Gospel Singer Tamirat Asefa

Gospel Singer Tamirat Asefa የእውነትን ቃል በትክክል የሚያስረዳ
የማያሳፍርም ሠራተኛ መሆን ።2ኛ ጢሞ2፡15

07/09/2026

ቆይ የምን በዓል ነው? የእግዚአብሔር በዓል ክርስቶስ ነው፣ በዓላችንም ነው፣ አትሸወዱ!

“ዮሴፍ ትንሹ የፍሬ ዛፍ ነው፥ በምንጭ አጠገብ የሚያፈራ የፍሬ ዛፍ፤ አረጎቹ በቅጥር ላይ ያድጋሉ።”  — ዘፍጥረት 49፥22
01/09/2026

“ዮሴፍ ትንሹ የፍሬ ዛፍ ነው፥ በምንጭ አጠገብ የሚያፈራ የፍሬ ዛፍ፤ አረጎቹ በቅጥር ላይ ያድጋሉ።”
— ዘፍጥረት 49፥22

♦   ?♦ =====================   በዘላለም ሕይወት ዋስትና አስተምህሮ ላይ ብዙውን ጊዜ የሚነሳው ተቃውሞ ይህ አስተምህሮ ሰዎች ድነታቸውን ስለማያጡ እንደፈለጉ እንዲኖሩ ፈቃድ ...
21/07/2026

♦ ?♦
=====================
በዘላለም ሕይወት ዋስትና አስተምህሮ ላይ ብዙውን ጊዜ የሚነሳው ተቃውሞ ይህ አስተምህሮ ሰዎች ድነታቸውን ስለማያጡ እንደፈለጉ እንዲኖሩ ፈቃድ ይሰጣል ወይንም በሀጥያት መኖር ይችላሉ የሚል ነው። ይህ ደግሞ በሰውኛ አስተሳሰብ ስንመለከተው እውነት ቢመስልም መፅሀፍ ቅዱሳዊ ግን አይደለም።

✍️ አንድ ሰው በእውነት በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከእግዚአብሔር ከተወለደ ሀጥያትን እንደልማድ ያደረገ ህይወት ሊኖር አይችልም ። 1ዮሐ3:6-9

✍️ ፀጋ ሀጥያተኝነትን እና አለማዊ ምኞትን ያስክዳል እንጂ ቅዱሳንን ወደ ሀጥያት አይመራም።ቲቶ 2:11-13

✍️ መፅሀፍ ቅዱስ ደህንነት በፀጋ ብቻ፥ በእምነት ብቻ እንደሆነ ይነግረናል።( ኤፌ ምዕ. 2)
8፤ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤9፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።

✍️ ሰው በእውነት በኢየሱስ ክርስቶስ ባመነበት ቅፅበት ድኗል የደህንነቱንም ዋስትና አግኝቷል። ነገር ግን አንድ ሰው ድነት በእምነት ነው የምንቀበለው ካለ በኋላ ላለመጥፋት መልካም ስራ መስራት ፣ አስራት መክፈል ፣ ሀይማኖታዊ ጥረቶችን ማድረግ አለብኝ ቢል ይህ መፅሀፍ ቅዱሳዊ አይደለም።

📖 ጳውሎስ በገላቲያ መልዕክቱ
❝ይህን ያህል የማታስተውሉ ናችሁን? በመንፈስ ጀምራችሁ በሥጋ ፍጹም ለመሆን ትጥራላችሁን?❞
—ገላትያ 3: 3 (አዲሱ መ.ት)

✍️ ድነታችንን በራሳችን ጥረት ማግኘት አንችልም። ስለዚህ ድነታችንን በራሳችን ጥረት ማፅናት አንችልም።
📌እግዚአብሔር ብቻ ነው ድነታችንን ማፅናት የሚችለው። ( ይሁዳ 24)
📌የእግዚአብሔር እጅ ነው ማንም እንዳይወስደን አጥብቆ የያዘን።( ዮሀንስ 10:28~29)
📌 የእግዚአብሔር ፍቅር ነው ማንም ከእርሱ ሊለየን እንዳይችል የደረገው ( ሮሜ 8:38~39)

✍️ ታዲያ ይህ ማለት አንድ ክርስቲያን ድነቱን ስለማያጣ እንደፈለገ በሃጢአት መኖር ይችላል ማለት ነው?

📖 መፅሀፍ ቅዱስ ምን ይላል፦

📌 ሐዋሪያው ጳውሎስ ስለዚህ ነገር ሲናገር ፥ ( ሮሜ ምዕ. 6)
1፤ እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ እንኑርን? #አይደለም።
2፤ ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን?

📌ክርስቲያኖች አዲስ ፍጥረት ናቸው።( 2 ቆሮ 5:17)

📌 ክርስቲያኖች የመንፈስ ፍሬዎች የሚገለጥባቸው ናቸው።( ገላ 5: 19~21)
📌 ክርስቲያኖች የእግዚአብሔር የቅድስና ዘር በውስጣቸው ስላለ ሀጥያትን እንደልምድ አርገው ሊኖሩ አይችሉም።( 1 ዮሐ 3:6~9)

📌በእግዚአብሔር ጸጋ ሀጥያተኝነትን እና አለማዊ ምኞትን በመካድ በጽድቅ በቅድስና እግዚአብሔርን በመምሰል በጸጋው ሀይል የሚኖሩ ናቸው።
ቲቶ 2:12-13

✍️ ፀጋ ሀጥያተኝነትን እና አለማዊ ምኞትን ያስክዳል እንጂ ቅዱሳንን ወደ ሀጥያት አይመራም።

✍️ስለዚህ የዘላለም ሕይወት ዋስትና ለሀጥያት ፈቃድ ይሰጣል ማለት አይደለም። ይልቅስ ይህንን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነት የተረዳ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ጸጋ ሀጥያተኝነትን እና አለማዊ ምኞትን በመካድ በጽድቅ በቅድስና እግዚአብሔርን በመምሰል በጸጋው ሀይል የሚኖር ነው።
ቲቶ 2:12-13

✍️ከእግዚአብሔር የተወለደ የእግዚአብሔር የቅድስና ዘር በእርሱ ውስጥ ይኖራልና ሀጥያትን እንደልማድ አድርጎ አይኖርም 1ዮሐ3:9 (ሕያው ቃል)

✍️ሮሜ 6:14
ኃጢአት አይገዛችሁምና፤ ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች አ

📌 ። ❤️"""""""""""""""""""""""""""በሰው ልጆች ታሪክ ያልተመዘገበና ከሰውኛ ፍቅር የጠለቀ ታላቅ ፍቅር የዛሬ 2000 አመት በቀራኒዮ ተራራ መስቀል ላይ ተገለጠ።  ኃጢአተኞች...
21/07/2026

📌 ። ❤️
"""""""""""""""""""""""""""
በሰው ልጆች ታሪክ ያልተመዘገበና ከሰውኛ ፍቅር የጠለቀ ታላቅ ፍቅር የዛሬ 2000 አመት በቀራኒዮ ተራራ መስቀል ላይ ተገለጠ። ኃጢአተኞች ፣በደለኞችና ጠላቶች በነበርንበት ጊዜ በፍፁም ፍቅሩ የወደደንና ሕይቱንም አሳልፎ የሰጠን አንድ ንጹህ ተገኝ።

በኃጢአታችን መገረፍ፣መሰቃየትና መሞት የሚገባን እኛ ሆነን ሳለ የማይገባው ኢየሱስ የእኛን ሞት ሞተ እኛን ለማዳን በእኛ ፈንታ ምራቅ ተተፋበት፣ተገረፈ፣ተሰቃየ፣በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ፤ኃጢአታችንን፣ እርግማናችንን፣ነውራችንን ሁሉ አስወገደልን።

ኢየሱስ ክርስቶስ ንጽህ ደሙን አፍስሶ፣ቅዱስ ሥጋውን ቆርሶ ውድ ሕይወቱን ስለእኛ ፍቅር አሳልፎ በመስጠት መውደዱን፣ፍቅሩን በቀራኒዮ አደባባይ ላይ ሲገልጥልን ጭራሽ በእግዚአብሔር እንደተቀሰፈ፣እንደተቸገር
፣እንደተመታ ተቆጠረ።

እርሱ አብዝቶ ቀረበን ፤ምንም የሚወደድ ነገር ሳይኖረን እርሱ ግን ወደደን።በሰማይ ያለውን የክብሩን ዙፋን ትቶ ስለእኛ ፍቅር ሲል እንደ ኃጢአተኛ፣እንደ ወንበዴ፣እንደ ምናምንቴ ተቆጠረ።በእውነት ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ የገለጠው ፍቅር ከአዕምሮ ያልፋል።

👉 ነብዩ ኢሳይያስ በትንቢት ስለመሲሁ ፍቅር ሲናገር፦
ኢሳይያስ 53 ፣6፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
7፤ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም

✍️ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ሰላም ይብዛላችሁ።

Dawit Fassil Ministry

❤️  #ሜምፊቦስቴ❤️==================✍️ንጉስ ዳዊት እና ሜምፊቦስቴ ፦2ሳሙ 4፡4, 9፡4-13✍️ሜምፊቦስቴ የሳኦል የልጅ ልጅ የዮናታን ልጅ ነው፡፡ሽባ የሆነበትም ምክንያት የአያ...
18/07/2026

❤️ #ሜምፊቦስቴ❤️
==================
✍️ንጉስ ዳዊት እና ሜምፊቦስቴ ፦
2ሳሙ 4፡4, 9፡4-13

✍️ሜምፊቦስቴ የሳኦል የልጅ ልጅ የዮናታን ልጅ ነው፡፡
ሽባ የሆነበትም ምክንያት የአያቱን እና የአባቱን ሞት የሰማች ሞግዚት ይዛው ለመሸሽ ስትሞክር ከእጇ በመውደቁ ነው፡፡
2ሳሙ 4፡4

✍️የሜምፊቦስቴ አያት የሆነው ሳኦል የንጉስ ዳዊት ቀንደኛ ጠላት እንደነበር ይታወቃል፡፡
✔️እንዲሁ የሰው ልጆች ምንጭ የሆነው አዳም በሀጥያት ምክንያት የእግዚአብሔር ጠላት ሆነ፡፡ ሮሜ 5፡9

✍️የሜምፊቦስቴ ሞግዚት ይዛው ልትሸሽ ስትሞክር ነው በ 5 አመቱ ወድቆ ሽባ የሆነው፡፡
✔️እንዲሁ የሰው ልጅ በክርስቶስ በማመን በፀጋ ብቻ እንጂ ሞግዚት በሆነው በሙሴ ህግ ህይወት ሊያገኝ እና ሊፀድቅ አይችልም፡፡
ገላ 2፡16, 3፡17-21,ሉቃ 14፡15

✍️የሜምፊቦስቴ አባት ዮናታን የንጉስ ዳዊት የልብ ጓደኛ ከመሆኑ የተነሳ ንጉሱ ስለ ዮናታን ቸርነት እና ምህረት ማድረግ ፈለገ፡፡ 2ሳሙ 9፡7
✔️እግዚአብሔር ለሀጢያተኛው ሰው በክርስቶስ በኩል ምህረት ማድረግ እና ከቁጣው ሊያድነው ፈለገ።
ዮሐ 3፡14-18,ሮሜ 3፡21,ሮሜ 4፡22- ,5:1, ኤፌ 2፡4-6

✍️ሜምፊቦስቴ ይኖር የነበረው ሎዶባር (ምድረበዳ) በሚባል ቦታ ነበር፡፡ 2ሳሙ 9፡4
✔️የሰው ልጅም በሀጥያቱ ምክንያት ከእግዚአብሔር መገኝት እና መግቦት ርቆ ይኖር ነበር፡፡ ኤፌ 2፡11, 1ጴጥ 2፡25

✍️ሜምፊቦስቴ ካለበት ቦታ ወደ ንጉስ ዳዊት እንዳይሄድ እግሩ ሽባ ነው ንጉስ ዳዊት ግን መልዕክተኛ በመላክ ወደ እርሱ እንዲመጣ አደረገው፡፡ 2ሳሙ 9፡1-2
✔️ሀጥያተኛ የሆነውም የሰው ልጅ በራሱ መልካም ስራ በአምላክ ፊት ተቀባይነት ማግኘት ስለማይችል እግዚአብሔር ግን በክርስቶስ ወደ ራሱ ማቅረብ ፈለገ፡፡ ኤፌ2፡8, ሮሜ 3፡21-24,ሮሜ 5፡6-10,

✍️ንጉስ ዳዊት ስለ ዮናታን ሲል ለሜምፊቦስቴ ቸርነትን በማድረግ
2ሳሙ 9፡7
1) እንደ ንጉስ ልጅ ሆነ
2) ከንጉሱ ጋ በማእድ ተቀምጦ ንጉሱ የሚበላውን በላ
3) በኢየሩሳሌም ከንጉሱ ጋር መኖር ጀመረ
4) የአያቱን ምድራዊ ርስት መለሰለት

✔️እንዲሁ እግዚአብሔር ለሀጥያተኛው በክርስቶስ ምክንያት
1) ልጅ አደረገው
2) በክብር በክርስቶስ በቀኙ አስቀመጠን
3) የሕይወት እንጀራ የሆነው ክርስቶስ ምግቡ ሆነለት
4) በአዲሲቱ ኢየሩሳሌም በክርስቶስ መኖር ጀመረ
5) በአዳም ምክንያት ያጣነውን ከዚያም በላይ በክርስቶስ ባረከን ፡፡ ኤፌ 1፡3, ዮሐ 1፡12,1ዮሐ 3፡1-,ዮሐ 6
ኤፌ 2:6-7,ዕብ12:22-24

🤔🤔ቅዱሳን ልብ ሊሉት የሚገባ ፦

✍️ሜምፊቦስቴ በንጉስ ዳዊት ቸርነት እንዲህ ቢሆንም አሁንም ግን #እግሩ #ሽባ #ነው፡፡

✔️ሰው በክርስቶስ አምኖ ከዳነ በኃላ ለመኖር መፍጨርጨር የለበትም ይልቅስ ጻዲቅ በእምነት በሕይወት ይኖራል፡፡ Dawit Fassil

እኔ ምን ኖሮኝ ነው የሚያስወድድ፣ከላይ ከዙፋንህ የሚያስወርድ፣እርቃንህን ሆነ ያለ በፍታ ፣ክብርህን መልሰሃል የኔ ጌታ፣አስቀምጠሄኛል በከፍታ።
08/07/2026

እኔ ምን ኖሮኝ ነው የሚያስወድድ፣
ከላይ ከዙፋንህ የሚያስወርድ፣
እርቃንህን ሆነ ያለ በፍታ ፣
ክብርህን መልሰሃል የኔ ጌታ፣
አስቀምጠሄኛል በከፍታ።

30/06/2026

አመልክሃለው በማደሪያዎችህ መካከል ቆሜ፣

05/06/2026

የቅጠል ሀይማኖት በዝህ ተቀየረ።
“በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤”
— ገላትያ 3፥13

23/05/2026

" #የወንጌል ትውልድ"
2ኛው ዓመት የወንጌል ትውልድ ኮንፈረንስ 2018
ከወጣቶች አገልግሎት ክፍል

#ግንቦት /2018
#አድራሻ:ሶዶ ከተማ መሀል አጥቢያ የሕይወት ቃል ቤተ ክርስቲያን (ማረሚያ ጀርባ)

ሁላችሁንም በጌታ ፍቅር ጋብዘናችኋል።

  Tesfayeመዳኛ ነህ መዳኛ (፪x) ለተረሳው ሰው ጓደኛመዳኛ ነህ መዳኛአባቴ ነህ አባቴ (፪x)አሳደከኝ ከልጅነቴአባቴ ነህ አባቴ (፪x)ህልመኛው ተሽጦ ለግብፃዊ ቤትአገልጋይ እንዲሆን ለረ...
16/05/2026

Tesfaye
መዳኛ ነህ መዳኛ (፪x)
ለተረሳው ሰው ጓደኛ
መዳኛ ነህ መዳኛ
አባቴ ነህ አባቴ (፪x)
አሳደከኝ ከልጅነቴ
አባቴ ነህ አባቴ (፪x)

ህልመኛው ተሽጦ ለግብፃዊ ቤት
አገልጋይ እንዲሆን ለረጅም ዓመት (፪x)
ሲመላለስ ሳለ በታማኝነት
በሀሰት ወንጅለው ከወይኒ ጣሉት (፪x)

ለመልካም ሆነለት አንተን በማክበሩ
ህልሙ እውን ሆነ ወጣ በመምበሩ (፪x)
ሰው ሳያይ በጓዳ እግዚአብሔርን ፈሪ
መሆኑ አይቀርም ተፅዕኖ ፈጣሪ (፪x)

የተጣለን ምታነሳ ለምስኪኑ ምትሳሳ
የታሰረን የምትፈታ የደህንነት ጌታ (፪x)

መዳኛ ነህ መዳኛ (፪x)
ለተረሳው ሰው ጓደኛ
መዳኛ ነህ መዳኛ
አባቴ ነህ አባቴ (፪x)
አሳደከኝ ከልጅነቴ
አባቴ ነህ አባቴ (፪x)

መከራው ስቃዩ ሲያልፍ በሕይወቴ
ከጐኔ አልተለየህ ኢየሱስ ረዳቴ ኢየሱስ አባቴ
እንዳያልፍ አለፈ ያ ሁሉ መከራ
ሃሩር ተሻገርኩኝ ከጌታዬ ጋራ ከኢየሱሴ ጋራ

የበረሃው ፀሐይ እንዳያቃጥለኝ
ደመናን አዞልኝ ጥላ አደረገልኝ (፪x)
እባብ እና ጊንጡ ነድፎ እንዳያስቀረኝ
ከፊቴ እየወጣ እረጋገጠልኝ (፪x)

መዳኛ ነህ መዳኛ (፪x)
ለተረሳው ሰው ጓደኛ
መዳኛ ነህ መዳኛ
አባቴ ነህ አባቴ (፪x)
አሳደከኝ ከልጅነቴ
አባቴ ነህ አባቴ (፪x)

Address

Tamiratasefa04@gmail. Com
Addis Ababa

Telephone

+251929772616

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gospel Singer Tamirat Asefa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Gospel Singer Tamirat Asefa:

Shortcuts

Share