Impact Worship Center - የክርስቲያኖች መቅደስ ቤ/ክ

Impact Worship Center - የክርስቲያኖች መቅደስ ቤ/ክ … ወደ ክርስቶስ ፍፁም ሙላት!

የአገልግሎት ስልጠና እድል"የበዛ ሕይወት እና አገልግሎት”“ሕይወት እንዲሆንላችሁ እንዲበዛላችሁም”- ዮሐ. 10:10ከበዛና ከተትረፈረፈ ሕይወት የሚወጣና ለሌሎች የሚፈስስ አገልግሎት!ስልጠናው ...
17/03/2026

የአገልግሎት ስልጠና እድል

"የበዛ ሕይወት እና አገልግሎት”

“ሕይወት እንዲሆንላችሁ እንዲበዛላችሁም”- ዮሐ. 10:10

ከበዛና ከተትረፈረፈ ሕይወት የሚወጣና ለሌሎች የሚፈስስ አገልግሎት!

ስልጠናው የሚመለከታቸው ሰዎች፡-

✝️ ከዚህ በፊት በመንፈሳዊ አገልግሎት ተሳትፋችሁ ካላወቃችሁ!

✝️ ከዚህ በፊት ከነበራችሁ አገልግሎት አቁማችሁ ከሆነ!

✝️ በአሁኑ ወቅት በአገልግሎት ላይ ካላችሁና ስለአገልግሎት ያላችሁን ምልከታ ለማስፋትና ጸጋን ለመካፈል ፍላጎት ካላችሁ!

ለመመዝገብ፦
➡️ በቴሌግራም፡- በዚህ የቴሌግራም user name inbox በማድረግ ስምና ስልክ ቁጥር ያስቀምጡ፡፡

➡️ በስልክ፡- በ 0933729694 በመደወል ሙሉ ስምና ስልክ ቁጥር ይስጡ፡፡

ማሳሰቢያ፡-
ስልጠናው የሚሰጠው ለተመዘገቡ ብቻ ነው፡፡

የስልጠኛው note በየሳምንቱ በቴሌግራም ስለሚለቀቅ ለስልጠናው ተመዝጋቢወች የሚከፈተውን የቴሌግራም ግሩፕ መቀላቀል የግድ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ ፖስተሩን ይመልከቱ!

በጥሪ፣ በራእይና በሕልም የማደግ የአንድ ወር ጉዞ!የየካቲት 2018ን ሶስት እሁዶች በዚህ ርእስ ላይ ተከታታይ ትምህርት ይሰጣል፡፡እንደ አማኞች•  ለጥሪ ምላሽ መስጠት ማለት ምን ማለት ነው?...
23/01/2026

በጥሪ፣ በራእይና በሕልም የማደግ የአንድ ወር ጉዞ!

የየካቲት 2018ን ሶስት እሁዶች በዚህ ርእስ ላይ ተከታታይ ትምህርት ይሰጣል፡፡

እንደ አማኞች

• ለጥሪ ምላሽ መስጠት ማለት ምን ማለት ነው?

• ተልእኳችንን እንዴት እንለያለን?

• ራእያችንን እንዴት እንወቅ?

• ሕልም የተሰኘውን ሃሳብ እንደ ጌታ ቃል እንዴት እናስተናግደው?

• በአነዚህ ከላይ በተጠቀሱት፣ በጥሪ፣ በተልእኮ፣ በራእይ እና በሕልም መካከል ያለው ግንኙነትና ልዩነት ምንድን ነው?

• ትርጉማቸውን አለማወቅና በእያንዳንዳቸው አለማደግ የሚያስከትልብን አሉታዊ ተጽእኖ ምንድን ነው?

ትምህርቱ የሚሰጠው - በዶ/ር ኢዮብ ማሞ!

የትምርቱ ቀናት - የካቲት 1፣ 8 እና 15 (ሶስት የየካቲት እሁዶች)

ሰዓት - ከ4፡30 እስከ 7፡00 (በመደበኛው የአምልኮ ጊዜ)

ቦታ - ኢምፓክት የአምልኮ ማዕከል (የክርስቲያኖች መቅደስ ቤ/ከ)

አድራሻ - ላንቻ ካለው ካልዲስ አጠገብ 30 ሜትር ገባ ብሎ፡፡

የጉግል አድራሻ መጠቀም ለምትፈልጉ

https://g.co/kgs/H8WPDwJ

የምክር አግልግሎት ማለት!“ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤ በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል” - ምሳ. 15፡22የምክር ጥበባችንን ስናሳድግ ሰዎች እቅዳቸውን እንዲያሳኩ የማገዝ አቅም ለማግኘት ስ...
08/07/2025

የምክር አግልግሎት ማለት!

“ምክር ሲጓደል ዕቅድ ይፋለሳል፤ በብዙ አማካሪዎች ግን ይሳካል” - ምሳ. 15፡22

የምክር ጥበባችንን ስናሳድግ ሰዎች እቅዳቸውን እንዲያሳኩ የማገዝ አቅም ለማግኘት ስለምንሰራ፣ እኛም በጥበብ ከማደጋችን በተጨማሪ ሰዎችንም ስኬታማ እናደርጋቸዋለን፡፡

እንዴት ያለ ልናጣው የማይገባን ስኬታማ ሕይወት!
በዚህ ርእስ ላይ የተዘጋጀው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡

የስልጠናው ርእስ፡- “ክርስቲያናዊ የምክር አገልግሎት መርሆዎች!” (Principles of Christian Counseling!)

ስልጠናው የሚሰጥባቸው ቀናት፡- ቅዳሜ ነሃሴ 10፣ ቅዳሜ ነሃሴ 17 እና ቅዳሜ ነሃሴ 24 (ለሶስት ቅዳሜ ከሰአቶች)

የስልጠናው ሰዓት፡- በሶስቱም ቅዳሜዎች ከሰዓት በኋላ ከ8፡30 እስከ 12፡30

የስልጠናው ቦታ፡- IMPACT Worship Center (ላንቻ ከአልፓውሎ ሕንጻ አጠገብ)

በስልጠናው ላይ የሚገኙት ግብዣ የተደረገላቸውና የተመዘገቡ ብቻ ናቸው፡፡

ለማስመዝብና ቦታ ለማስያዝ ለመካፈል ያለዎትን ፈቃደኝት ፈጥነው ያሳውቁኝ፡፡

ለመመዝገብ፡- በዚህ 👉🏼 የቴሌግራም user name inbox በማድረግ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር ያስቀምጡ፡፡

ለስልጠናው የምንቀበለው ቁጥር ውስን ስለሆነ ቀድሞ ለተመዘገቡ ቅድሚያ ይሰጣል!

ማሳሰቢያ:- ለመሰልጠን በአካል መገኘትን ስለሚጠይቅ ከመመዝገባችሁ በፊት ያንን ማድረግ መቻላችሁንና ፈቃደኛ መሆናችሁን እርግጠኛ ሁኑ፡፡

Dr. Eyob Mamo

ክርስቲያናዊ የምክር አገልግሎት መርሆዎች! (Principles of Christian Counseling!)የተሰኘ ስልጠና አዘጋጅቼላችኋለሁ፡፡በፖስተሩ ላይ ባለው መረጃ መሰረት ከአሁኑ መመዝገብ ት...
05/07/2025

ክርስቲያናዊ የምክር አገልግሎት መርሆዎች!
(Principles of Christian Counseling!)
የተሰኘ ስልጠና አዘጋጅቼላችኋለሁ፡፡

በፖስተሩ ላይ ባለው መረጃ መሰረት ከአሁኑ መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡

ለመመዝገብ፡- በዚህ 👉🏼 የቴሌግራም user name inbox በማድረግ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር ያስቀምጡ፡፡

ለስልጠናው የምንቀበለው ቁጥር ውስን ስለሆነ ቀድሞ ለተመዘገቡ ቅድሚያ ይሰጣል!

ማሳሰቢያ:- ስልጠናው ሙሉ በሙሉ ነጻ ስለሆነ፣ ክፍያ የሚጠይቅ መልእክት ቢደርሳችሁ ከእኛ እንዳልሆነ ማሳሰብ አንወዳለን፡፡

Dr. Eyob Mamo

31/08/2023
ተግባራችንና ንግግራች“ኢየሱስ ለማድረግና ለማስተማር የጀመረውን ሁሉ” - የሐዋ. 1፡1 “ሰዎች ንግግራችንና ተግባራችን ሲጋጭባቸው የሚያምኑት ተግባራችንን ነው” የሚባል የከረመ አባባል አለ፡፡...
03/11/2022

ተግባራችንና ንግግራች

“ኢየሱስ ለማድረግና ለማስተማር የጀመረውን ሁሉ” - የሐዋ. 1፡1

“ሰዎች ንግግራችንና ተግባራችን ሲጋጭባቸው የሚያምኑት ተግባራችንን ነው” የሚባል የከረመ አባባል አለ፡፡ እውነት ነው!

ክርስቶስ ከማስተማሩ በፊት ማንነቱን በተግባር ያስመሰከረ ቀዳሚ መሪያችን ነው፡- “ለማድረግና ለማስተማር”!

እንደ መሪዎች የምንመራቸው ወገኖቻችን ካለማቋረጥ ንግግራችንን፣ ትምህርታችንን፣ ዝማሬያችንንና የምናውጀውን አዋጅ ያደምጣሉ፡፡ ከዚያም ጋር አብረው የምንተገብረውን ተግባር በሚገባ ያጤናሉ፡፡

ሁለቱ ሲስማማላቸው ይህ ነው የማይባል መልካም ተጽእኖ ያድርባቸዋል፡፡ ሁለቱ ከተጣረሰ ግን የተወሰነ ግራ የመጋባት ጊዜን ካሳለፉ በኋላ በመጨረሻ የሚያምኑት ተግባራችንን ነው፡፡

የመሪነት ተጽእኗችን ከፍታ ልቆ እንዲገኝ ከሁሉም በፊት የተግባር ሰዎች እንድንሆን ቃሉ ያስተምረናል፡፡

መሪነታችንን በተግባር እንጀምረው፡፡ እንገኝ! ታማኝ እንሁን! እናገልግል! ራሳችንንና ገንዘባችንን እንስጥ! ያን ጊዜ ንግግራችን

ዛሬ “በእግዚአብሔርና በሰው ሁሉ ፊት በተግባርና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ኢየሱስ” (ሉቃ. 24፡19) ላስታውሳችሁ ወደድኩኝ፡፡

እወዳችኋለሁ! በርቱ!

Eyob Mamo

ከመሰናክል ባሻገር!“በአንድ እንቅፋት ምክንያት ተስፋ በመቁረጥ የሕይወታችሁን ግብ ከመከተል ማቆም ማለት የመኪናችሁ አንዱ ጎማ ስለተነፈሰ ብቻ ሌሎቹን ሶስት ጎማዎች በስለት በመቅደድ ማስተንፈ...
07/07/2022

ከመሰናክል ባሻገር!

“በአንድ እንቅፋት ምክንያት ተስፋ በመቁረጥ የሕይወታችሁን ግብ ከመከተል ማቆም ማለት የመኪናችሁ አንዱ ጎማ ስለተነፈሰ ብቻ ሌሎቹን ሶስት ጎማዎች በስለት በመቅደድ ማስተንፈስ እንደማለት ነው” - ካልታወቀ ምንጭ

ሰሞኑን ካልተሳካው ሙከራ፣ ከተዘጋው የእድል በር፣ ከተቋረጠው የሰው ተስፋ፣ ከባከነው ንብረት . . . ባሻገር የሚሄድ ማንነት እንዲኖራችሁ ጸሎቴ ነው፡፡

https://t.me/Dreyob

https://m.youtube.com/user/naeleyob623

https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Tuesday 09:00 - 20:00
Wednesday 09:00 - 20:00
Thursday 09:00 - 20:00
Friday 09:00 - 20:00
Saturday 09:00 - 20:00
Sunday 09:00 - 14:00

Telephone

+251114670154

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Impact Worship Center - የክርስቲያኖች መቅደስ ቤ/ክ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Impact Worship Center - የክርስቲያኖች መቅደስ ቤ/ክ:

Share