19/03/2024
" إن الحسنات يذهبن السيئات ذلك ذكرى للذاكرين "
"በእርግጥም መልካም ስራ መጥፎ ስራን ያብሳል።" /ሁድ፣ 114/
★★★ ★★★ ★★★
ምንጊዜም መዕሲያ በሰራህ ጊዜ ለራስህ:– "ዘመቻው ላይ ለጊዜው ተረትቻለሁ፣ ነገር ግን ዋናውን ጦርነት አልተሸነፍኩም! " በል።
ቁምና ዉዱእ አድርገህ ሁለት ረከዓ በመስገድ ለማገገም ሞክር።
ወንጀል የፈፀምክባቸውን ጣቶችህ ኢስቲግፋር ቁጠርባቸው፤
ሐራም በተመለከትክበት አይንህ ቁርአንን አንብብበት።
አላህ ዘንድ የፀፀተኞች ለቅሶና መዋደቅ ከሷሊሖች ጣዓ አይተናነስም።
እናም አላህ _ሱብሐነሁ ወተዓላ_ራሱን (አልገፉር) ብሎ የጠራው ወደሱ እንድትመለስ ስለሚፈልግ ብቻ ነውና እጅ አትድጥ።
#ረሳኢሉን ሚን አልቁርኦን
ነስሩ ከድር