Orthodox "Spiritual Question"

Orthodox "Spiritual Question" ይህ ዓምድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮችን የመፅሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶች የሚስተናገዱበት ብቻ ነው፡፡

19/04/2023

ጥያቄ ቁጥር ፵፪/ 42

15/12/2017

ካነበብኩት ~~~💯💯💯💯💯💯

ወደ ቤተክርስቲያን ስንመጣ እግዚአብሔርን ብለን እንጂ ሰባኪ እከሌ መጥቷል ብለን ልመጣ እንደማይገባን እንዲህ በማለት መክረውናል፦ወደ ቤተክርስቲያን ስትመጡ አየለ ከበደ ይሰብካል የሚለውን ትታችሁ እግዚአብሔርን ብላችሁ ኑ። እግዚአብሔር ለእናንተ ትምህርት አያጣም። ሆቴል እሚኬደው አስተናጋጅ ለማየት አይደለም ምግብ ለመብላት እንጂ። አስተናጋጅ ለማየት የሄዱት ወፍረው ሳይሆን ከስተው ነው የመጡት በልተው ሳይሆን ተበልተው ነው የመጡት።

ሰለዚህ ቤተክርስቲያን ስመጡ እንትና ቀደሰ እንትና ይሰብካል ባላችሁ አትምጡ ይሄ የሰነፍ ሰው ጠባይ ነው። እኛ መጣን ቀረን ምን አስጨነቃችሁ። እኛም በሽተኞች ነን እናንተም በሽተኞች ናችሁ የተገናኘነው ሃኪም ቤት ነው ሃኪሙ ደግሞ እግዚአብሔር ነው።

እኛ ትንሽ ቀዥቀዥ ብለን ማብራራት ጀመርን እንጂ ዶክተሩ እግዚአብሔር ነው። ሃኪም ቤታችን ቤተክርስቲያን ናት። አሁን ወደ ቤታችሁ ስትግቡ እንትና ሰብኮ እንትና አስተምሮ አትበሉ እግዚአብሔር ነገረኝ አስተማረኝ በሉ። አስተማሪ ማን ነው? እግዚአብሔር ነው።

ተናጋሪ ማን ነው እግዚአብሔር ነው።
ፈጣሪን ብቻ ያዙ ሌላ ሰው ላይ አትንጠልጠሉ።

እንደው አንዳንድ ሰው አለ በሰርግ ላይ ሙሽራውን ትቶ ሚዜ ላይ የሚያፈጥ። መታየት ያለበት እኮ ሙሽራ ነው። የቤተክርስቲያን ሙሽራዋ ማን ነው? ክርስቶስ ነው።

እኛ ምንም ማለት አይደለንም የሠርግ ቤት አውደልዳዮች ነን።
ለቀቅ አድርጉን እኛን በመድኀኒዓለም።

እርሱ ላይ ተጣበቁ ቁስሉ ፈውስ ነው፣ ችንካሩ ፈውስ ነው፣ ሃሞት ኮምጣጤው ፈውስ ነው፣ ግርፋቱ እጅ እግሩ ፈውስ ነው፣ ቃሉ ፈውስ ነው፣ የተሰበረውን ይጠግናል ያለቀሱትን እንባ ያብሳል፣ የወደቁትን ያነሳል፣ የጎደለ ይሞላል። እኔ ምን የጎደለ እሞላላችኋለው ወገኖቼ? ለራሳችን ጎሎብን እኮ እየተሰቃየን ነው ።

በመምህራችን ላይ አድሮ የመከረን የገሰፀን
እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን
ለመምህራችን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን አሜን

ጥያቄ ቁጥር፡ ፵፩/41
10/11/2014

ጥያቄ ቁጥር፡ ፵፩/41

ጥያቄ ቁጥር፡  ፵/40
08/11/2014

ጥያቄ ቁጥር፡ ፵/40

05/03/2012
27/10/2011
ጥያቄ ቁጥር፡ ሠላሳ ዘጠኝ
26/10/2011

ጥያቄ ቁጥር፡ ሠላሳ ዘጠኝ

ጥያቄ ቁጥር፡ ሠላሳ ስምንት
06/10/2011

ጥያቄ ቁጥር፡ ሠላሳ ስምንት

ጥያቄ ቁጥር፡ ሠላሳ ሰባት
04/10/2011

ጥያቄ ቁጥር፡ ሠላሳ ሰባት

Address

Addis Ababa

Telephone

+251900007555

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Orthodox "Spiritual Question" posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to Orthodox "Spiritual Question":

Share