ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን - Semien Full Gospel Local Church

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን - Semien Full Gospel Local Church

ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን - Semien Full Gospel Local Church “ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።”
— ዕብራውያን 13፥8 In those successive years the revival broke throughout the country.

The Ethiopian Full Gospel Believers' Church emerged out of the spontaneous gospel revival among students of high school and higher institutions in various parts of the country by the mid 1960s. Since then, the revival inundated the whole country the provincial towns, small towns and villages in the countryside. The church officially founded in 1966 at Addis Ababa. However the movement was not only

limited in Addis Ababa rather it covers the whole country. This brought the issue that the believers had to form unity on a national level and be organized as a denomination. In 1974, leaders from different places of the country came and agreed to be organized at a denominational level. Organizing the denomination had many advantages; among those are that it enabled to guard against false teaching/heresy/ and the other was to obtain recognition by the government and other denominations. Besides these, the unity had contributed in holding common understanding of doctrine, as well the believers were able to encourage and help one another during years of hardship. With the change of the government in Ethiopia came new chapter of the church. The national office of the church is established in Addis Ababa and the Federal Democratic Republic of Ethiopia accorded the church its full recognition on November 10, 1991 in accordance with the constitutional provision of the religious liberty and freedom of worship. Now a days the Church is one of few big evangelical Churches in the country. It consists of more than 3093 local churches and 8000 fellowships divided into 38 regions .

ማስታወቂያ ሰላም ቅዱሳን የቤተክርስቲያናችን አባላትና አገልጋዮች ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ እና ሰላም በያላችሁበት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። በሚመጣው እሮብ በካላን...
22/05/2026

ማስታወቂያ

ሰላም ቅዱሳን የቤተክርስቲያናችን አባላትና አገልጋዮች ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ እና ሰላም በያላችሁበት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። በሚመጣው እሮብ በካላንደር ዝግ ስለሆነና በእለቱ ትምህርትም ሆነ ስራ የማይኖር ስለሆነ የቤተክርስቲይናችን ወጣቶችና አባላት ሁሉ በእለቱ በመገኘት እግዚአብሔርን አብረን እናምልክ ይላሉ የወጣት አገልግሎት ዘርፍ አስተባባሪዎ።

🗓 እሮብ ግንቦት 19/ 2018 አ.ም

🕘 10:30 ሰአት ጀምሮ

📍ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን

🎙የቤተክርስቲያናችን ዘማሪት አናን

🎙ፓስትር ዳዊት

🎙ዘማሪ ሮሆቦት

🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹

⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️

Our Social Links🔗
Click here to Join 👇

YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

20/05/2026
"ለዚህ ምክንያት፥ እሳት እንደሚያቀጣጥል ሰው፥ እጆቼን በመጫኔ በአንተ ያለውን የእግዚአብሔርን ስጦታ እንድታነሣሣ አሳስብሃለሁ።"2 ጢሞቴዎስ 1:6ሰላም የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ የፊታችን...
18/05/2026

"ለዚህ ምክንያት፥ እሳት እንደሚያቀጣጥል ሰው፥ እጆቼን በመጫኔ በአንተ ያለውን የእግዚአብሔርን ስጦታ እንድታነሣሣ አሳስብሃለሁ።"
2 ጢሞቴዎስ 1:6

ሰላም የጌታ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ የፊታችን
🗓እሮብ ግንቦት 5 ቀን 2018 በቤተክርስቲያናችን በሚካሄደው ቆሚ የእሮብ የወጣቶች ፕሮግራም ላይ የቤተክርስቲያናችን መሪዎችና አገልጋዮች ለሁሉም ሰው እጅ በመጫን የሚጸልዩ ስለሆነ እናንተም በዚህ ቀን በመገኘት ከዚህ መልካም ክርስቲያናዊ ከሆነው ስርአት እንድትካፈሉ እናሳስባለን።

የወጣት የአገልግሎት ዘርፍ

ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን||Semen Full Gospel Believers Church (SFGBC)

📍 አድራሻ፦ ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን (ከሰሜን ሆቴል ፊት ለፊት)

YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

📍 Location: Semen Full Gospel Believers Church (In front of Semen Hotel)

2/09/2018ዶ/ር ዘለላው እርዳው                                        ብድራትን መመልከት፨ እምነት ማለት በእግዚአብሔር ላይ መደገፍ ማለት ነውዕብራውያን 10:19-...
15/05/2026

2/09/2018
ዶ/ር ዘለላው እርዳው

ብድራትን መመልከት

፨ እምነት ማለት በእግዚአብሔር ላይ መደገፍ ማለት ነው

ዕብራውያን 10:19-39
19-20 እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን፥
21 በእግዚአብሔርም ቤት ላይ የሆነ ታላቅ ካህን ስላለን፥
22 ከክፉ ሕሊና ለመንጻት ልባችንን ተረጭተን ሰውነታችንንም በጥሩ ውኃ ታጥበን በተረዳንበት እምነት በቅን ልብ እንቅረብ፤
23 የተስፋን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ፤
24 ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤
25 በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።
26 የእውነትን እውቀት ከተቀበልን በኋላ ወደን ኃጢአት ብናደርግ ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ኃጢአት መሥዋዕት አይቀርልንምና፥
27 የሚያስፈራ ግን የፍርድ መጠበቅ ተቃዋሚዎችንም ሊበላ ያለው የእሳት ብርታት አለ።
28 የሙሴን ሕግ የናቀ ሰው ሁለት ወይም ሦስት ቢመሰክሩበት ያለ ርኅራኄ ይሞታል፤
29 የእግዚአብሔርን ልጅ የረገጠ ያንንም የተቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እንደ ርኵስ ነገር የቆጠረ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋ፥ እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው ይመስላችኋል?
30 በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ፡ ያለውን እናውቃለንና፤ ደግሞም፦ “ጌታ በሕዝቡ ይፈርዳል።”
31 በሕያው እግዚአብሔር እጅ መውደቅ የሚያስፈራ ነው።
32-33 ነገር ግን ግማሽ በነቀፋና በጭንቅ እንደ መጫወቻ ስለ ሆናችሁ ግማሽም እንዲህ ካሉት ጋር ስለ ተካፈላችሁ፥ ብርሃን ከበራላችሁ በኋላ መከራ በሆነበት በትልቅ ተጋድሎ የጸናችሁበትን የቀደመውን ዘመን አስቡ።
34 የሚበልጥና ለዘወትር የሚኖር ገንዘብ በሰማይ ራሳችሁ እንዳላችሁ አውቃችሁ፥ በእስራቴ ራራችሁልኝ የገንዘባችሁንም ንጥቂያ በደስታ ተቀበላችሁ።
35 እንግዲህ ታላቅ ብድራት ያለውን ድፍረታችሁን አትጣሉ።
36 የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርጋችሁ የተሰጣችሁን የተስፋ ቃል እንድታገኙ መጽናት ያስፈልጋችኋልና።
37 ገና በጣም ጥቂት ጊዜ ነው፥ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም፤
38 ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም።
39 እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም።

• በእምነት ፀንተው በወንጌል እውነት ይኖሩ የነበሩ ነገር ግን አሁን ላይ የተናወጡ ይመስላሉ።
• ስለዚህም የቀድሞ ድፍረታቸውን (የእምነት ጭካኔያቸውን) መለሰው እንዲያነሱት ምክንያቱም ብድራት ስላለው።
• እግዚአብሔር ብድራትን ይመልሳል ስለዚ አለማፈግፈግ ያስፈልጋል።

ዕብራውያን 11:32-38
32 እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶንም ስለ ዮፍታሔም ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና።
33 እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ፥ ጽድቅን አደረጉ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ፥
34 የአንበሶችን አፍ ዘጉ፥ የእሳትን ኃይል አጠፉ፥ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፥ ከድካማቸው በረቱ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ።
35 ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤
36 ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤
37 በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤
38 ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።

• የእምነት አባቶች ብዙ ናቸው ነገር ግን የሚያመሳስላቸ፦
• በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ፥ ጽድቅን አደረጉ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ፥የአንበሶችን አፍ ዘጉ፥ የእሳትን ኃይል አጠፉ፥ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፥ ከድካማቸው በረቱ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ ይህ ነው።

ዕብራውያን 11:24-28
24 ሙሴ ካደገ በኋላ የፈርዖን የልጅ ልጅ እንዳይባል በእምነት እምቢ አለ፤
25-26 ከግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ፤ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።
27 የንጉሡን ቍጣ ሳይፈራ የግብፅን አገር የተወው በእምነት ነበር፤ የማይታየውን እንደሚያየው አድርጎ ጸንቶአልና።
28 አጥፊው የበኵሮችን ልጆች እንዳይነካ ፋሲካንና ደምን መርጨትን በእምነት አደረገ።

• በልጅነት የሚወሰን ውሳኔ ሀላፊነት አይሰጥም።
• ሙሴ ከሁለቱ ህይወቱ የፅድቁን መረጠ።

፨ ሙሴ

1, በእምነት
በእምነት እምቢ አለ።
የግብፅን አገር የተወው በእምነት ነበር።
ፋሲካንና ደምን መርጨትን በእምነት አደረገ።

2, አስቦልና
ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና።

3, ተመልክቷል
ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።

4, ፀንቷል
የማይታየውን እንደሚያየው አድርጎ ጸንቶአልና።

ቲቶ 2:11-13
11 ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
12-13 ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤

25/08/2018ፓስተር ጌታዬ ደሳለኝ                        እሳት የገለጠው ውበት1 ጴጥሮስ 1:6-76-7 በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋ...
05/05/2026

25/08/2018
ፓስተር ጌታዬ ደሳለኝ

እሳት የገለጠው ውበት

1 ጴጥሮስ 1:6-7
6-7 በዚህም እጅግ ደስ ይላችኋል፥ ነገር ግን በእሳት ምንም ቢፈተን ከሚጠፋው ወርቅ ይልቅ አብልጦ የሚከብር የተፈተነ እምነታችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ፥ ለምስጋናና ለክብር ለውዳሴም ይገኝ ዘንድ አሁን ለጥቂት ጊዜ ቢያስፈልግ በልዩ ልዩ ፈተና አዝናችኋል።

• የወርቅ የመከራ ጊዜ ማለት በእሳት የሚገባበት ጊዜ ነው።
• ነወርቅ መልካም ጊዜ ማለት አሁንም በእሳት የሚገባበት ጊዜ ነው ምክንያቱም አፈርም ሆነ ሌላ የማይገቡ ነገሮች ከላዩ ስለሚነሱ ነው።

፨ የመከራ ቀንን ከባድ የሚያደርገው
1, በመተው ሸሎቆ ውስጥ ስለሚያሳልፍ
• አባት ሆይ ስለምን ተውከኝ ብሎ ኢየሱስ እስኪጠይቅ ድረስ የመተው ስሜት ተሰምቶት ነበር።
2, የመከራ ማብራሪያ ስለማይሰጥ
• የኢዮብ ህይወት
3, አጃቢ እና ከባቢ ስለሚበተን
• በፊተኛው ሙግቴ አንድ ስንኳ አልደረሰልኝም፥ ሁሉም ተዉኝ እንጂ፤ ይህንም አይቍጠርባቸው፤ (2 ጢሞቴዎስ 4:16)
4, ሰይጣን ያሸነፈ ስለሚመስል
• የእግዚአብሔርን መኖር ስለሚያጠራጥር።

፨ እምነት ከመከራ ማውጣት ብቻ ሳይሆን በመከራም ውስጥ ያፀናል።

18/8/2018ፓስተር መርሐዊ ንጉሤለድሆች መኖሮገላትያ 2:10ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ። ፨ መሰጠት/መስጠት• ከፍቅር የተለየ እንዳልሆነ እና ለምንሰጠው...
29/04/2026

18/8/2018

ፓስተር መርሐዊ ንጉሤ

ለድሆች መኖሮ

ገላትያ 2:10
ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ።

፨ መሰጠት/መስጠት
• ከፍቅር የተለየ እንዳልሆነ እና ለምንሰጠው ሰው ፍቅር ሊኖረን ይገባል።
• እግዚአብሔርንም እንወድ ዘንድ ግድ ነው።

2 ቆሮንቶስ 8:5
አስቀድመውም በእግዚአብሔር ፈቃድ ራሳቸውን ለጌታ ለእኛም ሰጡ እንጂ እንዳሰብን አይደለም።

• አስቀድመን ለእግዚአብሔር ህወታችንን መስጠት አለብን።
• ከዛም ለድሆች አንደርሳለን።

ዘዳግም 12:17
የእህልህን የወይን ጠጅህን የዘይትህንም አሥራት፥ የላምህንና የበግህንም በኩራት፥ የተሳልኸውንም ስእለት ሁሉ፥ በፈቃድህም ያቀረብኸውን፥ በእጅህም ያነሣኸውን ቍርባን በደጆችህ ውስጥ መብላት አትችልም።

• ብዙ ስጦታዎች አሉ
1. በኩራት (ለእግዚአብሔር ቤት ሲሆን ከሚገኘው የመጀመሪያ ወይም የበኩር መስጠት ማለት ነው።)
2. አስራት (በየጊዜው ከምናገኘው ገቢ አንድ አስረኛውን ለእግዚአብሔር ቤት መስጠት ማለት ነው።)
3. ስእለት (ለእግዚአብሔር በየሆነ ጊዜ ይህን አደርጋለሁ ተብሎ የሚገባ ቃል ማለት ነው።)
4. ምፅዋት (ለድሆች ማካፈል ማለት ነው።)

፨ ምፅዋት
• ከፍሎ ሰጠ ማለት ነው።
• ድሆች ከምድሪቱ ላይ አያልቁምና ስለዚህ እኔ፦ በአገርህ ውስጥ ላለው ድሀ ለተቸገረውም ወንድምህ እጅህን ትከፍታለህ፡ ብዬ አዝዝሃለሁ። (ዘዳግም 15:11)
• ድሆች ሁል ጊዜም አሉ።
• የወይንህንም ቃርሚያ አትቃርም፥ የወደቀውንም የወይንህን ፍሬ አትሰብስብ፤ ለድሆችና ለእንግዶች ተወው፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ።(ዘሌዋውያን 19:10)
• ሁሉን አትውሰዱ አንዳንድ ለድሆች ተዉላቸው።
• የመሲሑ መምጣት ለድሆች የምስራች ነው።
• ወንጌል ህይወት ለከበዳቸው ነው።
• ዕውሮች ያያሉ አንካሶችም ይሄዳሉ፥ ለምጻሞችም ይነጻሉ ደንቆሮችም ይሰማሉ፥ ሙታንም ይነሣሉ ለድሆችም ወንጌል ይሰበካል፤ (ማቴዎስ 11:5)
• ለድሆች ወንጌልን መስበክ የቤተክርስቲያን ግዴታ ነው።
• ድህነት በገንዘብ ብቻ ሳይሆን በአስተዳደግ እና በአመለካከት ጭምር ነው።

2 ቆሮንቶስ 9:11-12
11 ሁልጊዜ በልግስና መስጠት እንድትችሉ በሁሉ ነገር ያበለጽጋችኋል፤ ልግስናችሁም በእኛ በኩል የሚደርሳቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ለማመስገን ምክንያት ይሆናቸዋል።
12 ይህ የምትሰጡት አገልግሎት የቅዱሳንን ጕድለት የሚያሟላ ብቻ ሳይሆን፣ ብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር የሚቀርብበት ነው።

20/04/2026
11/08/2018      ነብይ ግዛው                      አስተማማኝ ዋስትና መዝሙር 46:1-111 አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን፣  በሚደርስብን መከራ ሁሉ የቅርብ ረዳታችን ...
20/04/2026

11/08/2018
ነብይ ግዛው

አስተማማኝ ዋስትና

መዝሙር 46:1-11
1 አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን፣
በሚደርስብን መከራ ሁሉ የቅርብ ረዳታችን ነው።
2 ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ እንኳ፣
ተራሮችም ወደ ባሕር ጥልቅ ቢሰምጡ አንፈራም።
3 ውሆች ቢያስገመግሙ፣ ዐረፋ ቢደፍቁም፣ ተራሮችም ከውሆቹ ሙላት የተነሣ
ቢንቀጠቀጡም አንደናገጥም። ሴላ
4 የእግዚአብሔርን ከተማ፣
የልዑልን የተቀደሰ ማደሪያ ደስ የሚያሰኙ የወንዝ ፈሳሾች አሉ።
5 እግዚአብሔር በመካከሏ ነው፤ አትናወጥም፤
አምላክ በማለዳ ይረዳታል።
6 ሕዝቦች በዐመፅ ተነሡ፤ መንግሥታትም ወደቁ፤
ድምፁን ከፍ አድርጎ አሰማ፤ ምድርም ቀለጠች።
7 የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤
የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ
8 ኑና የእግዚአብሔርን ሥራ፣
ምድርንም እንዴት ባድማ እንዳደረጋት እዩ።
9 ከዳር እስከ ዳር ጦርነትን ከምድር ያስወግዳል፤
ቀስትን ይሰብራል፤ ጦርን ያነክታል፤
ጋሻንም በእሳት ያቃጥላል።
10 “ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ፤
በሕዝቦች ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፤
በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።”
11 የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤
የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

• አስተማማኝ ዋስትና ስለኛ ሙሉ ሀላፊነት ይወስዳል።
• እግዚአብሔር የማይለው ታማኝ አምላክ መሆኑ አስተማማኝ ዋስትና ማሳያ ነው።
• አቅም ሳይኖረን የቅርብ ረዳታችን መሆኑ የአስተማማኝ ዋስተና ማሳያ ነው።
• ሁሉን እግዚአብሔር ይቆጣጠራል ስለዚህ ዋስትናችን ነው።
• የያዕቆብ አምላክ መጠጊያ ነው።
• ይህ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር አለ።
• እግዚአብሔር በችግር ውስጥ ከአብሮነቱ ጋር ያኖረናል።
• ማኖር ብቻ ሳይሆን በችግር ውስጥ ሆነን ለሌሎች መፍትሄ ያደርገል።
• አስተማማኝ ዋስትና የማይለወጥ የእግዚአብሔር ፍቅር ነው።
• ሁሉን የሚቆጣጠር አምላክ ስላለን ልናርፍ ይገባናል።

የቤተክርስቲያችን ወንጌላዊ አየሁብርሀን ጓዴበዛሬው እለት ሚያዚያ 9, 2018 ዓ.ም  ወደ አገለገለውና ወደሚወደው ጌታ ስለሄደ የወንጌላዊ አየሁብርሀን ጓዴ የስንብት መርሀግብር አፈፃፀም የስን...
17/04/2026

የቤተክርስቲያችን ወንጌላዊ አየሁብርሀን ጓዴ
በዛሬው እለት ሚያዚያ 9, 2018 ዓ.ም ወደ አገለገለውና ወደሚወደው ጌታ ስለሄደ

የወንጌላዊ አየሁብርሀን ጓዴ የስንብት መርሀግብር አፈፃፀም

የስንብት መርሃ ግብር ቀን - ሚያዚያ 10, 2018 ዓ.ም ቦታ - በኢትዮጵያ መሉ ወንጌል ሰሜን አጥቢያ ቤተክርስቲያን

ከጠዋቱ -5:00 ሰዓት ጀምሮ ጉዞ ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ ሰሜን አጥቢያ ቤተክርስቲያን ይደረጋል

ከ7፡00 ሰዓት ጀምሮ በሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን የስንብት ፕሮግራም ይደረጋል

ከቀኑ 8፡00 ሰዓት አስክሬኑ ወደ መጨረሻ ማረፊያው ጉዞ ይጀምራል

ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ዊንጌት በሚገኘው ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር የግብዓተ መሬት ስነ- ስርአት ይፈፀማል

ማሳሰቢያ ፦ የመኖሪያ ቤት አድራሻ የካ አባዶ G7 ሀይስኩል ፊትለፊት ብሎክ 76

Address

Belay Zeleke Street Or Tunisia Street Or Mesfine Harrar Street
Addis Ababa
166CODE1029

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን - Semien Full Gospel Local Church posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share