ፍልውሃ / ተውፊቅ መስጂድ

ፍልውሃ / ተውፊቅ መስጂድ ስለ ፍልውሀ መስጂድ አመሰራረት እንዲሁም አሁን ያለበትን ሁኔታ ያገኙበታል እንዲሁም ሀዲስ ቁርአን እና ኢስላማዊ ነገሮችን ያገኙበታል

15/09/2025

በአዲስ አበባ ፍልውሃ ተውፊቅ መሰጂድ መሰራችና አኢማም ሸህ ሀቢብ ሙሀመድ የቀብር ስነስርአት ዛሬ መስከረም 5 ቱሉዲምቱ ሙስሊም መቃብር (ዩኒሳ) ከዝሁር በኋላ የሚከናወን በመሆኑ ሁላችንም በቀብራቸው ላይ በመገኘት ልንሸኛቸው ይገባል

አባታችንን እና መካሪያችንን ሼይኽ ሐቢብ አላህ ይዘንላቸው
ማረፊያቸውንም በጀነተል ፊርዶስ ያድርግላቸው
ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብም አላህ መፅናናቱን ይወፍቅ

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑንበአዲስ አበባ የፍልውሃ/ተውፊቅ መስጂድ ኢማም እና መስራች የነበሩት ታላቁ አሊም ሼይኽ ሐቢብ መሐመድ ወደ አኼራ ሄደዋል::ሼይኽ ሐቢብ ሃቅን በመናገር እና በማ...
14/09/2025

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን

በአዲስ አበባ የፍልውሃ/ተውፊቅ መስጂድ ኢማም እና መስራች የነበሩት ታላቁ አሊም ሼይኽ ሐቢብ መሐመድ ወደ አኼራ ሄደዋል::

ሼይኽ ሐቢብ ሃቅን በመናገር እና በማስተማር ማንንም የማይፈሩ የሃገራችን የእውቀት ዋርካ ነበሩ::

ሙስሊሙ ማህበረሰብ በሃገሩ ትልቅ ቦታ እንዲኖረው የሚመኙ እና ለዛ አላማም ሁሌም ጠንክሮ እንዲሰራ ይለፉ የነበሩ አባት ነበሩ::

የሼይኽ ሐቢብ መሀመድ ማለፍ ለሃገራችን ሙስሊም ትልቅ ኪሳራ ነው:: የግለሰብ ሞት ሳይሆን የኡማ ሞት ነው::

የሳቸው አይነት የእውቀት ባለቤት፣ ቆራጥ እና የሃቅ ጠበቃ በሞት መነጠቅ መተኪያ የማይገኝለት ትልቅ ኪሳራ ነው::

በውስጣችን በመኖራቸው በሃገራችን የሚከሰቱ በላዎችን እና ፈተናዎችን አላህ እንዲያነሳልን አላህን እንዲማፀኑልን እና ምክር እንዲለግሱን የምንሻቸው የእውነት አባታችን ነበሩ::

በዚህ ከባድ ወቅት ሼይኽ ሐቢብን የመሰሉ የሃገር ዋርካ የሆኑ አሊምን በሞት ማጣት ድርብርብ ሙሲባ ነው::

ሁላችንም ወደ አላህ ልንመለስ፣ ፈተናውንም በቃችሁ እንዲለን አልቀሰን ዱዓ ልናደርግ ይገባል::

የሼይኽ ሐቢብ ስርኣት ቀብርም ነገ ሰኞ የሚፈፀም በመሆኑ ሁላችንም በቀብራቸው ላይ በመገኘት ልንሸኛቸው ይገባል::

አባታችንን እና መካሪያችንን ሼይኽ ሐቢብ አላህ ይዘንላቸው
ማረፊያቸውንም በጀነተል ፊርዶስ ያድርግላቸው
ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብም አላህ መፅናናቱን ይወፍቅ

የጌታህ ምንዳ የተሻለ ነው!ለሰዎች መልካም ትሰራለህ ነገር ግን አፀፋው (ምላሹ) ክፋት ነው ይሉሃል። መልካም የሰራኸው የአላህን ፊትና የርሱን ውዴታ ከጅለህ ከሆነ የምታገኘው ክፋትን ሳይሆን ...
21/12/2022

የጌታህ ምንዳ የተሻለ ነው!

ለሰዎች መልካም ትሰራለህ ነገር ግን አፀፋው (ምላሹ) ክፋት ነው ይሉሃል። መልካም የሰራኸው የአላህን ፊትና የርሱን ውዴታ ከጅለህ ከሆነ የምታገኘው ክፋትን ሳይሆን የአላህን ፍቅርና መልካም ምንዳ ነው።
ምን አልባት ሰዎች የሰራህላቸውን መልካም ስራና የዋልክላቸውን ውለታ ይረሱ ይሆናል ፤ አላህ ግን ፈፅሞ አይረሳም በምትሰራው መልካም ስራ ሁሉ ይመነዳሃል።

ለጋስ የሆነው ጌታህ እንዲህ ይልሃል:—

《ታገስም ፤ አላህ የመልካም ሰሪዎችን ምንዳ አያጠፋምና》አል—ሁድ /115

ስለዚህ መልካም ስራን ስትሰራ ምንዳህን ከአላህ ከጅል።

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በ2014 10,704 ሰዎች ሐጅ ለማድረግ ተመዝግበው የነበረ ቢሆንም ፤ የስልጣን ጥመኛ ውሃቢያ ከ ብልፅግና ጋር ተመሳጥሮ የእስልምና አርካን የ...
01/10/2022

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በ2014 10,704 ሰዎች ሐጅ ለማድረግ ተመዝግበው የነበረ ቢሆንም ፤ የስልጣን ጥመኛ ውሃቢያ ከ ብልፅግና ጋር ተመሳጥሮ የእስልምና አርካን የሆነው ሀጅ እንዳይደረግ እንቅፋት በመሆን 4000 ሁጃጆች ወደ ሳዑዲ አረቢያ መሄዳቸው ይታወሳል

የብልፅግናው መጅሊስ ይህን ባልን 48 ሰአት ውስጥ በባንክ ተቀምጦ የነበረን የሁጃጆችን ብር ማለትም 1,584,334,000(አንድ ቢሊየን አምስት መቶሰማኒያ አራት ሚሊየን ሶስት መቶ ሰላሳ አራት ሺህ በር ) ለመመለስ ለወራት ከተሰቃየ በኋላ 1,430,383,395 (አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሰማንያ ሶስት ሺህ ሶስት መቶ ዘጠና አምስት ሺህ ብር ) መመለሱን አስታውቋል

አሁንም ቀሪውን 153,950,605 (መቶ ሀምሳ ሶስት ሚሊየን ዘጠኝ መቶ ሀምሳ ሺህ ስድስት መቶ አምስት ብር ) በሬ እና መሬታቸውን ሸጠው ና ለ አመታት አጠራቅመው በይቱላህን ለመዘየር ብለው ያወጡትን ገንዘብ በአስቸኳይ አላህን ፈርታቹ መልሱላቸው

ሼር ይደረግ

ለሁሉም ኢስላማዊ ሚዲያዎች (ውሃቢያን አይወክልም)

ቢስሚላህ
በዚህ ዓመት 10,704 ሰዎች ሐጅ ለማድረግ ተመዝግበው የነበረ ቢሆንም ፤ በዶላር እጥረት ምክንያት 4000 ሁጃጆች ወደ ሳዑዲ አረቢያ መሄዳቸው ይታወሳል

በዶላር እጥረት አልነው እንጂ ችግሩ የነበረው የስልጣን ጥመኛ ውሃቢያ ከ ብልፅግና ጋር ተመሳጥሮ የእስልምና አርካን የሆነው ሀጅ እንዳይደረግ እንቅፋት የሆነበት ነበር

የሆነው ሆኖ ከዚህ በታች በፎቶው ላይ ስም ዝርዝራችሁ የተገለፃችሁ 130 ግለሰቦች እና ለሐጅ ከፍላችሁ ያልሄዳችሁ ገንዘባችሁ በከፈላችሁበት ባንክ በኩል በቀድሞው መጅሊስ ተመላሽ ተደርጓል ፤ የሌሎቹንም 6574 ማለትም 1,584,334,000 ብር ለመመለስ በዚሁ መልኩ ስማቸውን ለየባንኮቹ በማስተላለፍ ላይ ሳሉ ነው እንግዲህ መፈንቅለ መጅሊሱ የተካሄደው

አሁንም ቢሆን የ እነዚህ 6547 ሁጃጆች ብር ከዚህ ቀደም የሱማሌ ሁጃጆችን ብር የዘረፈው ከማል ሀሩን እና ኢብራሂም ቱፋ እጅ ነው የወደቀውና የመመለስ እድሉ ጠባብ ነው

ኢስላማዊ ሚዲያዎች ሀገር ውስጥ ያሉት በሬ እና መሬታቸውን ሸጠው በ ውጭ ሀገር የሚኖሩ ወንድምና እህቶች ለአመታት አጠራቅመው ቤተሰቦቻቸውን በይቱላህን ለማዘየር ብለው ያወጡት ገንዘብ ነው ና ሁጃጆቹን ባሉበት በመሄድ ቃለመጠየቅ በማድረግ እና ድምፃቸው ይሰማ ዘንድ ትብብር ታደርጉላቸው ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን
ሐሪማ ቲቪ - Harima Tv
አስ-ሱና ቲቪ / As-Sunnah TV
ሚዛን ትዩብ "የሙስሊሙ እዉነተኛ ድምፅ"

እንሽቀዳደምvia ወንድም ሀሰን ኢንጃሞ-> ወንድም ሙሐመድ ሎባ (ቻይና) ለዑለሞቻችን ክብር ከፊት እየታገሉ ካሉ ወንድሞች የመጀመሪያው ነው:: -> የሚሊንየም መውሊድ ዝግጅት ለማደናቀፍ ድጋሚ...
29/09/2022

እንሽቀዳደም

via ወንድም ሀሰን ኢንጃሞ

-> ወንድም ሙሐመድ ሎባ (ቻይና) ለዑለሞቻችን ክብር ከፊት እየታገሉ ካሉ ወንድሞች የመጀመሪያው ነው::
-> የሚሊንየም መውሊድ ዝግጅት ለማደናቀፍ ድጋሚ 15 ቀናት ያለ ምንም ክስ ታስሮ ተፈቷል::
-> ብዙዎች ወንድሞች በታክሲ ነው የሚንቀሳቀሱት:: በኪራይ ቤት ነው የሚኖሩት::
-> ሁሉም እስኪባል ድረስ በነጻ እንደውም ከፍለው ነው የሚያገለግሉት::
-> ወንድም ቻይና እራሱ ይህንን ሁሉ ሥራ በታክሲ እየተንቀሳቀሰ ነው የሚከውነው:: ሥራውን በቅልጥፍና ይሠራ ዘንድ መጓጓዣ መኪና ብንኻድመው የሚል ሐሳብ ተነስቶ ብዙ ምእመን ዝግጁ መሆኑን ገልጿል::

-> እነሆ አካውንት ተከፍቷል::
-> እኔ ዓብዱልቃዲር ሒሳቡን በግልጽ አስቤና ተሳስቤ ለምእመናን አሳውቃለሁ::
-> በሚከተለው አካውንት ማስገባት ትችላላችሁ:: ልክ ፕሮጀክቱ ሲሟላ ሒሳቡ ይዘጋል:: ሀያ ተሽቀዳደሙ::

Commercial Bank of Ethiopia
Mukerem Ahmedin and Feysel M***a
1000500829196

ያለምንም ወንጀሉ ለአስራ አምስት ቀናቶች በግፍ ታስሮ የነበረው አሚራችን መሀመድ ሎባ በአላህ ፍቃድ በ10 ሺ ብር ዋስ ተፈቷዋል  አልሃምዱሊላህ የሀሰት ክሶች መደራረብ ትክክለኛው መንገድ ላይ...
28/09/2022

ያለምንም ወንጀሉ ለአስራ አምስት ቀናቶች በግፍ ታስሮ የነበረው አሚራችን መሀመድ ሎባ በአላህ ፍቃድ በ10 ሺ ብር ዋስ ተፈቷዋል

አልሃምዱሊላህ

የሀሰት ክሶች መደራረብ ትክክለኛው መንገድ ላይ ለመሆናችን ማሳያ ነው

በሀሰት ከሶ ማሳሰር ይበልጥ ቢያጠነክረን እንጂ ከትግላችን ፈፅሞ ፈቀቅ አያደርገንም ኢንሻአላህ

27/09/2022

"አንዳንዱ መዶሻ እጁ ሲገባ ሁሉ ነገር ሚስማር ይመስለዋል"
ሰይዲ ኡስታዝ ሸምሰዲን

ሼር ይደረግለሁሉም ኢስላማዊ ሚዲያዎች (ውሃቢያን አይወክልም)ቢስሚላህ በዚህ ዓመት 10,704 ሰዎች ሐጅ ለማድረግ ተመዝግበው የነበረ ቢሆንም ፤ በዶላር እጥረት ምክንያት 4000 ሁጃጆች ወደ ...
27/09/2022

ሼር ይደረግ

ለሁሉም ኢስላማዊ ሚዲያዎች (ውሃቢያን አይወክልም)

ቢስሚላህ
በዚህ ዓመት 10,704 ሰዎች ሐጅ ለማድረግ ተመዝግበው የነበረ ቢሆንም ፤ በዶላር እጥረት ምክንያት 4000 ሁጃጆች ወደ ሳዑዲ አረቢያ መሄዳቸው ይታወሳል

በዶላር እጥረት አልነው እንጂ ችግሩ የነበረው የስልጣን ጥመኛ ውሃቢያ ከ ብልፅግና ጋር ተመሳጥሮ የእስልምና አርካን የሆነው ሀጅ እንዳይደረግ እንቅፋት የሆነበት ነበር

የሆነው ሆኖ ከዚህ በታች በፎቶው ላይ ስም ዝርዝራችሁ የተገለፃችሁ 130 ግለሰቦች እና ለሐጅ ከፍላችሁ ያልሄዳችሁ ገንዘባችሁ በከፈላችሁበት ባንክ በኩል በቀድሞው መጅሊስ ተመላሽ ተደርጓል ፤ የሌሎቹንም 6574 ማለትም 1,584,334,000 ብር ለመመለስ በዚሁ መልኩ ስማቸውን ለየባንኮቹ በማስተላለፍ ላይ ሳሉ ነው እንግዲህ መፈንቅለ መጅሊሱ የተካሄደው

አሁንም ቢሆን የ እነዚህ 6547 ሁጃጆች ብር ከዚህ ቀደም የሱማሌ ሁጃጆችን ብር የዘረፈው ከማል ሀሩን እና ኢብራሂም ቱፋ እጅ ነው የወደቀውና የመመለስ እድሉ ጠባብ ነው

ኢስላማዊ ሚዲያዎች ሀገር ውስጥ ያሉት በሬ እና መሬታቸውን ሸጠው በ ውጭ ሀገር የሚኖሩ ወንድምና እህቶች ለአመታት አጠራቅመው ቤተሰቦቻቸውን በይቱላህን ለማዘየር ብለው ያወጡት ገንዘብ ነው ና ሁጃጆቹን ባሉበት በመሄድ ቃለመጠየቅ በማድረግ እና ድምፃቸው ይሰማ ዘንድ ትብብር ታደርጉላቸው ዘንድ በአላህ ስም እንጠይቃለን
ሐሪማ ቲቪ - Harima Tv
አስ-ሱና ቲቪ / As-Sunnah TV
ሚዛን ትዩብ "የሙስሊሙ እዉነተኛ ድምፅ"

ወላሂ ከውሃቢያ ጋር አንድ አይደለንም!ለአንድነት ከኛ በላይ የለፋ የለም!ፍላጎታችን የማስመሰል አንድነት አልነበረም መሪያችን ሙፍቲ እንዳሉት ልባዊ አንድነት እንዲመጣ ብዙ ለፍተናልእንዴት አን...
27/09/2022

ወላሂ ከውሃቢያ ጋር አንድ አይደለንም!

ለአንድነት ከኛ በላይ የለፋ የለም!

ፍላጎታችን የማስመሰል አንድነት አልነበረም መሪያችን ሙፍቲ እንዳሉት ልባዊ አንድነት እንዲመጣ ብዙ ለፍተናል

እንዴት አንድ ሙስሊም ሌላኛውን ሙስሊም ለማሳሰር እና ለማሳጣት ገንዘብና ጉልበቱን እንዲሁም ግዜውን ሰውቶ ሴራ ይጎነጉናል

ረጅም ትግል ይጠብቀናል ተዘጋጁ !!!

አሳዛኝ ዜናዛሬ በአሸዋ ሜዳ ዘሀራ መስጂድ አርባ የተማሪ ወላጆች በወሀብያ አዣዥነት ታስረዋል ባለፈው የተወሰኑ ቀናቶች መስጅድ ውስጥ የነበሩ የዳእዋ ጀመአዎች ላይ ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል! አሽ...
27/09/2022

አሳዛኝ ዜና

ዛሬ በአሸዋ ሜዳ ዘሀራ መስጂድ አርባ የተማሪ ወላጆች በወሀብያ አዣዥነት ታስረዋል ባለፈው የተወሰኑ ቀናቶች መስጅድ ውስጥ የነበሩ የዳእዋ ጀመአዎች ላይ ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል!

አሽዋ ሜዳ ሂልቶብስ አከባቢ የሚገኘው ዘሀራ መስጅድ በተብሊግ ጀመአዎች እንቅስቃሴ የተመሰረተ እና በነሱ አማካኝነት ከ 300 በላይ ተማሪዎች አፍተር ስኩል ደርስ የሚማሩበት ሲሆን ወሀብዮች ዛሬ ህዝቡን ሰብስበው መድረሳው እኛ እንወስዳለን ከአሁን በኋላ የሚቀሩትም የእኛን ቂርአት ብቻ ነው በሚሉበት ወቅት የአካባቢው ማህበረሰብ ይህማ አይሆንም ከዚህ በፊት በሲ ኤም ሲ መድረሳ ተርቲብ ለረጅም ዘመናት የሚያስቀሩ ዑስታዞች አሉን ቢሉም ውሀብዮች ወደ ጣቢያ በመደወል የኦሮሚያ ፖሊሶችን በመጥራት የተሰበሰቡትን የተማሪ ወላጆችን ጨምሮ ከአርባ በላይ የተማሪ ወንዶችን እና ብዛት ያላቸውን ሴቶች ከፍተኛ ድብደባ በመፈፀም የነበሩትን የተማሪዎችና ወላጆች በጠቅላላ ወደ ጣቢያ ፍፁም ህግን ባልተከተለ መንገድ አስረዋቸዋል::

ሴቶችን አሁን ከመሸ የለቀቋቸው ሲሆን አርባ ወንዶች አሁንም እስር ቤት መሆናቸው የታወቀ ሲሆን ይህንን መስጅድ የውሃቢያ ጀመዐ ለመቀማት የተለያዩ ጥረቶችን ሲያረግ እንነበርና እኛ ሳንፈቅድ አትማሩም በማለት ካለፉት ሁለት ቀናት ጀምሮ ተማሪዎች መማር ሳይችሉ ቀርተዋል::

እንዲሁም ለ አላህ ብለው ቤተሰቦቻቸውን ትተው ዳእዋ በወጡ ሰዎች ላይ ትላንት ማታ ድብደባ እደተፈፀመባቸው ታውቋል::

የተበዳይ ዱአ አይመለስምና ሁላችንም ወደ አላህ እጃችንን እንዘርጋ 🤲🤲🤲

በደጋግ ባሮችህ ይሁንብህ በቃቹ በለን 🤲🤲🤲

ፍትህ አሸዋ ሜዳ ያለ ምንም ወንጀላቸው ለታሰሩ የተማሪ ወላጆች !

የህግ ምሩቅ እንዲሁም ብዙዎችን ያቀሩ ታላቅ አሊም ሸይኽ ቃሲም መሀመድ ታጁዲን ያለ ወንጀላቸው ሜክሲኮ ያለው ፌደራል ፖሊስ እስር ቤት ይገኛሉአርብ መስከረም 13/2015 ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ...
26/09/2022

የህግ ምሩቅ እንዲሁም ብዙዎችን ያቀሩ ታላቅ አሊም ሸይኽ ቃሲም መሀመድ ታጁዲን ያለ ወንጀላቸው ሜክሲኮ ያለው ፌደራል ፖሊስ እስር ቤት ይገኛሉ

አርብ መስከረም 13/2015 ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በ10ሺ ብር ዋስ እንዲፈቱ ወስኖ የዋስትናው ብር ከተከፈለ በኋላ ፖሊስ ይግባኝ ስለተጠየቀባቸው ሰኞ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፣ መፈቻውን አልፈርምም ብሎ የነበረ ቢሆንም ሸህ ቃሲም ዛሬ ፍርድ ቤት አልቀረቡም እንደሚቀርቡም አልተነገራቸውም

ያለ ፍርድ ቤት ቀጠሮ በግፍ እስር ላይ ናቸው

Address

Taitu Street
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ፍልውሃ / ተውፊቅ መስጂድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Place Of Worship

Send a message to ፍልውሃ / ተውፊቅ መስጂድ:

Share

Category