Apostolic Generation Christian Ministry

Apostolic Generation Christian Ministry Let's Preach The Gospel of Christ to Every Nation!

እግዚአብሔር ይመስገን። አሁንም እግዚአብሔር ይነሳ🙏👉1 ዜና 16፡10፤ በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው።   17፤ ለያዕቆብ ሥርዓት እንዲሆን ለእስራኤልም የዘላ...
14/05/2026

እግዚአብሔር ይመስገን። አሁንም እግዚአብሔር ይነሳ🙏
👉1 ዜና 16፡10፤ በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። 17፤ ለያዕቆብ ሥርዓት እንዲሆን ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን እንዲሆን አጸና፤ 18፤ እንዲህም አለ፡— ለአንተ የከነዓንን ምድር የርስታችሁን ገመድ እሰጣለሁ፤ 19፤ ይህም የሆነው እነርሱ በቍጥር ጥቂቶች ሰዎች፥ እጅግ ጥቂቶችና ስደተኞች ሲሆኑ ነው። 20፤ ከሕዝብ ወደ ሕዝብ፥ ከመንግሥትም ወደ ሌላ ሕዝብ አለፉ።

📌አሁንም እግዚአብሔር መመንጠር ያለበትን መንጥሮ፣መቆረጥ ያለበትን ቆርጦ፣መገደል ያለበትን ገድሎ፣በደሙ ዋጃትን የተቀደሰ ህዝቡን ከውድቀት ከዘንዶ መንጋጋ ያወጣል።🙏
👉ኢሳይያስ 51:9፤ የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፥ ተነሥ፥ ተነሥ፥ ኃይልንም ልበስ፤ በቀድሞው ወራትና በጥንቱ ዘመን በነበረው ትውልድ እንደ ሆነው ተነሥ። ረዓብን የቈራረጥህ ዘንዶውንም የወጋህ አንተ አይደለህምን? 10፤ ባሕሩንና የታላቁን ጥልቅ ውኃ ያደረቅኸው፥ የዳኑትም ይሻገሩ ዘንድ ጠሊቁን ባሕር መንገድ ያደረግህ አንተ አይደለህምን?

እግዚአብሔር ስሙ ለዘላለም ይባረክ!

እግዚአብሔር ብቻውን መራው ፤ ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም። ዘዳ 32፥12 ቃሉ የጸና ነው።እግዚአብሔር ብቸኛ መሆኑን ለሚጠራጠሩ ሰዎች አሁንም አትጠራጠሩ እግዚአብሔር ብቸኛ አምላክ ...
10/05/2026

እግዚአብሔር ብቻውን መራው ፤ ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም። ዘዳ 32፥12 ቃሉ የጸና ነው።

እግዚአብሔር ብቸኛ መሆኑን ለሚጠራጠሩ ሰዎች አሁንም አትጠራጠሩ እግዚአብሔር ብቸኛ አምላክ ነው።

በመጽሐፍ ቅዱስ በተለያዩ ቦታ እግዚአብሔር እነ ብቸኛ ነኝ ፡ከእኔ በፊት አምላክ አልተሠራም ከእኔም በኋላ አይሆንም። ብሎ በተለያዩ ቦታ ገልጸዋል።

ያ ብቸኛ አምላክ ነው የመጣው ሌላ ሁለተኛ አካል አይደለም። ኢሳ 59፥15 እግዚአብሔርም አየ፥ ፍርድም ስለሌለ ተከፋ። ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው። ጽድቅንም እንደ ጥሩር ለበሰ፥ በራሱም ላይ የማዳንን ራስ ቍር አደረገ፤ የበቀልንም ልብስ ለበሰ፥ በቅንዓትም መጐናጸፊያ ተጐናጸፈ። *

ስለዚ ለሰው ልጅ ኃጥያት ስጋ ለብሶ ወደ ምድር የወረደው ከወረደ ቦኃላ ሞትን አሸንፍ ወደ ሰማይ ያረገው ያ ብቸኛው አምላክ ራሱ ነው።

@የአንድ አምላክ ልጆች

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ! የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በምስራቅ አያት አጥቢያ የህብረት መዘምራን የተዘጋጀውን “ዛሬም ኢየሱስ ሙላቴ” የተሰኘውን የህብረት...
20/04/2026

ሰላም ለቅዱሳን በሙሉ!

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በምስራቅ አያት አጥቢያ የህብረት መዘምራን የተዘጋጀውን “ዛሬም ኢየሱስ ሙላቴ” የተሰኘውን የህብረት ዝማሬ ቁጥር 2 አልበም ሲያቀርብላችሁ በታላቅ ደስታ ነው።

ለእግዚአብሔር ክብር፣ ለብዙዎች መታነጽና መጽናናት እየሆነ ያለው የዝማሬ ጸጋ አሁንም በተለያየ አቅጣጫ እያደገና እየሰፋ ስላለ ክብር ይህንን ጸጋ ለሚያፈስሰው የብርሃናት አባት ይሁን!

የዝማሬ አልበሞችን ለማዘጋጀት ብዙ መስዋዕትነትን ይጠይቃልና ይህንን የዝማሬ አልበም በታላቅ ያዘጋጁትና መዘምራንን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ሁሉ የቤተክርስቲያን አምላክ ኢየሱስ በማያልቀው በረከት እንዲባርክ ጸሎታችንም ምኞታችንም ነው።

አልበሙ በቅርብ ቀናት ውስጥ በApostolic Songs መተግበሪያ ላይ ዝግጁ የሚሆን ሲሆን ቅዱሳን ሁሉ ዝማሬዎቹን በተለያዩ የግዢ አማራጮች በማውረድ ጸጋውን፣ ቤተክርስቲያንን እና አገልግሎቱን ትደግፉ ዘንድ በኢየሱስ ፍቅር እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን
ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
ሚያዚያ 2018 ዓ.ም
Apostolic Songs

28/03/2026

#ኢየሱስ ሕይወት ሰላም የሆነልኝ

 113 አድስ ነፍሳት ተጨመሩ በአጠቃላይ 12,409 ሰዎች በሐዋርያት ትምህርት ተጨመሩ።በዓለም አቀፍ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን 35ኛው ዙር ዋራ በቴል ጉባኤ ከ መጋቢት 3-6/2018 ዓ.ም በ...
22/03/2026


113 አድስ ነፍሳት ተጨመሩ በአጠቃላይ 12,409 ሰዎች በሐዋርያት ትምህርት ተጨመሩ።

በዓለም አቀፍ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን 35ኛው ዙር ዋራ በቴል ጉባኤ ከ መጋቢት 3-6/2018 ዓ.ም በታላቅ መንፈሳዊ ጉብኝት ተካሄደ።

በጉባኤ 12,296 አድስ ነፍሳት በሐዋርያት ትምህርት እንደተጨመሩ የተነገረው ስሆን ይህ ሪፖርት የተነገረው በ እሁድ ጉባኤ ከምሳ መልስ ስሆን እስከ ማጠቃለያ ባለው ግዜ 113 ነፍሳት በሐዋርያት ትምህርት የተጨመሩ መሆኑን ስንሰማ እጀግ ደስ ብሎናል።

በአጠቃላይ በ ኮንፈረንሱ 12,409 አድስ ነፍሳት በሐዋርያት ትምህርት ተጨመሩ።
ገና ነው ተአምራቱ
እግዚአብሔር ይመስገን 🙏
ወንድማችሁ ነኝ

የዘማሪ ዶ/ር    መልዕክት! ይነበብ!"ወዳጄና ጋደኛዬ ትሁቱ የእግዚአብሔር ሰው፣ የአሁኑ የኢትዮጵያ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ ቢሾፕ ኢሳያስ አሻ አሁን የደረሰበት የሀላፊነት ...
16/03/2026

የዘማሪ ዶ/ር መልዕክት! ይነበብ!

"ወዳጄና ጋደኛዬ ትሁቱ የእግዚአብሔር ሰው፣ የአሁኑ የኢትዮጵያ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ ቢሾፕ ኢሳያስ አሻ አሁን የደረሰበት የሀላፊነት ደረጃ የደረሰው ፣ በሄደበተት የቅንነት መንገድና ለእግዚአብሔር በተሰጠ ህይወቱ ነው። ከወንም ኢሳየያስ /ቢሾፕ / ጋር ከ35 ዓመታት በላይ በጣም በቅርበት እንተዋወቃለን፣ በሚገባ አውቀዋለሁ እሱም እንዲሁ ያውቀኛል። በተለይ የበለጠ እንድንቀራረብ እና አዉቀዋለሁ ለማለት ያስቻለኝ ምክንያት፣ የአዲስ አበባ ሰበካ የወጣትች መሪ ሆነን ባገለገልንበት ወቅት አብረን ስናገለግል ብዙ የመቀራረብ በተደጋጋሚ አብሮ የማገልገል አጋጣሚው ሰፊ ነበር።ወንም ኢሳያስ /ቢሾፕ/ ንፁህ ልብ እና በጎ ህሊና ያለው በሳል ሰው፣ ማስመሰል ጨርሶ የማይታይበት፣ ላመነው ብቻ የሚኖር፣ ለመሪዎቹ አክብሮት ያለው፣ ሰዎችን ከልቡ የሚወድ፣ የአገልጋይነትና የመሪነት ፀጋ የተጎናጸፈ፣ የእውቀት ሰው በሁኔታዎች በዝቅታ እና በከፍታ የማይለዋወጥ ባለራእይ ነው።ዛሬ ለደረሰበት የአገልግሎት ደረጃ የሚመጥን ፀጋም ሆነ እውቀት የተጎናጸፈ የእዚአብሔር ባሪያ ነው። ቀደም እንዳሉት አስደናቂ መሪዎች እግዚአብሔር በእሱም ቤተክርስቲያን ወደሚቀጥለው ምእራፍ ያሻግራል።ገና ከጅምሩ በዋራ 12,994 ሰዎች መጠመቃቸው እግዚአብሔር ከሱ ጋር ስለመሆኑ ምልክት ነው። ይህንን ዜና በምድረ አሜሪካ ሆኜ በሶሻል ሚዲያ ስሰማ ስለሰራው ድንቅና ስለዳኑት ነፍሳት እግዚአብሔርን አመስግኜአለሁ።ወዳጄ እና ውዱ ጋደኛዬ ይከናወንልህ።"

16/03/2026

Apostolic Church of Ethiopia: 12,296 baptized in “Jesus name” in 3 day Wara Bethel Crusade.

Address

Gofa Sefer
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Apostolic Generation Christian Ministry posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share