Tewahedo ተዋህዶ

Tewahedo  ተዋህዶ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Tewahedo ተዋህዶ, Eastern Orthodox church, addis ababa, Addis Ababa.

✝️ የቤተ ክርስቲያን ሰማዕታት ዝምታ? የ43ኛውና የ44ኛው የሰበካ ጉባኤ ሪፖርቶች ንጽጽር አሳሳቢነት! 🕯️የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 44ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባ...
17/10/2025

✝️ የቤተ ክርስቲያን ሰማዕታት ዝምታ?
የ43ኛውና የ44ኛው የሰበካ ጉባኤ ሪፖርቶች ንጽጽር አሳሳቢነት! 🕯️

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 44ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በጥቅምት 2018 ዓ.ም. በድምቀት ተጀምሯል። ሆኖም የብዙዎች ጥያቄ የዓምናው አስደንጋጭ ሪፖርት ዘንድሮም ተገቢውን ትኩረት አግኝቷል ወይ የሚለው ነው።

የሰማዕታት ደም በጉባኤው አደራሽ ውስጥ ዝም ሊባል አይገባም!

ለምን ዝምታ? የሰማዕታቱ ደም ይጮኻል!

ባለፈው ዓመት እንደዚህ ያሉ ከባድ ሪፖርቶች ሲቀርቡ፣ ዘንድሮ በኦርቶዶክስ ምእመናን ላይ ግፍ የተፈጸመባቸው አካባቢዎች ቢኖሩም፣ የዝርዝር መረጃዎች በአደባባይ አለመቅረባቸው የሚከተሉትን ጥያቄዎች ያሰነሳል፡-

❓ የጉዳዮቹ ክብደት ቀንሷል? በየአካባቢው የሚፈጸሙት ግፎች (እንደ የምሥራቅ ሸዋ የመነኮሳት ጉዳይ) አልቆሙም!
❓ ፖለቲካዊ ጫና ነው? ቤተ ክርስቲያን የሰማዕታቶቿን ደም መርሳት የለባትም፤ ጫና ቢኖርም እንኳን የእውነት ድምፅ መሆን ይጠበቅባታል!
❓ የሪፖርት ለውጥ? የጉዳዩን ክብደት ለቅዱስ ሲኖዶስና ለዓለም ማቅረብ ዋናው ዓላማ ነው። ዝምታ ለሰማዕታት ግፍ መጨመር በር ይከፍታል።

📢 ጥሪ ለኦርቶዶክሳውያን ምእመናን:
“በጎች በግፍ ሲያልቁ እረኛ በዝምታ አይታይም። ቅዱስ ሲኖዶስ የልጆቹንና የአብያተክርስቲያናቱን መከራ በድፍረትና በግልጽ እንዲያቀርብ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን!”

👉 ይህንን መልዕክት ሼር በማድረግ የዝምታውን ግድግዳ እንስበር!



17/10/2025
✨
17/10/2025

17/10/2025

ይህቺ ጥያቄ ?✨
ማነው የሚበለጠው ?✨

ምግብ
17/10/2025

ምግብ

17/10/2025

🥰🥰🥰 ገራሚ ምርቃት ✨✨✨

🙏
17/10/2025

🙏

ባለፉት ዓመታት ከተፈጸሙትና አሁንም  ከሚፈጸሙት  አሰቃቂ ግፎች የዚች ልጅ አንዱ ነው። በትግራይ ጦርነትም፣ አሁንም በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምድሪቱ ላይ የሚፈጸሙ የጭካኔ አይነቶች ተቆጥ...
16/10/2025

ባለፉት ዓመታት ከተፈጸሙትና አሁንም ከሚፈጸሙት አሰቃቂ ግፎች የዚች ልጅ አንዱ ነው። በትግራይ ጦርነትም፣ አሁንም በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምድሪቱ ላይ የሚፈጸሙ የጭካኔ አይነቶች ተቆጥረው አያልቁም። ወደ ሚዲያ ስለማይወጡ እንጅ አብዛኞቹ። እኔ እንኳ የሰማሗቸው አለመኖርን የሚያስመኙ፣ ሰው መሆንን የሚያስጠሉ፣ ሀገር ምንድን ነው እንድንል የሚያደርጉ እጅግ አሰቃቂ ሰቆቃዎች ብዙ አሉ።

ወታደር ሳይሆን አረመኔ፣ ጨካኝ፣ ሰው በላ አውሬ ነው ተፈቶ የተለቀቀው። ገድሎ እንኳ የማይረካ ደም መጣጭ።

እስከማውቀው ድረስ ውትድርና ሳይንስ ነው።በጥብቅ ዓለማቀፋዊና ሳይንሳዊ ሥርዓት የሚመራ የሀገር የመጨረሻ ደጀን እና ጠባቂ ነበር። አሁን ባለው ጦርነት የምናየው ግን ከዚህ ፈጽሞ የራቀ፣ በገዛ ሀገሩ ልጅ ላይ አውሬያዊ ድርጊት የሚፈጽም ነው የምንመለከተው።

እንዲህ አይነት ጭካኔን በቃ ካላልን ፣ የትም የሚፈጸም ግፍ ካላመመን፣ የከበረው የሰው ልጅ ሕይወት ሞት፣ ሰቆቃና መዋረድ ካላንገበገበን ሰውነት ምንድን ነው!?

@ስምዐ ጽድቅ ኤልያስ

ወንድማችንን አፋልጉን ሼር በማድረግ ተባበሩቤተሰቦቹ በጣም በጭንቀት ላይ ናቸው ። ከአሁን አሁን ይመጣል እያሉ ቢጠብቁም እስካሁን ድምጹ አልተሰማም ። ስሙ ተስፋዬ አበራ ይባላል አዲስ አለም ...
15/10/2025

ወንድማችንን አፋልጉን

ሼር በማድረግ ተባበሩ

ቤተሰቦቹ በጣም በጭንቀት ላይ ናቸው ። ከአሁን አሁን ይመጣል እያሉ ቢጠብቁም እስካሁን ድምጹ አልተሰማም ።

ስሙ ተስፋዬ አበራ ይባላል አዲስ አለም ከእናቱ ጋር ነበር የሚኖረው ። የእናታችን ዘመድ ለቅሶ መጥቶ ወደ አለም ጤና ወስዶት እየሰራ ነበር ። ዛሬ ከጠፋ 25ኛ ቀኑ ነው ።

የወንድማችንን አድራሻ ያየ ከታች በተጠቀሰው ስልክ እንድታሳውቁን ስንል በእግዚአብሔር ስም አደራ እንላለን ።

የቤተሰብ አድራሻ ፦ 0947456124

ቤተሰቦቹ

15/10/2025

✨ማን ነው ?✨

እንደ እኛ  ያመለጣችሁ እንሞክር !ተደራጅታችሁ አቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 05 ወርቁ ሰፈር ለሚገነቡ የማህበር ቤቶች  !በ70/30  የጋራ ህንፃ ማህበር ቤት በተጠባባቂነት መመዝገቢያ የኦንላይን ሊን...
15/10/2025

እንደ እኛ ያመለጣችሁ እንሞክር !
ተደራጅታችሁ አቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 05 ወርቁ ሰፈር ለሚገነቡ የማህበር ቤቶች !
በ70/30 የጋራ ህንፃ ማህበር ቤት በተጠባባቂነት መመዝገቢያ የኦንላይን ሊንክ

https://t.me/constructionIE/30366

 !በቀጣይ ሳምንት 10/02/2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አንባቢያን እጅ ትገባለች። ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት ተስፋዎች ናቸው። ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በሙሉ በጥ...
15/10/2025

!

በቀጣይ ሳምንት 10/02/2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አንባቢያን እጅ ትገባለች።

ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት ተስፋዎች ናቸው። ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በሙሉ በጥንቃቄ መጠበቅና ወደ አምላኳ መምራት የኹል ጊዜ ሥራዋ መኾኑ የታወቀ ነው። በተለይም ደግሞ ወጣት ልጆቿን የዚህ ዓለም ርካሽ ሐሳብ ከቤተ ክርስቲያናዊ ሕይወት (Ecclesiastical life) እንዳያጎድላቸው፥ ከቀድሞ የበለጠ መሥራት አለባት። በጥሩ መሠረት ላይ ያልቆሙ ወጣቶች ስንኳንስ የሌላው ቀርቶ የራሷ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ይኾናሉና። በዚህም መሠረታዊ ምክንያት ቤተ ክርስቲያን ክርስቶሳዊት መኾኗ በጉልህ ይታወቅ ዘንድ ወጣቶቿን በመንፈሳዊ ሕይወትም ኾነ በቤተ ክርስቲያናዊ መረዳት እንዲገኙ ተግታ መሥራት አለባት።

ወጣቶች የምድራዊቷን ቤተ ክርስቲያን (Earthly Church) አባል ስለ ኾኑ፥ በንስሐ ሳሙን እየታጠቡ፥ ከክርስቶስ ሥጋና ደም እየተሳተፉ፥ በቅድስና ሕይወት እንዲኖሩ ማድረግ የቤተ ክርስቲያን እረኞች የተባሉ የካህናት ዋና ሥራ መኾን አለበት። ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ያሉ አካላትም ቢኾኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ብልጫ በዋነኛነት የሚያዩት ከወጣት ልጆቿ ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ነውና። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ በተለይም በዚህ የኃጢአት እሳት በተለያየ መንገድ በሚቀጣጠልበት ዘመን፥ ኦርቶዶክሳዊ የኾነ የወጣትነት አኗኗርን የሚመለከቱ ብዙ ሥራዎች ያስፈልጉናል። ወጣትነት በብዙ መንገድ ሊጠበቅ የሚገባው የሕይወት ክፍል ስለ ኾነ፥ በእያንዳንዱ የወጣትነት የሕይወት ክፍል ውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮችን የሚፈቱ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮዎች ለወጣቱ በእጅጉ ያስፈልጋሉ።

ይህ "የኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች መስታወት" የተሰኘው መጽሐፍ በዋነኛነት በወጣቶች ሕይወት ዙሪያ የሚከሰቱ ነገሮችን መሠረት አድርጎ፥ በተለያዩ ጉዳዮች ቤተ ክርስቲያናዊ አስተምህሮዎችን ለማሳየት የተሞከረበት መጽሐፍ ነው። በመስታወት ፊት ቆመን ፊታችንን ስንመለከት በላያችን ላይ ያለውን ቆሻሻ ማስወገድ እንደምንችል ኹሉ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአስተምህሮ መስታወት ፊት ስንቆምም፡ በውስጣችን ያሉ የኃጢአት ቆሻሻዎችን ማስወገድ እንችላለን፡፡ ይህ መጽሐፍ በወጣትነት ሕይወታችን ኦርቶዶክሳዊውን አኗኗር ገንዘብ አድርገን ጣዕም ያለው ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት እንድንኖር በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትምህርት መስታወትነት ያሳየናል፡፡ የተዘጋጀበት ዋና ዓላማውም ይኸው ነውና፡፡ በዚህ በኹለተኛ ክልስ ዕትም ውስጥ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የማዳበሪያ ሐሳቦች ተጨምረውበታል፡፡ ለምሳሌ አለባበስን፣ ግለ ወሲብን፣ ሰዶማዊነትን፣ ጸሎትን፣ የወር አበባን እንዲሁም በሌሎች አንዳንድ ቦታዎች ላይ የተጨመሩ ሐሳቦች አሉ፡፡

በዚህ መጽሐፍ ስምንት ክፍሎች ያሉት ሲኾን የመጀመሪያው ክፍል ወጣትነት ምን እንደ ኾነ፣ መልካም ወጣት መኾንስ እንዴት ወይም መልካም ወጣት ማለት በራሱ ምን ዓይነት እንደ ኾነ በዝርዝር ተገልጾበታል። ኹለተኛው ክፍል ደግሞ "ፍቅር" ምን እንደ ኾነ የሚያብራራ ነው። እውነተኛ ፍቅር ከተሳሳተ ፍቅር የሚለየው በምን በምን እንደ ኾነ፣ አንድ ሰው በእውነተኛ ፍቅር ውስጥ መኾኑን እንዴት ማወቅ እንደሚችል እንዲሁም የፍቅር ቀን የሚባለው ምን እንደ ኾነ ተብራርቶበታል። በክፍል ሦስት ደግሞ ኦርቶዶክሳዊውን የአለባበስ ሥርዓት እና በዚያ ዙሪያ ያሉ ሐሳቦችን ለማብራራት የተሞከረበት ሲኾን፥ "ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ" ከሚለው አንሥቶ ጌጣጌጦች መጠቀም፣ እንዲሁም በሰውነት ላይ መነቀስን ጨምሮ የተብራራበት ክፍል ነው። አራተኛው ክፍል የመጽሐፉ ሰፊ ክፍል ነው። ይኸውም ስለ ሱስ ምንነት እና መፍትሔዎችን የያዘ ነው። እንግዲህ በዚህ ክፍል ውስጥ በወጣትነት ሕይወት ውስጥ እጅግ በጣም ፈታኝ የኾኑ የሱስ ዓይነቶች ተዘርዝረዋል፥ ከእነዚያ ሱሶችም መውጫ መንገዶች በዝርዝር ተቀምጧል። ለምሳሌ ጫት፣ ሲጋራ፣ ማኅበራዊ ሚዲያ፣ ትዕይንተ ግብረ ዝሙት፣ ግብረ አውናን፣ ሰዶማዊነት፣ ... የመሳሰሉት ሌሎች ከሱስ ጋር ተያያዥነት ያሏቸው ጉዳዮች ተብራርተዋል። በክፍል አምስት ደግሞ በሴቶች የሚከሰተው የወር አበባን በተመለከተ እና በወንዶች የሚከሰተውን ዝንየትን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊው ትምህርት ምንድን ነው የሚለው የተተነተነበት ክፍል ነው። ክፍል ስድስት ዓለማዊነት ምን እንደ ኾነ፥ የትኩረት አቅጣጫውም ምን ምን ላይ እንደ ኾነ ተገልጿል። በሰባተኛው ክፍል ውስጥ ደግሞ ሕልምን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊው አረዳድ ምን እንደ ኾነ ተብራርቷል፡፡ የዚህ መጽሐፍ የመጨረሻው ክፍል ደግሞ ወጣቶች መልካም ይኾኑ ዘንድ ይጠቅሟቸዋል ተብለው የታሰቡ ትምህርታዊ ስብከቶች የተዘረዘሩበት ክፍል ነው።

በአጠቃላይ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ እጅግ መሠረታዊ ናቸው የተባሉ የወጣትነት ሕይወትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ለመብራራት የተሞከሩበት ነው። ይህን መጽሐፍ የምታነቡ በሙሉ በመጽሐፉ ውስጥ የምታገኟቸው የተጣመሙ አገላለጾችና ሐሳቦች ካሉ አስተካክላችሁ እንድታነቡና በጎ የኾነ ምክረ ሐሳባችሁን እንድትለግሱኝ በትሕትና እጠይቃለሁኝ። !

በቀጣይ ሳምንት 10/02/2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ አንባቢያን እጅ ትገባለች።

ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የወደፊት ተስፋዎች ናቸው። ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን በሙሉ በጥንቃቄ መጠበቅና ወደ አምላኳ መምራት የኹል ጊዜ ሥራዋ መኾኑ የታወቀ ነው። በተለይም ደግሞ ወጣት ልጆቿን የዚህ ዓለም ርካሽ ሐሳብ ከቤተ ክርስቲያናዊ ሕይወት (Ecclesiastical life) እንዳያጎድላቸው፥ ከቀድሞ የበለጠ መሥራት አለባት። በጥሩ መሠረት ላይ ያልቆሙ ወጣቶች ስንኳንስ የሌላው ቀርቶ የራሷ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ይኾናሉና። በዚህም መሠረታዊ ምክንያት ቤተ ክርስቲያን ክርስቶሳዊት መኾኗ በጉልህ ይታወቅ ዘንድ ወጣቶቿን በመንፈሳዊ ሕይወትም ኾነ በቤተ ክርስቲያናዊ መረዳት እንዲገኙ ተግታ መሥራት አለባት።

ወጣቶች የምድራዊቷን ቤተ ክርስቲያን (Earthly Church) አባል ስለ ኾኑ፥ በንስሐ ሳሙን እየታጠቡ፥ ከክርስቶስ ሥጋና ደም እየተሳተፉ፥ በቅድስና ሕይወት እንዲኖሩ ማድረግ የቤተ ክርስቲያን እረኞች የተባሉ የካህናት ዋና ሥራ መኾን አለበት። ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ያሉ አካላትም ቢኾኑ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ብልጫ በዋነኛነት የሚያዩት ከወጣት ልጆቿ ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ነውና። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ በተለይም በዚህ የኃጢአት እሳት በተለያየ መንገድ በሚቀጣጠልበት ዘመን፥ ኦርቶዶክሳዊ የኾነ የወጣትነት አኗኗርን የሚመለከቱ ብዙ ሥራዎች ያስፈልጉናል። ወጣትነት በብዙ መንገድ ሊጠበቅ የሚገባው የሕይወት ክፍል ስለ ኾነ፥ በእያንዳንዱ የወጣትነት የሕይወት ክፍል ውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮችን የሚፈቱ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮዎች ለወጣቱ በእጅጉ ያስፈልጋሉ።

ይህ "የኦርቶዶክሳዊ ወጣቶች መስታወት" የተሰኘው መጽሐፍ በዋነኛነት በወጣቶች ሕይወት ዙሪያ የሚከሰቱ ነገሮችን መሠረት አድርጎ፥ በተለያዩ ጉዳዮች ቤተ ክርስቲያናዊ አስተምህሮዎችን ለማሳየት የተሞከረበት መጽሐፍ ነው። በመስታወት ፊት ቆመን ፊታችንን ስንመለከት በላያችን ላይ ያለውን ቆሻሻ ማስወገድ እንደምንችል ኹሉ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአስተምህሮ መስታወት ፊት ስንቆምም፡ በውስጣችን ያሉ የኃጢአት ቆሻሻዎችን ማስወገድ እንችላለን፡፡ ይህ መጽሐፍ በወጣትነት ሕይወታችን ኦርቶዶክሳዊውን አኗኗር ገንዘብ አድርገን ጣዕም ያለው ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት እንድንኖር በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትምህርት መስታወትነት ያሳየናል፡፡ የተዘጋጀበት ዋና ዓላማውም ይኸው ነውና፡፡ በዚህ በኹለተኛ ክልስ ዕትም ውስጥ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የማዳበሪያ ሐሳቦች ተጨምረውበታል፡፡ ለምሳሌ አለባበስን፣ ግለ ወሲብን፣ ሰዶማዊነትን፣ ጸሎትን፣ የወር አበባን እንዲሁም በሌሎች አንዳንድ ቦታዎች ላይ የተጨመሩ ሐሳቦች አሉ፡፡

በዚህ መጽሐፍ ስምንት ክፍሎች ያሉት ሲኾን የመጀመሪያው ክፍል ወጣትነት ምን እንደ ኾነ፣ መልካም ወጣት መኾንስ እንዴት ወይም መልካም ወጣት ማለት በራሱ ምን ዓይነት እንደ ኾነ በዝርዝር ተገልጾበታል። ኹለተኛው ክፍል ደግሞ "ፍቅር" ምን እንደ ኾነ የሚያብራራ ነው። እውነተኛ ፍቅር ከተሳሳተ ፍቅር የሚለየው በምን በምን እንደ ኾነ፣ አንድ ሰው በእውነተኛ ፍቅር ውስጥ መኾኑን እንዴት ማወቅ እንደሚችል እንዲሁም የፍቅር ቀን የሚባለው ምን እንደ ኾነ ተብራርቶበታል። በክፍል ሦስት ደግሞ ኦርቶዶክሳዊውን የአለባበስ ሥርዓት እና በዚያ ዙሪያ ያሉ ሐሳቦችን ለማብራራት የተሞከረበት ሲኾን፥ "ሴት የወንድን ልብስ አትልበስ" ከሚለው አንሥቶ ጌጣጌጦች መጠቀም፣ እንዲሁም በሰውነት ላይ መነቀስን ጨምሮ የተብራራበት ክፍል ነው። አራተኛው ክፍል የመጽሐፉ ሰፊ ክፍል ነው። ይኸውም ስለ ሱስ ምንነት እና መፍትሔዎችን የያዘ ነው። እንግዲህ በዚህ ክፍል ውስጥ በወጣትነት ሕይወት ውስጥ እጅግ በጣም ፈታኝ የኾኑ የሱስ ዓይነቶች ተዘርዝረዋል፥ ከእነዚያ ሱሶችም መውጫ መንገዶች በዝርዝር ተቀምጧል። ለምሳሌ ጫት፣ ሲጋራ፣ ማኅበራዊ ሚዲያ፣ ትዕይንተ ግብረ ዝሙት፣ ግብረ አውናን፣ ሰዶማዊነት፣ ... የመሳሰሉት ሌሎች ከሱስ ጋር ተያያዥነት ያሏቸው ጉዳዮች ተብራርተዋል። በክፍል አምስት ደግሞ በሴቶች የሚከሰተው የወር አበባን በተመለከተ እና በወንዶች የሚከሰተውን ዝንየትን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊው ትምህርት ምንድን ነው የሚለው የተተነተነበት ክፍል ነው። ክፍል ስድስት ዓለማዊነት ምን እንደ ኾነ፥ የትኩረት አቅጣጫውም ምን ምን ላይ እንደ ኾነ ተገልጿል። በሰባተኛው ክፍል ውስጥ ደግሞ ሕልምን በተመለከተ ኦርቶዶክሳዊው አረዳድ ምን እንደ ኾነ ተብራርቷል፡፡ የዚህ መጽሐፍ የመጨረሻው ክፍል ደግሞ ወጣቶች መልካም ይኾኑ ዘንድ ይጠቅሟቸዋል ተብለው የታሰቡ ትምህርታዊ ስብከቶች የተዘረዘሩበት ክፍል ነው።

በአጠቃላይ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ እጅግ መሠረታዊ ናቸው የተባሉ የወጣትነት ሕይወትን የሚመለከቱ ጉዳዮች ለመብራራት የተሞከሩበት ነው። ይህን መጽሐፍ የምታነቡ በሙሉ በመጽሐፉ ውስጥ የምታገኟቸው የተጣመሙ አገላለጾችና ሐሳቦች ካሉ አስተካክላችሁ እንድታነቡና በጎ የኾነ ምክረ ሐሳባችሁን እንድትለግሱኝ በትሕትና እጠይቃለሁኝ።

@መምህር ዮሐንስ ጌታቸው

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tewahedo ተዋህዶ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

ለተዋህዶ ተዋህደን እናገልግል

የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትልቅ ፈተና ላይ ናት

ጠላቶቾ ግዙፋን እና እረቂቃን ናቸው ለዚህም

ለተዋህዶ ተዋህደን እናገልግል