29/05/2022
ዘመናችንን አድስ!!!!
ክፍል 3
የሆነብንን አስብ!!!
በሰቆቃው ኤርሚያስ መፅሐፍ ላይ ****እንዴት**** ይሄ ሆነብን እያለ የሚጠይቅ የሚማፀን ወደ እግዚአብሔር የሚያለቅስ ነብይ ፅሁፍ ነው!!! ሰቆ.ኤር 5:1
"አቤቱ የሆነብንን አስብ" ብሎ ይጮሃል!!! ይሄን ደስ የማይል ነገር ዝም ብሎ በህይወታችን እና በዘመናችን ሲሆን ቁጭ ብሎ መመልከት የለብንም!!! እየሆነልን ሳይሆን እየሆነብን ሲቀጥል እግዚአብሔር የሆነብንን አስብ???ማለት መልካም ነው?? የሚሆኑትን መጥፎ ነገሮች መላመድ እና አብሮ መቀጠል የለብንም!!እስኪ የሆነብንን ምንድነው???
1.ስድብ(ክብር አልባ ሕይወት)
"ስድባችንንም እይ" ቁ 1
ንቀትና ስድብ እንዲሁም ውርደት ሲሆንብን ዝም አይባልም!!!
2.ንጥቂያ(የእኛ የሆነ ነገር ሌሎች ሲወስዱት)
"ርስታችን ለእንግዶች
ቤቶቻችን ለሌሎች ሆኑ" ቁ2
በሕግም በተፈጥሮም የእኛ የሆኑ ነገሮች በሌሎች ሲወስዱት እና ስንቀማ ዝም አይባልም??
3.ምንጭ እና ከለላ አልባ ስንሆን!!!
"አባት የሌለን ሆነናል" ቁ 3
አባት ምንጭ ነው አባት ከለላ ነው ከለላ እና ምንጭ አልባ መሆን ሲመጣ ዝም ብለን መመልከት የለብንም!!
4.ለትንንሽ ነገሮች ብዙ ዋጋ መክፈል!!
"ውኃችንን በብር ጠጣን
እንጨታችንን በዋጋ ገዛን" ቁ 4
ለሕይወት የሚያስፈልጉ ትንንሽ ነገሮች በጣም ብዙ ዋጋ እንድንከፍልባቸው ስንጠየቅ ይሄንን ዝም ማለት የለብንም!!!
እናም አቤቱ የሆነብንን አስብ??? ማለት አለብን እንጂ ዝም ብለን ማየይት የለብንም!!! ደግሞም ዘመናችንን አድስ ማለት ይጠበቅብናል!!! ቁጭ ብለን የሆነብንን እያየን ብናማርር መፍትሄ አይሆንም!!! ዘመን ይታደሳል!!!