህ "ለምን እኔ?" ከማለት ይልቅ "ከዚህ ምን እማራለሁ?" ብለህ ጠይቅ። የእድገት አመለካከት ያለው ሰው ፈተናን የሚመለከተው እንደ ግድግዳ ሳይሆን እንደ መሰላል ነው። በወጣህ ቁጥር ከፍ ትላለህ፤ በጠነከርክ ቁጥር ትበቅላለህ።

3. ጥረትን አድንቅ (Value the Process)

ውጤቱ ላይ ብቻ አታተኩር። ለደረስክበት ደረጃ ያደረግከውን ልፋት፣ ትግልና ጥረት አድንቅ። ስኬት ማለት መድረሻው ብቻ ሳይሆን በጉዞው ውስጥ የምታገኘው ማንነትህ ጭምር ነው።

💡 የዛሬው ትምህርት፦
አእምሮህ እንደ መሬት ነው። የእድገት አመለካከት ደግሞ መሬቱን የምታርስበትና ዘር የምትዘራበት ጥበብ ነው። አስተሳሰብህን ካሳደግክ፣ ሕይወትህ ማፍራቱ አይቀሬ ነው! 🌱

🔥 የዕለቱ ጥያቄ፦
ዛሬ፣ "አልችልም" ብለህ ትተኸው የነበረ ግን አሁን "ገና አልቻልኩም" ብለህ ዳግም ልትጀምረው የወሰንከው ነገር ምንድነው? 👇 በኮሜንት አጋሩን!

📌 ይህንን ጠቃሚ ትምህርት ለሚወዱት ሰው Share በማድረግ የእድገት አጋር ይሁኑ!

ብርሃናችሁ ይብራ! ✨

የሕይወትንና የስኬት ሚስጥር ለመረዳት፣ የ21 ቀን Dawit Life class ስልጠናችንን ይቀላቀሉ። ለበለጠ መረጃ እና ለመመዝገብ በስልክ ቁጥር +251 938 25 25 25 ይደውሉ።

05/01/2026

🌍 የገና በዓል ታሪክ (ክፍል ፩)፦ ዓለም አቀፋዊ እይታና መሠረተ-ታሪክ

የገና በዓል (Christmas) በዓለም ዙሪያ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የሚያከብሩት ታላቅ ሃይማኖታዊና ባህላዊ በዓል ነው። ይህ በዓል ዛሬ ላለው ገጽታ እንዲበቃ በታሪክ ሂደት ውስጥ ብዙ መንገዶችን አልፏል።

🏷️ ፩. ስያሜው እና ትርጉሙ (The Name)
Christmas: "Christ's Mass" (የክርስቶስ ቅዳሴ) ከሚለው የጥንት እንግሊዝኛ ቃል የመጣ ነው።

Xmas: ብዙ ጊዜ በምህጻረ ቃል "Xmas" የሚባለው "X" የሚለው ፊደል በግሪክ ቋንቋ የክርስቶስ (Christos) መጀመሪያ በመሆኑ ነው።

Nativity: ከላቲን "Natalis" የመጣ ሲሆን "ልደት" ማለት ነው።

⏳ ፪. መቼ እና በማን ተጀመረ? (Origins)
መጀመሪያ፦ በመጀመሪያዎቹ ሁለት መቶ ዓመታት ክርስቲያኖች የክርስቶስን ልደት ሳይሆን ሞቱንና ትንሳኤውን (ፋሲካን) ብቻ ያከብሩ ነበር።

የመጀመሪያው በዓል፦ በታሪክ መዝገቦች ለመጀመሪያ ጊዜ የገና በዓል በሮም መከበር የጀመረው በ336 ዓ.ም (ከክርስቶስ ልደት በኋላ) ነው።

ማን አጸደቀው?፦ በ350 ዓ.ም አካባቢ ፓፓ ጁሊየስ ፩ኛ (Pope Julius I) ታህሳስ 25 የክርስቶስ ልደት በዓል ተብሎ እንዲከበር በይፋ ወሰኑ።

📅 ፫. ቀኑ ለምን ተመረጠ? (Why December 25?)
መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ የተወለደበትን ትክክለኛ ቀን አይገልጽም። ታህሳስ 25 እንዲመረጥ ያደረጉት ምክንያቶች፦

የአረማውያን በዓላትን ለመተካት፦ በሮማውያን ዘንድ "Saturnalia" (የእርሻ አምላክ በዓል) እና የፀሐይ አምላክ ልደት በዚሁ ሰሞን ይከበር ነበር። ቤተክርስቲያን እነዚህን በዓላት በክርስትና ትምህርት ለመተካት ቀኑን መረጠች።

The Winter Solstice: ቀን አጥሮ ሌሊት የሚረዝምበት ወቅት አልፎ ብርሃን የሚበረታበት ወቅት በመሆኑ፣ ክርስቶስም "የዓለም ብርሃን" መሆኑን ለመግለጽ ተመረጠ።

📜 ፬. ሃይማኖታዊና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት (Theological Context)
መጽሐፍ ቅዱስ፦ በማቴዎስ እና በሉቃስ ወንጌል ላይ የልደቱ ታሪክ ተጽፏል። ገብርኤል መልአክ ለማርያም ማብሰሩ፣ የሰብአ ሰገል ስጦታ እና በቤተልሔም በግርግም መወለዱ ዋናዎቹ ናቸው።

ጥንታዊ ጽሑፎች፦ እንደ ሂፖሊተስ (Hippolytus) ያሉ የቀደሙ የቤተክርስቲያን ምሁራን፣ ኢየሱስ የተፀነሰው በመጋቢት (Annunciation) ከሆነ ልደቱ በታህሳስ መሆን አለበት የሚል ስሌት ተጠቅመዋል።

⛪ ፭. በተለያዩ እምነቶች ያለው ወግ (Traditions)
ካቶሊክ (Catholic): በዓሉን በታህሳስ 25 (Dec 25) ያከብራሉ። "Midnight Mass" ወይም የእኩለ ሌሊት ቅዳሴ ትልቁ ስርአታቸው ነው።

ፕሮቴስታንት (Protestant): አብዛኞቹ ታህሳስ 25ን ያከብራሉ። በ17ኛው ክፍለ ዘመን ግን አንዳንድ የፕሮቴስታንት ክፍሎች (Puritans) "በመጽሐፍ ቅዱስ አልታዘዘም" በሚል በዓሉን ከልክለውት ነበር።

ኦርቶዶክስ (Eastern Orthodox): እንደ ኢትዮጵያ፣ ሩሲያ እና ግብፅ ያሉ አገራት የጁሊያን አቆጣጠርን ስለሚከተሉ በዓሉን በጥር 7 (Jan 7) ያከብራሉ።

አይሁዶች (Jews): የክርስቶስን ልደት ባያከብሩም፣ በዚሁ ሰሞን "Hanukkah" (የመቅረዝ በዓል) የተሰኘውን የብርሃን በዓላቸውን ያከብራሉ።

🎄 ፮. የአከባበር ልማዶች (Customs)
የገና ዛፍ፦ መነሻው ጀርመን ሲሆን፣ የማይረግፍ አረንጓዴ ዛፍ የዘላለም ህይወት ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል።

ሳንታ ክላውስ (አባ ገና)፦ በ4ኛው ክፍለ ዘመን ይኖር ከነበረውና በቸርነቱ ከሚታወቀው ቅዱስ ኒቆላዎስ (St. Nicholas) የመጣ ታሪክ ነው።

ስጦታ መለዋወጥ፦ ሰብአ ሰገል ለክርስቶስ ያቀረቡትን ስጦታ በማሰብ የተጀመረ ልማድ ነው።

የገና በዓል ከሮም ቤተ መንግስት እስከ ዛሬው ዘመናዊ አከባበር ድረስ የሺህ ዓመታት ጉዞ አለው። ምንም እንኳን የአከባበር ስርአቱ ቢለያይም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰላምና የፍቅር ምልክት ሆኖ ቀጥሏል።

በክፍል ሁለት፦ የኢትዮጵያ ገና ልዩ ገጽታዎች፣ የገና ጨዋታ ታሪክ እና በኢትዮጵያ አቆጣጠር የታህሳስ 29 ምስጢርን በዝርዝር እንመለከታለን።

05/01/2026

[ ክፍል-1].......➡️ ‼️

" ...እኔ እንደሆንሁ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ....።"
(የዮሐንስ ወንጌል 8:24)
✍✍ ኢየሱስ ማነው??
ይህ ጥያቄ በምድር ላይ የሚኖር ሁሉም ሰው ሊመልሰው የሚገባ ወሳኝ ጥያቄ ነው።
እርሱ ታላቅ የሃይማኖት መምህር ነበር?? ወይንስ አይምእሮውን የሳተ ሰው?? አምላክ ነበር ወይንስ ሰው ብቻ??
የእርሱን ማንነትና ስልጣን በተመለከተ ትልቅ ክርክርና ጭቅጭቅ አለ።

#⃣ታድያ ኢየሱስ ማነው??
#⃣እናንተስ ማን ትሉኛላቹ?? ይላቹሀል!!
/ ማቲ 16-15/

የክርስቶስን ማንነት እና ስራዎች ወደ ማጥናቱ ስንመጣ በክርስቲያናዊ የስነ መለኮት ትምህርት ዋናው እምብርት
ላይ ነው የምንደርሰው። ክርስትናን ልዩ የሚያደርገውም የኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት ነው። አንድ ሰው ስለ ኢየሱስ
ክርስቶስ የሚያስበውን ያህል እጅግ ጠቃሚ የሆነ ምንም ነገር የለም። ከመጽሀፍቅዱስ አወዛጋቢ ከተባሉ ርእሰ
ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት ነው። በተመሳሳይ መንገድም እምነታችን ዋጋ እንዲኖረው
በማድረግም መሠረታዊ ነገር ነው።

ብዙ ሰዎች በመጽሀፍቅዱስ እንመራለን እያሉና ራሳቸውን ክርስቲያን ብለው እየጠሩ ነገር ግን በተለያየ
ትምህርትና እና እምነት ውስጥ ያሉት ጥቂት አይደሉም። የዚህም ዋናው ምክንያት ስለ ኢየሱስ ማንነት ያላቸው
የተዛባ አመለካከት ነው።

ብዙ ሰዎች ኢየሱስን ትህትናን የተሞላ ስነ ምግባርን ያስተማረ ስርአት ላለው ማህበረሰብ ምሳሌ ሊሆን የሚችል ሰው ብቻ አድርገው ያቀርቡታል። አንዳንዶች ደግሞ ኢየሱስን ከእግዚአብሄር መላእክት አንዱ እንደነበር ይናገራሉ ለዛውም ሚካኤልን። እንደዚ እንደዚ አይነት ብዙ የተዛባ አመለካከት ስለ ኢየሱስ ማንነት ቢኖሩም ነገር ግን መጽሀፍ ቅዱስን የሕይወታቸው መመሪያ ያደረጉ ሰዎች የኢየሱስን ትክክለኛ ማንነትና ይህ አይነቶቹ ትምህርቶች ከመጽሀፍቅዱስ የወጡ እንግዳ ትምህርት መሆናቸውን መረዳት አይከብዳቸውም። #ምክንያቱም ይህ መገለጥ የሚጠይቅ እውቀት ነውና። 👇👇
(የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 10)
21፤ በዚያን ሰዓት ኢየሱስ በመንፈስ ቅዱስ ሐሤት አደረገና። የሰማይና የምድር ጌታ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና
ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ
ሆኖአልና። 22፤ ሁሉ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቶኛል፥ ወልድንም ማን እንደ ሆነ ከአብ በቀር የሚያውቅ የለም፥ አብንም ማን እንደ
ሆነ ከወልድ በቀር ወልድም ሊገልጥለት ከሚፈቅድ በቀር የሚያውቅ የለም አለ።

ኢየሱስ ማን እንደሆነ አብ ካልገለጠለት በቀር በራሱ ፍለጋ ጥረትና ምርምር ማወቅ የሚችል ማንም የለም።
ስለዚህም የኢየሱስ ማንነት ራሱ የሚታወቀው አብ በገለጠለት መሠረት ብቻ ነው የሚሆነው። ጌታ ኢየሱስ ስለማንነቱ ሊገልጥላቸው ደቀመዛሙርቱን ፊልጶስ ቂሳርያ ወደ ተባለ አውራጃ ይዞአቸው ሄደ ፣ ይህቦታ የሚገኘው በእስራኤል ሰሜናዊ ጫፍ ሲሆን በጣም ጸጥተኛ በመሆኑም ይታወቃል፤ በዚያ ወቅት ከየአቅጣጫው በኢየሱስ ላይ የሚሰነዘር ተቃውሞ የበረታበት ጊዜ ነበር። ሊያነሳላቸው የፈለገው ርዕሰ ጉዳይ ለእነርሱም ሆነ ለእኛ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነው፣ ምክንያቱም እንደ ደቀመዛሙርቱ ሁሉ እኛም "ኢየሱስ ክርስቶስ ማነው?" ለሚለው ጥያቄ በምንሰጠው መልስ እጅግ በጣም እርግጠኞች መሆን ስላለብን ነው።

"ኢየሱስ ፊልጶስ ቂሳርያ ወደ ተባለው ሀገር በደረሰ ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ለመሆኑ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን
ይሉታል?" ብሎ ጠየቃቸው /ማቲ 16-12/
በዚህ ጊዜ ጌታ የመረጠው "የሰው ልጅ" የተባለውን መጠሪያውን ሲሆን ይህም "ፍጹም ሰውነቱን (ሰብአዊነቱ) የሚያመለክት ነበር። እነርሱም አንዳንዶች መጥምቁ ዩሀንስ ሌሎችም ኤልያስ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነብያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት(ቁ.14)

እንግዲህ በጊዜው ስለኢየሱስ ክርስቶስ ማንነት የተለያየ ሀሳቦች ነበሩ
👉 አንዳንድ መጥምቁ ዩሀንስ
👉 ሌሎቹ ኤልያስ
👉 ሌሎቹ ደሞ ኤርምያስ
👉 ወይም ከነብያት አንዱ የሚል መልስ የሰጡት በዚህ ምክንያት ነበር።
👉 አንዳንዶች "መጥምቁ ዩሀንስ ነው ይላሉ"

እነዚህ ሰዎች ስለኢየሱስ ላይ ላዩን ብቻ እውቀት የነበራቸው ናቸው። ምክንያቱም መጥምቁ ዩሀንስ ከኢየሱስ ጋር በአንድ ዘመን የነበሩ ከመሆንም አልፎ ኢየሱስን ያጠመቀው እርሱ እንደነበረ ይታወቃል /ማቲ 3-13/

ታድያ እንዴት ኢየሱስ መጥምቁ ዩሀንስ ነው ለማለት ቻሉ??
መጥምቁ ዩሀንስ ምንም ተአምር አላደረገም። በአለባበሱም ሆነ በአኗኗሩ ፈጽሞ የተለየ ሰው ነበር /ማቲ 3-4/
ሰዎቹ በዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሱበት ምክንያት ግን ነበራቸው።

⚜ ሁለቱም (ኢየሱስም ፣ መጥምቁ ዩሀንስም) አገልግሎታቸውን የጀመሩት "መንግስተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሀ
ግቡ" በሚል ስብከት ስለነበር ( ማቲ 3-2 ; 4-17)
ሄሮድስም በበኩሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት የተነሳው መጥምቁ ዩሀንስ ሊሆን እንደሚችል አስቦ ነበር። /ማቲ 14-
1/።
የእርሱም ሆነ የእነዚህ ሰዎች ዕውቀትና አመለካከት ላይ ላዩን ብቻ ነበር ማለት ነው።
👉 ሌሎቹ ኤልያስ ነው ይላሉ፦
ኤልያስ ብዙ ተአምራትን በማድረጉ ይታወቃል ይሁን እንጂ እርሱ የፈጸማቸው ተአምራት ጌታ ከፈጸማቸው
የተለዩ ነበሩ። ኤልያስ ያደረጋቸው ብዙዎቹ ተአምራት ሰዎች ላይ የእግዚአብሄርን ቁጣና ፍርድ ለማምጣት የተደረጉ
ሲሆኑ የኢየሱስ ተአምራት ግን ህዝብን ለመባረክ፣ ለማጽናናት ..... ነበር።
በእርግጠኝነት እነዚህ ሰዎች ኢየሱስ ኤልያስ ነው ብለው ያሰቡት ወይም ሊያስቡ የቻሉት በትንቢተ ሚል 4-5 ላይ ከተጻፈው ትንቢት በመነሳት ይመስላል።
እንዲህ ይላል 👇
" እነሆ፥ ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ። "
(ትንቢተ ሚልክያስ 4:5)
ነገር ግን የእነዚህ ሰዎችም ዕውቀት ላይ ላዩን እንደነበር ያስረዳል።
👉 ሌሎቹ ኤርምያስ ነው ይላሉ፦
ኤርምያስና ኢየሱስን የሚያመሳስላቸው ሁለቱም የሀዘንና የልብ ስብራት ሰዎች በመሆናቸው ነው። ኤርምያስ
በተለምዶ "አልቃሻው ነብይ" ይባላል። እርሱ ያዘነው ህዝብ የእግዚአብሄርን ቃል ለመቀበል ባለመፈለጋቸው ነበር።
ጌታ ኢየሱስ ደግሞ ያዘነው ኢየሩሳሌም የጉብኝትዋን ወራት ባለማወቋ ሊያድናቸው የመጣ ህዝብ እርሱን
ባለመቀበሉ ነው።
👉 ሌሎቹ ከነብያት አንዱ ነው ይላሉ።
ለምሳሌ ሙሴ ስለሚመጣው ነብይ በትንቢት አመልክቶ ነበር። /ዘዳ 18-15/ ይንሁ እንጂ ኢየሱስ ከነብያት አንዱ
ሊሆን እንደሚችል እንጂ በስጋ የተገለጠ አምላክ ነው ብለው ጨርሶ አላሰቡም ነበር።
ከሰዎች መካከል ምርጥ ከሚባሉት አንዱ ነው ብለውም ሳያስቡ አልቀሩም።
ማሰባቸው እውነት ነው። ሆኖም ግን የተቀሩት ሁሉ ሰብአዊ ፍጡራን እንጂ በስጋ የተገለጠ አምላክ አይደሉም።
በመሆኑም የኢየሱስ ማንነት መገለጥ የሚጥይቅ እውቀት ነበር።

ጌታ ኢየሱስ በመቀጠል ደቀ መዛሙርቱን እናንተስ እኔ ማን እንደሆንሁ ትላላቹሁ??
አላቸው!!
በተለይ " እናንተስ " ሲል ! ምን ማለቱ ነው??
"እናንተስ" ብሎ ለምን ይጠይቃቸዋል ?? አብረው ናቸው!!
የራቁት እንኳ ስለ እርሱ ጥሩ ግንዛቤ አልነበራቸውም::
የነርሱ መረዳት እሺ ይሁን !
እናንተስ ?
የራቁት የእይታ ችግር አለባቸው! እናንተ ግን ከእይታ ችግር
ወጥታችኃል ! ስለዚህ እናንተስ እኔን ማን እንደሆንኩ ትላላችሁ ?
⚜ እውነት ነው አብሮ እየኖሩ አለመኖር አለ !
⚜ አብሮ እየኖሩ አለመተዋወቅ አለ !
አንዳንድ ባል ወይም ሚስት አሉ አብረው እየኖሩ ምንም የማይተዋወቁ!! ምንም! ማለት ነው። ይገርማል!!
የማንም ማንነት በመንፈሳዊ ብረሀን መፈተሽ አለበት ::
የሁሉም እውቀት በመለኮት እውነት መቃኘት አለበት !
ምክንያቱም በስምህ አድርገናል ተብሎ ከጌታ ዘንድ ዋስትና የለምና :: ስለዚህ እርሱን ማወቅ ይቀድማል !!
ዛሬ ማነው? ከፊታችን ያለውና የምንከተለው ??? ክርስትና የህይወት ለውጥና የሰብዕና
ሸግግር ላይ ያተኮረ ነው ! የእውነት መንገድ ነው ! ለብዙዎች ክርስትና የሀይማኖት ተቋም ከመሆን ያለፈ ትርጉም
የለውም::
እናንተም እንደዛ ናቹ??
አዎ እናንተ አንባቢዎቹ!!
አንድ ደቀ መዝሙር ደግሞ ከሚከተለው መምህር በትክክል ተምሮ እርሱን ለመምሰልና ለለውጥ ራሱን
ማዘጋጀት አለበት:: " ፈፅሞ የተማረ እንደ መምህሩ ይሆናል" ተብሎአልና :: የደቀመዛሙርቱ አብይ የሕይወት መርህ
ጌታን መከተል ! የተከተሉትን ጌታ ማወቅ ! ያወቁትን ጌታ መምሰል ! የመሰሉትን ጌታ መግለጥ ወይም ስለ እርሱ
መመስከር ነው !

ዛሬ የሚሰብኩ የሚሰብኳቸውን የሚዘምሩ የሚሰሟቸውን መሪዎች የሚመሩትን መንጋ የሚያስተምሩ
ተማሪዎቻቸውን ጌታ ደቀመዝሙርቱን የጠየቀውን ጥያቄ ለመጠየቅ ይደፍራሉን?? ለምን ? ደግሞስ ጌታ ጥያቄው
ለኛስ ቢሆን ኖሮ ምላሻችን ምን ይሆን ነበር??
ወደ መለኮት መገለጥ እውነት ገና አልገባንም በምድር በሆኑልንና ባልሆኑልን ነገሮች ብቻ ንፅፅር ይዘናል ! አልያም
ስላላወቅነው ስለ ጌታ መናገር አንችልም ! እርሱን ሳያውቁ መናገር እንደሰዎቹ መላ ምት ነው የሚሆነው ! ብዙዎች
ስለ ጌታ የሚናገሩት አውቀውት ሳይሆን ከትሩፋቶቻቸው ተነስተው ነው !
እንዲህ ስላደረገልኝ እንዲህ ብዬዋለሁ !
ይህ ደግሞ እስከተከናወነልን ብቻ የሚቀጥል ነው !
ስንለብስ አልባሼ
ብንራቆትስ ??
ሁሉ ሲተረፈረፍ ሁሉንም ነህ !
ሁሉ ቢጠፋስ ??
ሰላም ስናገኝ ሰላሜ ! ሰላም ባይኖርስ ?
መልሶቻችን ብዙ ጊዜ በአኗኗራችን ላይ ይንፀባረቃሉ ! ሰው ሁሉ የራሱን ቲኦሎጂ(Theology) እየፈበረከ ባለበት
ዘመን የኛ እውቀት በእውነተኛው መለኮታዊ ብረሀን መፈተሽ የለበትም ትላላችሁ ??
በእውነት ራሳቹን እየጠየቃቹ ሂዱ??
ኢየሱስ ከጊዚያዊ ችግር ጋር የሚነጻጸር ነው??
የቀረበው ጥያቄ ጌታን የማወቅ ጥያቄ ነው !! የደቀ መዛሙርቱም ሆነ የሕዝቡ እውቀት የተፈተሸበት ነው!! ወደ
መለኮታዊ ሰብእና የማያቀርብና ለለውጥ ያልሆነ የራስ ፍልስፍና ዋጋ የለውም ! ኢየሱስ ክርስቶስ ማን መሆኑን
ማወቅ ከዘላለም ህይወት ጋር የሚገናኝበት ታላቅ ሚስጥር አለው !! 👇👇👇
👉 " እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት
ናት።"

(የዮሐንስ 17:-3)ተብሎ ተፅፎአል
የኢየሱስ ክርስቶስን ማንነት ለማወቅ እርሱ ራሱ ስለ ራሱ የተናገረውን እና የመለኮት መገለጥ የተገናኛቸው
አብረውት የነበሩ ከርሱ የሰሙ የዳሰሱት ተከታዮቹ ስለ እርሱ ያስተማሩትን ከማወቅ የበለጠ ስለ እርሱ ማንነት
ሊነግርህ የሚችል ማንም የለም!
ኢየሱስን ደቀመዛሙርቱን ያን ጥያቄ በጠየቀ ጊዜ ትክክለኛውን መልስ የሰጠው ጴጥሮስ ብቻ ነበር።

እሱም፦ "አንተ ክርስቶስ የእግዚአብሄር ልጅ ነህ" በማለት ነበር።
ጌታም፦ በሰማይ ያለው አባቴ እንጂ ስጋና ደም ይህን አልገለጠለህምና ብፁዕ ነህ አለው።
ለምን? ስንል ይህ እውቀት በመገለጥ ካልሆነ በቀር ስለማይገኝ ነው።
👇👇👇

እግዚአብሔር አብም የኢየሱስን ማንነት መግለጥ ያስፈለገው ከእርሱ በቀር የወልድን ማለትም የኢየሱስን ማንነት
የሚያውቅ ማንም ስለሌለ ነው።

ስለዚህ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ የተገለጠው በእግዚአብሔር አብ ነው ማለት ነው።
እግዚአብሔር አብ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው በማለት ወልድ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን
የመሰከረው በዚህ ምክንያት ነው።

ጌታ ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዩሐንስን ይዞ በተራራ ላይ እየጸለየ እያለ ሙሴና ኤልያስ በተገለጡ ጊዜ፤
(የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 17)
3፤ እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።
4፤ ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን። ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን
ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።
5፤ እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ
ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።
ይህ ስለ ኢየሱስ የመሰከረው የእግዚአብሄር አብ ምስክርነት ነው። ከዚህ ቡሀላ ነው ጴጥሮስ፦

(2ኛ ጴጥ- 1)
----------
16፤ የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ሳንከተል የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና
መምጣት አስታወቅናችሁ።
17፤ ከገናናው ክብር። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር
አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና፤
18፤ እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን። በማለት በድፍረት ስለ ኢየሱስ ማንነት መናገር የቻለው። መገለጡም የመጣለት ለእርሱ ብቻ ሳይሆን ከእርሱ ጋር
አብረው ለነበሩ ለዩሐንስና ለያዕቆብ ስለ ነበረ በተራራው ላይ የነበረውን ሁኔታ "እኛ" በማለት ገልጾታል።

ኢየሱስ የእግዚአብሄር ልጅ ነው ተብሎ የተሰበከውም እግዚአብሔር የጌታ የኢየሱስን ማንነት ለሰዎች በመግለጡ
ነው። ያም መገለጥ ነው ለእግዚአብሄር ሕዝብ እምነት የመሠረት ድንጋይ የሆነው።

ሀዋሪያው ዩሀንስ ራሱ ወንጌሉን ለምን እንደጻፈው ሲናገር👇👇
👉 " ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት
ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።
(የዮሐንስ ወንጌል 20:31)
እንዲሁ በመልክቱ ላይ በብዛት የገለጸው ይህንኑ ነበር 👇
👉 " ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም
በእግዚአብሔር ይኖራል።"
(1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4:15)
👉 (1ኛ የዮሐንስ መልእክት ምዕራፍ 5)
----------
4፤ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው።
5፤ ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው?
ልክ እንደዚሁ ደግሞ አብንም ማን እንደሆነ ከወልድ በቀር የሚያቅ የለም። ስለዚህ ሰዎች የአብንም ማንነት
ለመረዳት የሚችሉት ልክ እንደዚሁ ወልድ በገለጠላቸው መሠረት ብቻ ነው። ለዛ ነው ፦
" መቼም ቢሆን እግዚአብሔርን ያየው አንድ ስንኳ የለም፤ በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ እርሱ ተረከው።"(ዩሀ 1:18)
ያለው።

ስለሆነም ኢየሱስ ከሰው ወይም ከመለአክ ያልበለጠ ከሆነ እምነታችን ችግር ላይ ይወድቃል። ምክንያቱም
እምነታችን በእውነቱ ኢየሱስ በስጋ የተገለጠ አምላክ በመሆኑ ላይ ያረፈ ነው። ትክክለኛው መገለጥም ይህ ነውና።
ሲ ኤስ ሌዊስ የተሰኘው ዝነኛው የእንግሊዝ ጸሐፊና ፈላስፋ ስለ ኢየሱስ እንዲህ ብሎ ነበር፡-
“እንደ ሞኝ ሰው ቆጥራችሁት ዝም ልታሰኙትና እንደ ክፉ ጋኔን ቆጥራችሁ ልትገድሉት ትችላላችሁ ይህ ካልሆነ ግን
በእግሮቹ ስር ተንበርክካችሁ ጌታዬና አምላኬ ብላችሁ ልትጠሩት ይገባል፡፡

ነገር ግን ታላቅ የሆነ ሰብዓዊ መምህር ብቻ ነበር የሚለውን የቂላቂል ንግግር አንናገር፡፡ ያንን አማራጭ እንድንይዝ
ምንም ክፍተት አልተወልንም፡፡ በጭራሽ አላሰበውም፡፡”

እውነታው ኢየሱስ አምላክ መሆኑ ነው፡፡ የስህተት ትምህርቶችን የመለያ ጥሩ መንገድ ስለ ኢየሱስ ምን
እንደሚያስተምሩ መመርመር ነው፡፡ ኑፋቄዎችና ሐሰተኛ አብያተ ክርስቲያናት በአጠቃላይ የክርስቶስን አምላክነት
ይክዳሉ፡፡ ለክርስቲያኖች ስለ ኢየሱስ የምናምነው ነገር ደህንነታችንን ይወስናል፡፡ ስለ እርሱ ያለን ዕውቀት ስለ
እግዚአብሔር ባሕርይና ዓላማ ያለንን መረዳት እንዲሁም ከእርሱ ጋር ያለንን ግንኙነት ይወስናል፡፡

ሰዎች ማንነቱን በተመለከተ ግራ ቢጋቡም እውነተኛ ተከታዮቹ እንደሚያውቁትና እርሱም እንደሚያውቃቸው
ኢየሱስ ተናግሯል (ማቴ. 7፡21-23)፡፡
ግን ግን የአዋቂዎች የሕዝቡ መሪዎች እውቀት ስለ ጌታ በሆነ እውቀት በመለኮታዊ በመለኮታዊ ብረሀን ተፈትሾ
የወደቀው ለምንድነው ???
ስለ ሶስት አይነት እውቀት እንመልከት !
1ኛ ⚜ የአዕምሮ እውቀት :- ይህ ከመማር መረጃ ከመሰብሰብ የሚገኝ ዕውቀት ነው በዚህ ዕውቀት ሰዎች ከተለያዩ
ትምህርት ቤቶች እና ኮሌጆች በተለያየ የትምህርት ደረጃ ይመረቃሉ ይህየረጅም ለማወቅ
ያስችል ይሆን ? በፍፁም መላ ከመስጠትና የቃሉን ፊደል ከማንበብያለፈ ስለ ጌታ እውቀት ሊሰጥ አይችልም።

2ኛ ⚜ የልምድ ዕውቀት :-ይህ እውቀት ከመተግበር ይገኛል ! ሰዎች በዕለት ተዕለት ተግባራዊ ልምሞዶቻቸው
የሚጎናፀፉት ዕውቀት ነው ! ይህ የረጅም ዕድሜ ልምምድ የጌታን ማንነት ወደ ማወቅ ያደርሳቸው ይሆን ?
በፍፁም እድሜ ጠገብ ፈሪሳውያን እንኳ የሀይማኖትን ሥረዓት ከመጠበቅና ከማስጠበቅ ባለፈ የጌታን ማንነት ዕውቀት
ሊጎናፀፉት አልቻሉም! እንግዲህ ዛሬ ቤተክርስቲያን የምትኩራራው ከነዚህ የዕውቀት ማዕከላት የተገኙትን ሙሁራን
ዶክተሮች ሊቃውንት አሉኝ ብላ ነው ! እነርሱ ራሳቸው ጌታን አውቀው ጌታን ወደማወቅ ይመሯት ይሆን በፍፁም !
የግድ በሶስተኛው ላይ ካለው የእውቀት ማዕከል ጋር መገናኘት አለባቸው።

3ኛ ⚜ የመገለጥ ዕውቀት :-
ይህ ማንበብም መጻፍም የማይችለውን
ሐዋርያው ጴጥሮስን የተገናኘ ከመለኮት የዕውቀት ማዕከል የሚገኝ
አስደናቂ ዕውቀት ነው ! የጠርሴስ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ የሆነውን ሐዋርያው ጳውሎሶን በደማስቆ መንገድ የተገናኘ
የመገለጥ ዕውቀት ነው።
1ኛና⚜ እናንተስ ከየትኛው የዕውቀት ማዕከል ጋር ተገናኝታችኃል ???
2ኛ⚜ ጌታንስ የምታውቁት በመላ ምት ወይስ የልቦናዎቻችሁ አይኖች በርተው
አያችሁት ???

3ኛ⚜ እናንተስ ጌታን ማን ትሉታላችሁ??? የዕውቀታችሁስ ምንጭ የትኛው የትምህርት ማዕከል ነው ??? ስለ ጌታ
ያላችሁ እውቀት በመለኮታዊ ብረሀን ይፈተሽ ! ያኔ እንደ ሳውል( ጳውሎስ) በታላቅ ፍረሀትና መንቀጥቀጥ ምን
አደርግ ዘንድ ትወዳለህ ትላላችሁ !!!
ስለዚህ የኢየሱስን ማንነት ጠንቅቆ መረዳት በእጅጉ አስፈላጊ ነው፡፡
እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ራሱን ስለገለጠልን ስለ ኢየሱስ ለማወቅ ዋነኛ ምንጫችን እርሱ ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ የሚናገረው ነገር ብዙ ጎን ያለው ምስል ይሰጠናል፡፡ ኢየሱስ ስለ ራሱ የተናገረውንና
ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሐፊያን የተናገሩትን በማየት የበለጠ ልናውቀው እንችላለን።

ይቀጥላል........✍️✍️✍️



Christ Centered Missionaries Gospel Ministry

Address

Addis Ababa
WWSERNVANT

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Servant Adisu ute posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share