24/05/2026
#-ከዕርገት በኋላ ያለዉ እሑድ
በዛሬዉ ዕለት መደበኛ የእሑድ አምልኮ በማህበራችን ባማረ ሁኔታ አካሂደናል።
ለዕለቱ የተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:- ዘኁልቁ 11÷24-30 ፣ቆላስይስ 3÷1-11 እና ማርቆስ 13÷1-13 ናቸዉ።
ርዕስ:-የመንፈስ ቅዱስ መምጣት ተስፋ የምል ሲሆን:-
የእግዚአብሔርን ቃል ወ/ዊ መሰለ አድማሱ ከመልዕክት ክፍሉ ቆላስይስ 3÷1-13 ያለዉን ክፍል አካፍሎናል።
ቆላስይስ 3÷1-4
1: እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ።
2: በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም።
3: ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና።
4: ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ፥ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ። ያለዉን ክፍል በዝርዝር አስተምሮናል።
በዝማሬ የማህበራችን ኳሮች ባማረ ሁኔታ አገልግለዋል።
በዕለቱ በጸሎት ፣በንስሃ ፣በምስጋና እና በአምልኮ ወደ ጌታ ፍት የቀረብንበት ዕለት ነዉ። ይህንን ያማረ ግዜ የሰጠን ልዑል እግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።
ግንቦት 16/2018 ዓ.ም
ጎጋሌ
የማ/ምዕመናናችን የሚዲያ አማራጮችን ለመከታተል:-
📌Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100063750078335
📌Telegram:-https://t.me/Gogalemekaneyesus
📌TikTok:-tiktok.com/