17/05/2026
ከ1950ዎቹ ወዲህ ባለው ታሪክ፣ በተለያዩ አገራት የመንፈስ ቅዱስን ስጦታዎችና መለኮታዊ እንቅስቃሴዎች በመቃወም የወጡ ይፋዊ መግለጫዎች በአብያተ ክርስቲያናት ላይ ያስከተሏቸው ዋና ዋና ተጽዕኖዎች የሚከተሉት ናቸው፦
🔖ከፍተኛ የአባላት ፍልሰትና የቁጥር ማሽቆልቆል፦ መግለጫዎቹ ታሪካውያን አብያተ ክርስቲያናት አባላቶቻቸውን እንዲያጡ ሲያደርጉ፤ በተቃራኒው የጴንጤቆስጤና የካሪዝማቲክ አብያተ ክርስቲያናት በከፍተኛ ፍጥነትና በስፋት እንዲያድጉ ምቹ ሁኔታን ፈጥረዋል።
🔖የውስጥ መከፋፈልና መዋቅራዊ ቀውስ (Internal Schisms)፦ እነዚህ የተቃውሞ መግለጫዎች በቤተ ክርስቲያን መሪዎችና በምሁራን፣ በመሪዎችና በወጣቶች፣ እንዲሁም በመጋቢዎችና በምዕመናን መካከል ጥልቅ መከፋፈልን አስከትለዋል። ይህም አልፎ ተርፎ ምዕመናን ከዋናው መዋቅር በመውጣት የራሳቸውን አጥቢያዎች እንዲመሰርቱ በር ከፍቷል።
🔖የወጣቶች ተሳትፎ መዳከምና የትውልድ ክፍተት (Generational Gap)፦ የዘመኑን መንፈሳዊ መነቃቃትና የአምልኮ አገላለጽ የናፈቁ ወጣቶች ተገፊ በመሆናቸው፣ በቤተ ክርስቲያንና በትውልዱ መካከል የማይታረቅ የትውልድ ክፍተት ተፈጥሯል።
🔖የስነ-መለኮት ቀውስና የብቃት ጥያቄ (Theological Dilemma)፦ ንቅናቄውን ለመግታት የተደረጉ ጥረቶች አዳዲስና አድካሚ ለሆኑ የስነ-መለኮት ክርክሮች በር የከፈቱ ሲሆን፣ የቤተ ክርስቲያናትን መንፈሳዊ ብቃትና የወቅቱን ጥያቄ እና የመንፈስ ቅዱስ እንቅስቃሴን በስነ መለኮት እይታ የመመለስ አቅም ጥያቄ ውስጥ ጥለውታል።
🔖የታላቁን ተልዕኮ መዳከም (Loss of Missional Impact)፦ አብያተ ክርስቲያናት ወንጌልን ለዓለም የማድረስ ቀዳሚ ተግባራቸውን ትተው፣ በውስጥ ግጭት አፈታት እንዲጠመዱና ይባስ ብሎም ወደ ስጋዊ አሰራርና አምባገነንነት እንዲዘፈቁ አድርጓቸዋል።
ጨከን ብለን ከታሪክ ብንማር፦ ይህ ተግዳሮት ከጊዜ በኋላ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት አቋማቸውን እንዲያለዝቡና ከመቃወም ይልቅ ወደ ውስጣዊ የቤት ሥራቸውና መታደስ ላይ እንዲያተኩሩ አስገድዷቸዋል።
ዋና ስጋቴ በእኛ ሀገር አውድ ተቃውሞም ያለ ጥናትና ያለ ጥንቃቄ፣ በዚሁ በመግለጫ ብቻ የኮነነ አካሄድ የሚቀጥል ከሆነ፤ ነገ ለቁጥር የሚያዳግትና ከቁጥጥር ውጪ የሆነ መጠነ-ሰፊ ቀውስ መፈልፈሉ አይቀሬ ነው።
የእናተው ወንድም አሊ
የጴንጤቆስጤ እንቅስቃሴ ውስጥ ነው ያደኩት።
ክብር ለኢየሱስ ይሁን።