Prophetess kidist markos

Prophetess kidist markos prophetess kidist markos is a women of God whom God has raised for the people of Ethiopia.
(3)

በፍቅር የተዋጠ ግዴታ ❤️ ❤️ ❤️ ወደ እግዚአብሔር ቤት መሄድ በሳምንት አንድ ቀን የሚፈጸም ሃይማኖታዊ ልማድ ወይም በሕግ ተገዶ የሚከፈል የዕዳ ክፍያ አይደለም። ወደ እግዚአብሔር ቤት መገ...
24/05/2026

በፍቅር የተዋጠ ግዴታ ❤️ ❤️ ❤️
ወደ እግዚአብሔር ቤት መሄድ በሳምንት አንድ ቀን የሚፈጸም ሃይማኖታዊ ልማድ ወይም በሕግ ተገዶ የሚከፈል የዕዳ ክፍያ አይደለም።
ወደ እግዚአብሔር ቤት መገስገስ በፍቅር የተዋጠ ግዴታ እና በግዴታ የተደገፈ ውዴታ ነው።
አንድ ሕፃን ልጅ ለመኖር መተንፈስ ግዴታው እንደሆነ ሁሉ የክርስቶስ ሕይወት በውስጡ ያለ የተጠማ አማኝም ወደ አባቱ ቤት መሄድ የነፍሱ መተንፈሻ ነው። ሕጉ ሳይሆን ፍቅሩ ያስገድደዋል።
ዳዊት የዚህን ምስጢር ሲገልጠው፡ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ (መዝሙር 122፥1) ይላል። ዳዊት ወደ ቤተ መቅደስ የሮጠው ንጉሣዊ ፕሮቶኮል አስገድዶት ሳይሆን በውስጡ ባለው መለኮታዊ ናፍቆትና ፍቅር ተውጦ ነው።
ፍቅር ግዴታን ወደ ታላቅ ደስታ ይለውጠዋል
የእግዚአብሔር ቃል፡ አንዳንዶችም እንደሚያደርጉት መሰብሰባችንን አንተው (ዕብራውያን 10፥25) በማለት ያዝዘናል። ይህ ትእዛዝ (ግዴታ) ስሜታችን በሚደክምበት ቀን ወደ እግዚአብሔር ቤት የምንሮጥበትን መለኮታዊ ጉልበትና አጥር ይሆንልናል።

ወዳጆቼ ሆይ
አሁኑኑ ካለንበት ድንዛዜና ምቾት ተነስተን የምህረት እጅ የደገፈን የብርሃኑ ሕይወት የበራልን የእግዚአብሔር ልጆች ነን።
የአባታችን ቤት የአምልኮ የፈውስ የነጻነትና የክብር ስፍራ ነው።
እግሮቻችን ወደ እግዚአብሔር ቤት ይገስግሱ አሁኑኑ እንነሳና ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሩጥ

ነቢይት ቅድስት ከትውልድ ማስነሳት ቤተክርስትያን

ምናሴያችሁ በደጃችሁ ነው።ዛሬ በታላቅ እምነት በተስፋና በእግዚአብሔር ዘላለማዊ ታማኝነት ላይ ቆሜ ከትናንት ስብራትና ከዛሬ ጨለማ በላይ ከፍ የሚል ድንቅ አዋጅ በሕይወታችሁ ላይ አውጃለው። ይ...
21/05/2026

ምናሴያችሁ በደጃችሁ ነው።
ዛሬ በታላቅ እምነት በተስፋና በእግዚአብሔር ዘላለማዊ ታማኝነት ላይ ቆሜ ከትናንት ስብራትና ከዛሬ ጨለማ በላይ ከፍ የሚል ድንቅ አዋጅ በሕይወታችሁ ላይ አውጃለው።

ይህ ቃል ዘመናችሁን ወደማሻገርና መከራችሁን ወደማስረሳት ምዕራፍ ያሻግራችኋል።
የእግዚአብሔር ጉብኝት የደረሰለት ሰው የትናንቱን ጩኸት አይለማመድም። ዛሬ በሕይወታችሁ በቤታችሁና በአገልግሎታችሁ ላይ ምናሴ ይወለዳል።
ዮሴፍ ያስተናገደው የመሸጥ በሐሰት የመወንጀልና በባዕድ ምድር የመንከራተት ዘመናት በዮሴፍ ላይ እንዳበቃ ሁሉ
በሕይወታችሁ ላይ ተጭነው የነበሩ አያልፉም የሚያስባሉ ክፉ ቀናቶች ዛሬ ፍጻሜያቸውን አግኝተዋል።

የባርነትና የወህኒ ቤት ልብሳችሁ ተገፎ የክብርና የባለስልጣን ልብስ የምትለብሱበት የታሪካችሁ ምዕራፍ የሚቀየርበት አዲስ ቀን ሆኖ ታውጆላችዋል

የእግዚአብሔር ካሳ ሲመጣ የዓመታት መከራ በአንድ ቀን ስኬት ይረሳል እግዚአብሔር ሲያበራው የማይነጋ የመሰለው ጨለማ ሁሉ እንደ ሕልም ያልፋል።

እግዚአብሔር ያስረሳል ሲል ታሪኩን ከአእምሯችን ያጠፋዋል ማለት ሳይሆን በትናንቱ ስብራት ላይ አዲስ የክብር ምዕራፍ እየጻፈ ሕመሙን ያጠፋዋል ማለት ነው።

ዛሬ እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ድንቅ ነገር ያደርጋል።
በትላንት ስብራታችሁ ላይ አዲስ የክብር ምእራፍ ተፃፈ።

መከራ የሚያስረሳ የእንባችሁን ዘመን የሚያበቃ ፍጹም ሰላምና መጽናናትን የሚሰጥ መለኮታዊ አዋጅ በላያችሁ ላይ ጸና።
እግዚአብሔር በእውነት ያስረሳችኋል ።
ጨለማው የቱንም ያህል ቢበረታ መከራ የሚያስረሳው
የእግዚአብሔር የብርሃን አዋጅ ማለዳ መውጣቱ አይቀርም።

ነቢይት ቅድስት ከትውልድ ማስነሳት ቤተክርስትያን

የምድር አበቦች ተገለጡ የዜማም ጊዜ ደረሰ (መኃልየ መኃልይ 2:12)🌸 የተፈጥሮ ውበትና የፈጣሪ ድንቅ ጥበብ 🌸ዛሬ ዓይኖቼ በአበቦች በተሸለመች በተፈጥሮ እቅፍ ውስጥ በለመለመች ምድር ላይ አ...
19/05/2026

የምድር አበቦች ተገለጡ የዜማም ጊዜ ደረሰ
(መኃልየ መኃልይ 2:12)

🌸 የተፈጥሮ ውበትና የፈጣሪ ድንቅ ጥበብ 🌸

ዛሬ ዓይኖቼ በአበቦች በተሸለመች በተፈጥሮ እቅፍ ውስጥ በለመለመች ምድር ላይ አረፉ ልቤም በፈጣሪ ታላቅነት ተደነቀ
እኔ ለአበቦች ያለኝ ፍቅር ልዩ ነው።
አበቦች የፈጣሪ የውበት ቀለም የምድር ፈገግታዎች ናቸው። የነሱ መፈንጠቅ የየቀለማቱ ውህደትና ልዩ መዓዛ ነፍስን የማደስ ድንቅ ኃይል አለው።
ብዙ ጊዜ በአኗኗራችንና በሃሳብ ስንባክን እንውላለን ነገር ግን ቆም ብለን እንዲህ ያለውን የተፈጥሮ ድንቅ ስራ ስንመለከት አእምሯችን በአዲስ ተስፋ ይታደሳል ውስጣችንም ሰላምን ያገኛል።
ይሄ ዝም ብሎ እይታ አይደለም የፈጣሪን ፍቅርና ጥበብ የምናይበት ድንቅ መገለጥ እንጂ
አዎየሜዳ አበቦችን እንዲህ አሳምሮ የሸለመ ይሄ ጌታ የእኛንም ሕይወት በውበትና በበረከት የመሙላት አቅም አለው። ይህንን ድንቅ ተፈጥሮ አይቶ እግዚአብሔርን ያለማመስገን አይቻልም ።

ከምድር መመረኮዝ ጀርባ ያለው ስውር ጦርቆም ብለን እናስብ?ሕይወት ስትከብደን መንገዱ ሲያዳልጠን የምንመረኮዘው ጠንካራ የሚመስል ነገር እንፈልጋለን። ብዙ ጊዜ ግን ምርጫችን በዙሪያችን ያሉ ሰ...
18/05/2026

ከምድር መመረኮዝ ጀርባ ያለው ስውር ጦር
ቆም ብለን እናስብ?
ሕይወት ስትከብደን መንገዱ ሲያዳልጠን የምንመረኮዘው ጠንካራ የሚመስል ነገር እንፈልጋለን። ብዙ ጊዜ ግን ምርጫችን በዙሪያችን ያሉ ሰዎች ሥልጣን ገንዘብ ወይም ምድራዊ ተስፋዎች ይሆናሉ።
ነገር ግን ይህ ጥቅስ አንድ አስደንጋጭ እውነት ይነግረናል የሰዎችና የምድር ትዕግሥትም ሆነ አቅም እንደ ሸምበቆ ነው።
2ኛ ነገሥት 2፥21
እነሆ፥ በዚህ በተቀጠቀጠ በሸምበቆ በትር በግብፅ ትታመናለህ፤ ሰው ቢመረኰዘው ተሰብሮ በእጁ ይገባል ያቈስለውማል፤ የግብፅ ንጉሥ ፈርዖን ለሚታመኑበት ሁሉ እንዲሁ ነው።

በታሪክ ታላላቅ መንግሥታትና ነገሥታት በጦርነት አውድማ ላይ ሲጨነቁ መጀመሪያ ዓይናቸውን የሚጥሉት ወደ ግብፅ ነበረ። ግብፅ በሰረገላዎቿ ብዛት በፈረሰኞቿ ጉልበትና በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በበቀለው የሸምበቆ አጥር የተከበበች የምድር ኃይል ምሳሌ ነበረች።
ከሩቅ ሲያዩት በዓባይ ዳርቻ የበቀለው ሸምበቆ ጥቅጥቅ ያለ ቀጥ ብሎ የቆመና ለመረገጫም ሆነ ለመመረኮዣ የሚበጅ የአጥር ግንብ ይመስላል።
ነገር ግን ታሪክና መለኮታዊው ቃል አንድን አስደንጋጭ እውነት ይገልጡልናል የሸምበቆ እውነተኛ ተፈጥሮው ባዶነቱ ነው።

ይህ ታሪክ በነገሥታት ዘመን የተፈጸመ የፖለቲካ ውድቀት ብቻ አይደለም ዛሬም በየቀኑ በሕይወታችን የሚደገም መንፈሳዊ እውነታ ነው። ሰውን ሥርዓትን ምድራዊ ፍቅርንና ቁሳቁስን የመረኮዙ ሁሉ መጨረሻቸው እጃቸው ላይ በገባ ስብራት ማልቀስ ሆኗል።

ክርስቶስ ኢየሱስ ወደዚህ ምድር የመጣው ግን ይህንን ምርኩዝ እንድንቀይር ነው። እርሱ እንደ ሸምበቆ በውስጡ ባዶ አይደለም መለኮታዊ ሙላት ነው። እርሱ እንደ ሸምበቆ በነፋስ አይወዛወዝም ትናንትም ዛሬም እስከ ዘላለምም ያው የማይናወጥ ማዕዘን ነው።

ሸምበቆ ከሩቅ ሲያዩት ቀጥ ያለ የማያወለዳና ሊደግፍ የሚችል ይመስላል። ነገር ግን ከባድ ሸክም ሲያርፍበት መቋቋም አይችልም ይሰበራል። የሚገርመው ግን መሰበሩ ብቻ አይደለም ተሰብሮ መሬት ላይ አይወድቅም—ወደ መረከዘው ሰው እጅ ገብቶ ያቆስለዋል።

ያኔ የሸምበቆውን መለስተኛ ተፈጥሮ እንረዳለን።
በሰው መታመን መጨረሻው መሰበር ብቻ ሳይሆን መወጋትና መቁሰልም ጭምር ነው። ሰውን ስንመረኮዝ ክብደታችንን በሙሉ እሱ ላይ ስናደርግ ሸክማችንን መሸከም የማይችለው ያ ሰው ሲሰበር ስብራቱ እኛኑ ይወጋናል።

​ዛሬ እኛስ ምንድ ነው የተመረኮዝነው?
ፈራሽና ተሰባሪ የሆነውን የሰውን ትከሻ ወይስ ፈጽሞ የማይናወጠውን የእግዚአብሔርን ክንድ?

​ዛሬ ቆም ብለን እናስብ። መቁሰልና ማዘን የሚቀረው ምርኩዛችንን ከተደገፉናቸው በኋላ ከሚወጉን ምድራዊ ሸምበቆዎች ላይ አንስተን ዘላለም ጸንቶ በሚኖረው በማይናወጠው ዓለት ላይ ስናደርግ ብቻ ነው።
​በሰው ከመታመን ይልቅ በእግዚአብሔር መታመን ይሻላል። (መዝሙር 118፥8)

ነቢይት ቅድስት ከትውልድ ማስነሳት ቤተክርስትያን

እግዚአብሔር እኮ ለቃሉ ታማኝ ነው ።
16/05/2026

እግዚአብሔር እኮ ለቃሉ ታማኝ ነው ።

ለምድር መሞት ለሰማይ መንቃት ​ዓለም ስታወድስህ ካልፈነጠዝክ ስትሰድብህም ካልተሰበርክ አንተ ለዓለም ሞተሃል ለሰማይ ነቅተሃል ። የሞተ ሰው በፊቱ ወርቅ ቢነሰነስለት አይነሳም ጭቃ ቢቀባም አ...
15/05/2026

ለምድር መሞት ለሰማይ መንቃት
​ዓለም ስታወድስህ ካልፈነጠዝክ ስትሰድብህም ካልተሰበርክ አንተ ለዓለም ሞተሃል ለሰማይ ነቅተሃል ።
የሞተ ሰው በፊቱ ወርቅ ቢነሰነስለት አይነሳም ጭቃ ቢቀባም አይቆጣም።
አንተም ለዚህ ዓለም ክብርና ውርደት እንዲህ ስትሆን በምድር ላይ ያለህ ሰማያዊ ነፃ አውጪ ትሆናለህ። ሰማይ የሚገዝፈው ምድር በልብህ ውስጥ ስትሞት ብቻ ነውና።
​ለዝና የምትሞት ነፍስ የሌሎችን ሰዎች ምስጋና እንደ አየር ትፈልጋለች ሰዎች ዝም ሲሉ ግን ትታፈናለች።
ይህም የዘላለም ረሃብ ነው። ዓለም ሁሉን ስትይዝ ትከብራለህ ትላለች ሰማይ ግን ሁሉን ስትተው ትበልጣለህ ይላል።
ይህንን እውነት የጨበጠ ሰው ምድርን ረግጦ ሰማይን የተጎናጸፈ ድንቅ ፍጥረት ነው።
1ኛ ዮሐንስ 2፥16-17
ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም።
17: ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።

ነቢይት ቅድስት ከትውልድ ማስነሳት ቤተክርስትያን

መሰላሉን የረሱት የሰገነት ላይ ሰዎች​ዘጠኙስ ወዴት አሉ? (ሉቃስ 17፡17)​በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ውስጥ ዐሥር ለምጻሞች በጭንቅ ሰዓት በአንድ ድምፅ ማረን  ብለው ጮኹ ሁሉም ተፈወሱ። ነገር...
11/05/2026

መሰላሉን የረሱት የሰገነት ላይ ሰዎች
​ዘጠኙስ ወዴት አሉ? (ሉቃስ 17፡17)
​በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ውስጥ ዐሥር ለምጻሞች በጭንቅ ሰዓት በአንድ ድምፅ ማረን ብለው ጮኹ ሁሉም ተፈወሱ።
ነገር ግን ታሪካቸው ሲቀየር ቆዳቸው ሲታደስና ወደ ማኅበረሰቡ የመቀላቀል የስኬት ሰገነት ላይ ሲወጡ ዘጠኙ የወጡበትን መሰላል ረሱት። ዛሬም በሕይወት ሰገነት ላይ ሆነው መሰላሉን ገፍትረው የጣሉ ትላንትን በዛሬ ብርሃን የሸፈኑ ብዙዎች ናቸው።

​ብዙዎች ፎቅ ላይ ሲደርሱ ዐይናቸው የሚያርፈው አድማሱ ላይ ብቻ ነው። የወጡበትን መሰላል ብቻ ሳይሆን ወደ ላይ እንዲወጡ የተዘረጉ ደጋፊ እጆች ጭምር ይረሳሉ።
በጨለማ ውስጥ ሆነህ በጸሎትና በዋጋ ክፍያ የከፈትክላቸውን በር ቆመው ሲገቡበት በጥረቴ መጣሁ የሚል የትዕቢት ካባ ይለብሳሉ።
​ይህ ግን ስኬት ሳይሆን የመንፈሳዊ ውድቀት አውራ ጎዳና ነው። መፅሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል
​እንግዲህ ምን ይልሃል? ያልተቀበልኸውስ ምን አለህ? የተቀበልህ ከሆንህ ግን እንዳልተቀበልህ የምትመካው ስለ ምንድር ነው?
(1 ቆሮ. 4፡7)
​ማንኛውም ስኬት በሌላው ሰው ጸሎት ምክርና ድጋፍ ላይ የቆመ መሆኑን መዘንጋት መሰረት የሌለውን ቤት እንደ መገንባት ይቆጠራል።
መሰላሉን ገፍትሮ የጣለ ሰው መውረጃው ሲመጣ መቆሚያ እንደማይኖረው ይዘነጋል።

​አንዳንዶች ዋጋ የከፈለላቸውን ሰው ስም ማንሳት ክብራችንን ይቀንሳል ብለው ያስባሉ። ስኬታቸውን ከራሳቸው ብቃት ጋር ብቻ ማያያዝ ይፈልጋሉ። ነገር ግን ምስጋና ቢስነት በረከትን ያመክናል።


​ለሰዎች ስኬት ሻማህን አቅልጠህ እነሱ ግን ብርሃን ሲበራላቸው እንደ ባዕድ ቢገፉህ አትዘን። ያንተ የክፍያ መዝገብ ያለው በሰው ኪስ ሳይሆን በሰማይ አባት ዘንድ ነው። ሰዎች ቢረሱህም የጸለየው መንፈስህና የፈሰሰው እንባህ በእግዚአብሔር መዝገብ ላይ በማይጠፋ ቀለም ተጽፏል።
​ትልቁ ስኬትህ እነሱ አንተን ማስታወሳቸው ሳይሆን አንተ ለእነሱ መባረክ ምክንያት መሆንህ ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል

እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና። (ዕብ. 6፡1

ለእንደነዚህ አይነት ሰዎች ምክር አለኝ
​ዛሬ በብርሃን ላይ ስትቆም በጨለማ ውስጥ ሆኖ ስለ አንተ የጸለየውን ሰው አትዘንጋ።
ሰዎች ስምህን ሲያከብሩት ስምህ እንዲከበር በጌታ ፊት ስምህን በለቅሶ ሲጠራ የነበረውን ልብ አስብ።

​ ያለ ማንም ረዳት ብቻህን የቆምክ ቢመስልህም ያንተ ሆኖልኛል በሌላው ይሁንለት ጸሎት ላይ የቆመ መሆኑን ማወቅ እውነተኛ ትሕትና ነው።

​ትልቁ ድህነት በኪስ ምትፈልገውን ማጣት ሳይሆን ለተደረገልህ መልካም ነገር አመሰግናለሁ የሚል ልብ ማጣት ነው።
​በጨለማ ውስጥ ሆኖ ሻማህን የለኮሰልህን ሰው ብርሃን ሲበራልህ ልታየው ካልፈለግህ ብርሃኑም ውበት አይኖረውም።
​ሰው ቢረሳህም እግዚአብሔር ግን የታማኞች ዋጋ ከፋይ ነው። መሰላሉን የረሱት ሰዎች በሰገነቱ ላይ ለጊዜው ቢደምቁም መሰላሉን የሆኑት ቅኖች ግን በሰማይ ለዘላለም ይመሰገናሉ።

ነቢይት ቅድስት ማርቆስ ከትውልድ ማስነሳት ቤተክርስትያን

መልካም የእናቶች ቀን ይሁንልሽ ሁሌም በደስታ እና በጤና አጠገቤ በመሆንሽ በጣም ደስ ይለኛል። ስለ ሁሉም ነገር አመሰግናለሁበጣም እወድሻለሁ።
10/05/2026

መልካም የእናቶች ቀን ይሁንልሽ ሁሌም በደስታ እና በጤና አጠገቤ በመሆንሽ በጣም ደስ ይለኛል።
ስለ ሁሉም ነገር አመሰግናለሁበጣም እወድሻለሁ።

ጌታ መልካም ጊዜ ይሰጠናል ።
09/05/2026

ጌታ መልካም ጊዜ ይሰጠናል ።

የሰው ልጅ ብዕር ተስፋ የለም ብሎ ነጥብ በጣለበት ስፍራ የእግዚአብሔር ስልጣን ግን ንዑስ አንቀጽ ይጨምራል። ማንም ሊዘጋው የማይችለው ደጅ ሲከፈት የቆየው የልብ ጭንቀት ልክ እንደ ጠዋት ጸዳ...
07/05/2026

የሰው ልጅ ብዕር ተስፋ የለም ብሎ ነጥብ በጣለበት ስፍራ የእግዚአብሔር ስልጣን ግን ንዑስ አንቀጽ ይጨምራል።
ማንም ሊዘጋው የማይችለው ደጅ ሲከፈት የቆየው የልብ ጭንቀት ልክ እንደ ጠዋት ጸዳል በደስታ ይተካል።
የዚህ ሳምንት መጨረሻዎ በሰው ጥበብ የማይፈታ ነገር ግን በእግዚአብሔር ተአምራት የታተመ ድንቅ የታሪክ መዝጊያ ይሆናል።
ከትውልድ ማስነሳት ቤትክርስትያን ።

ዛሬ ማክሰኞ እና ነገ እሮብ በነዚህ ቀናት እግዚአብሔር የልቡን ፈቃድ በመካከላችን ይፈፅመዋል ። ሁላችሁም ተጋብዛችዋል ታላቅ የኃይል ተካፍሎ ይሆንልናል
05/05/2026

ዛሬ ማክሰኞ እና ነገ እሮብ በነዚህ ቀናት እግዚአብሔር የልቡን ፈቃድ በመካከላችን ይፈፅመዋል ።
ሁላችሁም ተጋብዛችዋል ታላቅ የኃይል ተካፍሎ ይሆንልናል

Address

ሰሚት ፊየል ቤት 20 ሜትር ወደ ዘመን ባንክ ሲሄዱ ኦ ቱ ሬስቶራንት 200 ሜትር ገባ ብሎ
Addis Ababa
1000

Telephone

+251912243838

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prophetess kidist markos posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Prophetess kidist markos:

Shortcuts

Share