14/05/2026
እግዚአብሔር ይመስገን። አሁንም እግዚአብሔር ይነሳ🙏
👉1 ዜና 16፡10፤ በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። 17፤ ለያዕቆብ ሥርዓት እንዲሆን ለእስራኤልም የዘላለም ኪዳን እንዲሆን አጸና፤ 18፤ እንዲህም አለ፡— ለአንተ የከነዓንን ምድር የርስታችሁን ገመድ እሰጣለሁ፤ 19፤ ይህም የሆነው እነርሱ በቍጥር ጥቂቶች ሰዎች፥ እጅግ ጥቂቶችና ስደተኞች ሲሆኑ ነው። 20፤ ከሕዝብ ወደ ሕዝብ፥ ከመንግሥትም ወደ ሌላ ሕዝብ አለፉ።
📌አሁንም እግዚአብሔር መመንጠር ያለበትን መንጥሮ፣መቆረጥ ያለበትን ቆርጦ፣መገደል ያለበትን ገድሎ፣በደሙ ዋጃትን የተቀደሰ ህዝቡን ከውድቀት ከዘንዶ መንጋጋ ያወጣል።🙏
👉ኢሳይያስ 51:9፤ የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፥ ተነሥ፥ ተነሥ፥ ኃይልንም ልበስ፤ በቀድሞው ወራትና በጥንቱ ዘመን በነበረው ትውልድ እንደ ሆነው ተነሥ። ረዓብን የቈራረጥህ ዘንዶውንም የወጋህ አንተ አይደለህምን? 10፤ ባሕሩንና የታላቁን ጥልቅ ውኃ ያደረቅኸው፥ የዳኑትም ይሻገሩ ዘንድ ጠሊቁን ባሕር መንገድ ያደረግህ አንተ አይደለህምን?
እግዚአብሔር ስሙ ለዘላለም ይባረክ!