21/08/2026
#በኢየሱስ ንግግር ወደ አብ መሄድ" ማለት ብዙ ኪሎ ሜትር ተጉዞ ወደ ሌላ ፕላኔት መሄድ ማለት ነውን❓
ምክንያቱም ጌታችን ኢየሱስ አብ በእኔ ይኖራል ብሏልና ደግሞም እግዚአብሔር መንፈስ ነው መንፈስ ደግሞ በሁሉ ስፍራ ይኖራል ስለሆነም ወደ አብ መሄድ" ማለት ኪሎ ሜትር ተጉዞ ወደ ሌላ ፕላኔት መሄድ ማለት አይደለም ይልቁንም ያ የተናቀው፣ የተገረፈውና የሞተው "ሰውነቱ" (ሥጋው) ወደ መለኮታዊ ክብሩ መመለሱን የሚያሳይ ነው።
✍️ዮሐንስ 17፥5 ላይ "ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አሁን አንተ በእራስህ ዘንድ አክብረኝ" እንዳለ፣ ወደ አብ መሄድ የሥጋ መክበር (Glorification) ነው። ቃል በአብ ዘንድ ክብር ነበረው ያን ክብር ቀርቶ ሥጋ ስሆን እንደ ሰው ሆነና በአብ መልክ ይኖር የነበረው ቃል የባሪያን መልክ በመያዙ ምክንያት ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አሁን አንተ በእራስህ ዘንድ አክብረኝ አለ ማለት ነው። እንዲህ ሲባል መልሰህ ቃል አድርገኝ ሳይሆን ሰው የሆነው ኢየሱስ ወደ አብ በመሄድ በአብ ክብር ወይንም በአባትነት መኖሩን ነው የሚያጎላ።
✍️በተጨማሪም
ወደ አብ መሄድ" ማለት "ማንነቱን ማሳየት" ነው
ኢየሱስ ወደ አብ መሄዱን ሲናገር ከቦታ ቦታ መዘዋወር ሳይሆን፣ በምድር ላይ በውርደትና በድካም (በመራብ፣ በመጠማት፣ በመሰቀል) ውስጥ የነበረው ማንነቱ አልፎ፣ ቀደም ስል ደምጹ እንደ ብዙ ውሆች ወደ ሚያስፈራው ወደ መለኮታዊ ስልጣን ሙሉነት መሄዱን የሚገልጸው ስለዚህ "ወደ አብ መሄድ" ማለት ወደ ሙሉ ክብሩ መመለስ ማለት ነው።
✍️በተመሳሳይ
"የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ"
ኢየሱስ ራሱን "የሰው ልጅ" (Son of Man) ብሎ መጥራቱ የሁላችንንም የሰውነት ባሕርይ ወክሎ ነው። ስለዚህ፡
እርሱ ሲከብር፣ ሰውነት (ሰብአዊነት) አብሮ ከበረ ማለት ነው።
ቀደም ሲል ሞትና ውርደት የሰው ልጅ መጨረሻ ይመስል ነበር፤ እርሱ ግን ያንን "ሰውነት" ይዞ እስከ መለኮት ክብር (እስከ አብ) ድረስ ከፍ በማድረጉ፣ ለሰው ልጅ አዲስ የክብር በር ከፈተ።
ሁለቱ ለምን ተያያዙ?
"ወደ አብ መሄድ" እና "መክበር" አንድ ናቸው። ምክንያቱም፦
አብ ማለት የክብር ሁሉ ምንጭ ነው።
መሄድ ማለት ደግሞ ያንን ክብር መጎናጸፍ ነው።
ኢየሱስ "የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደረሰ" ሲል፣ እግዚአብሔር በለበሰው ሥጋ (በሰውነቱ) አማካኝነት ሞትን ድል አድርጎ፣ ያንን የሰውነቱን ማንነት ወደ መለኮታዊ ክብሩ ከፍ ሊያደርገው መሆኑን መናገሩ ነው።
ባጭሩ፦
ኢየሱስ ወደ አብ ሄደ ማለት በለበሰው ሥጋ (በሰውነቱ) ውስጥ ሆኖ ይሠራው የነበረውን የተዋረድ ሥራ ጨርሶ፣ አብ ባለው ክብር ያ ሥጋ እንዲከብር አደረገ ማለት ነው። ስለዚህ የኢየሱስ መክበር የሰው ልጅ ተስፋና ትልቅ ክብር ማሳያ ሆነ።
Follow👇
ቃሉ ይናገር- 𝐋𝐞𝐭 𝐓𝐡𝐞 𝐖𝐨𝐫𝐝 𝐒𝐩𝐞𝐚𝐤
Apostolic Generation