24/05/2026
በፍቅር የተዋጠ ግዴታ ❤️ ❤️ ❤️
ወደ እግዚአብሔር ቤት መሄድ በሳምንት አንድ ቀን የሚፈጸም ሃይማኖታዊ ልማድ ወይም በሕግ ተገዶ የሚከፈል የዕዳ ክፍያ አይደለም።
ወደ እግዚአብሔር ቤት መገስገስ በፍቅር የተዋጠ ግዴታ እና በግዴታ የተደገፈ ውዴታ ነው።
አንድ ሕፃን ልጅ ለመኖር መተንፈስ ግዴታው እንደሆነ ሁሉ የክርስቶስ ሕይወት በውስጡ ያለ የተጠማ አማኝም ወደ አባቱ ቤት መሄድ የነፍሱ መተንፈሻ ነው። ሕጉ ሳይሆን ፍቅሩ ያስገድደዋል።
ዳዊት የዚህን ምስጢር ሲገልጠው፡ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ (መዝሙር 122፥1) ይላል። ዳዊት ወደ ቤተ መቅደስ የሮጠው ንጉሣዊ ፕሮቶኮል አስገድዶት ሳይሆን በውስጡ ባለው መለኮታዊ ናፍቆትና ፍቅር ተውጦ ነው።
ፍቅር ግዴታን ወደ ታላቅ ደስታ ይለውጠዋል
የእግዚአብሔር ቃል፡ አንዳንዶችም እንደሚያደርጉት መሰብሰባችንን አንተው (ዕብራውያን 10፥25) በማለት ያዝዘናል። ይህ ትእዛዝ (ግዴታ) ስሜታችን በሚደክምበት ቀን ወደ እግዚአብሔር ቤት የምንሮጥበትን መለኮታዊ ጉልበትና አጥር ይሆንልናል።
ወዳጆቼ ሆይ
አሁኑኑ ካለንበት ድንዛዜና ምቾት ተነስተን የምህረት እጅ የደገፈን የብርሃኑ ሕይወት የበራልን የእግዚአብሔር ልጆች ነን።
የአባታችን ቤት የአምልኮ የፈውስ የነጻነትና የክብር ስፍራ ነው።
እግሮቻችን ወደ እግዚአብሔር ቤት ይገስግሱ አሁኑኑ እንነሳና ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሩጥ
ነቢይት ቅድስት ከትውልድ ማስነሳት ቤተክርስትያን