EECMY Gogale congregation ጎጋሌ ከተማ መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • EECMY Gogale congregation ጎጋሌ ከተማ መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን

EECMY Gogale congregation ጎጋሌ ከተማ መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን እንዲህም አላቸው፦ “ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፡ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።

 #-ከዕርገት በኋላ ያለዉ እሑድበዛሬዉ ዕለት መደበኛ የእሑድ አምልኮ በማህበራችን ባማረ ሁኔታ አካሂደናል።ለዕለቱ የተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:- ዘኁልቁ 11÷24-30 ፣ቆላስይስ 3÷1-1...
24/05/2026

#-ከዕርገት በኋላ ያለዉ እሑድ

በዛሬዉ ዕለት መደበኛ የእሑድ አምልኮ በማህበራችን ባማረ ሁኔታ አካሂደናል።

ለዕለቱ የተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:- ዘኁልቁ 11÷24-30 ፣ቆላስይስ 3÷1-11 እና ማርቆስ 13÷1-13 ናቸዉ።
ርዕስ:-የመንፈስ ቅዱስ መምጣት ተስፋ የምል ሲሆን:-

የእግዚአብሔርን ቃል ወ/ዊ መሰለ አድማሱ ከመልዕክት ክፍሉ ቆላስይስ 3÷1-13 ያለዉን ክፍል አካፍሎናል።

ቆላስይስ 3÷1-4
1: እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ።
2: በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም።
3: ሞታችኋልና፥ ሕይወታችሁም በእግዚአብሔር ከክርስቶስ ጋር ተሰውሮአልና።
4: ሕይወታችሁ የሆነ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ፥ በዚያን ጊዜ እናንተ ደግሞ ከእርሱ ጋር በክብር ትገለጣላችሁ። ያለዉን ክፍል በዝርዝር አስተምሮናል።

በዝማሬ የማህበራችን ኳሮች ባማረ ሁኔታ አገልግለዋል።
በዕለቱ በጸሎት ፣በንስሃ ፣በምስጋና እና በአምልኮ ወደ ጌታ ፍት የቀረብንበት ዕለት ነዉ። ይህንን ያማረ ግዜ የሰጠን ልዑል እግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

ግንቦት 16/2018 ዓ.ም
ጎጋሌ

የማ/ምዕመናናችን የሚዲያ አማራጮችን ለመከታተል:-
📌Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100063750078335

📌Telegram:-https://t.me/Gogalemekaneyesus

📌TikTok:-tiktok.com/

✟✟ የኢትዮጵያ  ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አመለካከት ስለሐዋሪያት እና ስለ ነብያት ሹመት ምንድነው?➾ ቤተ ክርስቲያን በመሠረቱ የ“ሐዋርያ” ሹመት ለመጀመሪያው የክርስትና ዘመን...
21/05/2026

✟✟ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አመለካከት ስለሐዋሪያት እና ስለ ነብያት ሹመት ምንድነው?
➾ ቤተ ክርስቲያን በመሠረቱ የ“ሐዋርያ” ሹመት ለመጀመሪያው የክርስትና ዘመን ልዩ አገልግሎት እንደነበረ ታምናለች። እነርሱም 12ቱ ሐዋርያት በቀጥታ በጌታ ኢየሱስ የተጠሩ እና የምሥራቹ መሠረት የሆኑ ነበሩ።
➾ ኤፌሶን 2፥20 እንዲህ ይላል፦ “በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጸዋል።” ይህም ማለት መሠረቱ አንድ ጊዜ የተጣለ ነው እንጂ በየዘመኑ አዲስ ሐዋርያትና ነብያትን ማቋቋም አይደለም።

✟✟ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ ኢየሱስ አመለካከት ስለነብያት ሹመት ምንድነው?
➾ እግዚአብሔር በቃሉ የሚናገሩ ብዙ ሰዎች አሉ። ነገር ግን “ነቢይ” በሚል ልዩ የሥልጣን ወይም የሹመት ደረጃ በጣም ጥንቃቄ ማድርግ እንዳለበት ታምናለች። ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ሙሉ ሆኖ ተሰጥቷል፤ ከእርሱ ውጭ አዲስ መገለጥ አያስፈልግም ብላ ታምናለች።
✟✟ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ በግልፅ የምትቀበለው፦
➾ የእረኝነት (Pastoral Ministry)
➾የወንጌል አገልግሎት
➾የማስተማር እና የመጋቢነት አገልግሎት(ክህነት ) አገልግሎት ነው።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ ትኩረታቸው በ“ቃልና ቅዱሳት ምሥጢራት” አገልግሎት ላይ ነው፥ እንጂ በአዲስ የሐዋርያት ወይም የነብያት ደረጃ ላይ አይደለም።
✟✟ ለምን ጥንቃቄ ያደርጋሉ?
➾ሰዎች “እግዚአብሔር መኖሩን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደመለከቱ፣
➾ የሰው ሥልጣን ከቃሉ በላይ እንዳይሆን ቤተ ክርስቲያን በወንጌል ላይ እንድትቆም ነው።

መደምደሚያ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤ/ክ መካነ ኢየሱስ አንጻር፦
የመጀመሪያዎቹ ሐዋርያትና ነብያት ልዩ መሠረታዊ አገልግሎት ነበራቸው። ዛሬ ግን “ሐዋርያ” ወይም “ነቢይ” በሚል ልዩ ሹመት ማቋቋም አስፈላጊ አይደለም ብለው ያምናሉ። ዋናው ጥሪ ወንጌልን በትክክል መስበክና መጽሐፍ ቅዱስን በታማኝነት ማስተማር ነው። ከዚህ ያፈነገጠ ትምህርት አትቀበልም ።

ቄስ አየለ አጥሬ

ወቅታዊ መግለጫ ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋናዉ ጽ/ቤት:-
19/05/2026

ወቅታዊ መግለጫ ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋናዉ ጽ/ቤት:-

የማህበራችን የተወጣጡ ኳር 13ኛ አመት ምስረታ በዓላቸዉን በዛሬዉ ዕለት በድምቀት አክብረዋል። በዓላቸዉን ስያከብሩ በምስጋናና በአምልኮ ጌታን አመስግነዋል፣ ክብርና ምስጋና ለስሙ ይሁን።ስለ ...
17/05/2026

የማህበራችን የተወጣጡ ኳር 13ኛ አመት ምስረታ በዓላቸዉን በዛሬዉ ዕለት በድምቀት አክብረዋል።

በዓላቸዉን ስያከብሩ በምስጋናና በአምልኮ ጌታን አመስግነዋል፣ ክብርና ምስጋና ለስሙ ይሁን።

ስለ እነርሱ እኛም እንደማህበረ ጌታን አመስግነናል። ስለሁሉም ነገር የጌታ ስም የተመሰገነ ይሁን።

 #-ከትንሳኤ በኋላ 5ኛ እሑድመደበኛ የእሑድ አምልኮ በማህበራችን ባማረ ሁኔታ አካሂደናል።ለዕለቱ የተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:- 1ኛ ነገሥት 18÷30-39 ፣ሮሜ 8÷26-30 እና ማቴዎስ...
17/05/2026

#-ከትንሳኤ በኋላ 5ኛ እሑድ

መደበኛ የእሑድ አምልኮ በማህበራችን ባማረ ሁኔታ አካሂደናል።

ለዕለቱ የተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:- 1ኛ ነገሥት 18÷30-39 ፣ሮሜ 8÷26-30 እና ማቴዎስ 7÷7-12 ናቸዉ።
ርዕስ:-ስለ ጸሎት የምል ነዉ።

የእግዚአብሔርን ቃል ከወንድማችን አማኑኤል ዛዉቴ የተካፈለን ስሆን ከወንጌል ክፍሉ ማቴዎስ 7÷7-12 ያለዉን ክፍል ስለ ጸሎት አስተምሮናል።
ጸሎት ማለት ሰዉ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ማለት ነዉ። መለመን፣ መፈለግ እና ማንኳኳት እንዴ ቃሉ በቃሉ ዉስጥ ሆነን መሆን አለበት። የምል ጭብጥ ሀሳብ አካፍሎናል።

በዝማሬ የማህበራችን የተወጣጡ ኳሮች ባማረ ሁኔታ አገልግለዋል።
በአጠቃላይ በዛሬዉ ዕለት በጸሎት ፣በንስሃ ፣በምስጋና እና በአምልኮ ወደ ጌታ ፍት የቀረብንበት ዕለት ነዉ። ይህንን ያማረ ግዜ የሰጠን ልዑል እግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።

ግንቦት 09/2018 ዓ.ም
ጎጋሌ

የማ/ምዕመናናችን የሚዲያ አማራጮችን ለመከታተል:-
📌Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100063750078335

📌Telegram:-https://t.me/Gogalemekaneyesus

📌TikTok:-tiktok.com/

በአካል ጉዳተኞች አገልግሎት ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በቤተ ክርስቲያቱ ዋና ጽሕፈት ቤት እየተካሄደ ይገኛል።****  **** አውደጥናቱ "ከስቃይ ባሻገር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ሲሆን ...
14/05/2026

በአካል ጉዳተኞች አገልግሎት ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በቤተ ክርስቲያቱ ዋና ጽሕፈት ቤት እየተካሄደ ይገኛል።
**** ****
አውደጥናቱ "ከስቃይ ባሻገር" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ሲሆን ከተለያዩ የቤተ ክርስቲያቱ ሲኖዶሶች እና የአገልግሎት ክፍሎች የመጡ አገልጋዩች እና መሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛል።

አላማውም በቤተ ክርስቲያን እና በማህበረሰብ ውስጥ ያሉ አካል ጉዳተኞችን ፍላጎቶችኝ በመረዳት በአካታችነት የማገልገል አስፈላጊነት ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ነው።

በመክፈቻ መርሃ ግብሩም የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዝዳንት ባደረጉት ንግግር ይህ ስልጠና በይዘቱ የመጀመሪያው መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ድምበር የለሽ መሆኑን ገልፀዋል። አክለውም በቤተ ክርስቲያን እና በማህበረሰብ ውስጥ ውስንነት ያላቸውን ሰዎች አቅማቸውን በመጠቀም በህይወታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ መርዳት አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

የአውደ ጥናቱም ተካፋዮች መጽሐፍ ቅዱሳዊ የአካል ጉዳተኝነትን ትርጓሜ መገንዘባቸውን እና ሊሰጣቸው ስለሚገባ አገልግሎት መረዳታቸውን በመግለጽ ብዙ ጎጂ ባህላዊ መረዳቶችን እንዲቀይሩ ስልጠናው እንደረዳቸው ተናግረዋል።

አገልግሎቱን በብሔራዊ ደረጃ እያስተባበረ ከሚገኘው የወንጌል እና ቲኦሎጂ መምሪያ የዲያቆና አገልግሎት የሥራ ክፍል ለመረዳት እንደተቻለው ይህንን መሰል ሥልጠና በቀጣይ በተለያዩ ክላስተሮች ከአጋር ድርጅት ከሆነው ከጆኒና ጓደኞቹ ተቋም ጋር በመተባበር እንደሚሰጥ ተገልጿል።

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus

12/05/2026
 #-የእሑድ መደበኛ አምልኮ በማህበራችን በድምቀት አካሂደናል።📌ከትንሳኤ በኋላ 4ኛ እሁድ👉ለዕለቱ የተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:-ዘጸአት 6÷1-9 ፣ 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5÷1-5 እና ማ...
10/05/2026

#-የእሑድ መደበኛ አምልኮ በማህበራችን በድምቀት አካሂደናል።

📌ከትንሳኤ በኋላ 4ኛ እሁድ

👉ለዕለቱ የተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች:-
ዘጸአት 6÷1-9 ፣ 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5÷1-5 እና ማርቆስ 12÷28-34 ናቸዉ።
👉ርዕስ:- ስለ ቅድስና መንገድ የምል ነዉ

የእግዚአብሔርን ቃል በወ/ዊት የኔነሽ ኩምባታ አማካኝነት ለዕለቱ ከተመደቡ መጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የወንጌሉን ክፍል ማርቆስ 12÷28-34 ያለዉን ክፍል ተካፍለናል።

በዝማሬ አገልግሎት የማህበራችን ይድድያ ኳር ያገለገሉን ስሆን 14ኛ ምስረታ በዓላቸዉንም በድምቀት አክብረዋል።
በእነዚህና በሌሎች መንፈሳዊ ዝግጅቶች የዛሬዉን ፕሮግራም በእግዚአብሔር እገዛ በድምቀት አድርገናል።
በዚህ ሁሉ ለረዳን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ለስሙ ይሁን!!

ግንቦት 02/2018 ዓ.ም
ጎጋሌ

የማ/ምዕመናናችን የሚዲያ አማራጮችን ለመከታተል:-
📌Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100063750078335

📌Telegram:-https://t.me/Gogalemekaneyesus

📌TikTok:-tiktok.com/

Address

Gogale, Garda Marta
Addis Ababa

Telephone

+251919322193

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EECMY Gogale congregation ጎጋሌ ከተማ መካነ ኢየሱስ ማ/ምዕመናን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share