Catholic Bishops’ Conference of Ethiopia

Catholic Bishops’ Conference of Ethiopia The Ethiopian Catholic Church (ECC), is the presence of the Universal Catholic Church in Ethiopia

በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ የአዲግራት ሀገረስብከት ቆይታበቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካ...
09/06/2026

በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ የአዲግራት ሀገረስብከት ቆይታ

በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ በአዲግራት ሀገረስብከት ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ። ብፁዕነታቸው በመቀሌ በአሉላ አባ ነጋ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ የአዲግራት ሀገረስብከት ጳጳስ፣ በካህናት፣ በገዳማውያን እና በምዕመናን አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ብፁዕነታቸው ጉዟቸውን ወደ አዲግራት በመቀጠል በመንገዳቸው ጥንታዊ እና ታሪካዊውን የአል ነጃሺ መስጊድ የጎበኙ ሲሆን አዲግራት ሲደርሱ በመድሃኔአለም ካቶሊክ ካቴድራል ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በመድሃኔአለም አመታዊ ክብረበዓል ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ከብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ ጋር መስዋዕተ ቅዳሴ የሳረጉ ሲሆን በዕለቱም ከሰበካው ካህናት፣ ገዳማውያን፣ ምዕመናን ወጣቶች እና ህጻናት ጋር መገናኘት ችለዋል።
በዕለቱም የአዲግራት ሀገረስብከት በጦርነቱ ምክንያት ላለፉት በርካታ አመታት በከባድ ፈተና እና ተስፋ መቁረጥ ያሳለፈ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በእምነት እና በጥንካሬ ወደቀድሞ ለመመለስ ጥረት በሚያደርግበት ወቅት መሆኑ ብዙዎችን የሚያጽናና እና የሚያበረታ መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ በበኩላቸው በምዕመናን ላይ ያዩትን መንፈሳዊ ጥንካሬ በማድነቅ ሀገረስብከቱ ያሳለፈውን ፈተና እንደሚረዱ እና እንደሚያውቁ ገልጸዋል። አክለውም “ሕንጻና ሌሎች ቁሳዊ ነገሮች ሊፈራርሱ ይችላሉ፣ በብዙ መንገድ ልትጎዱ ትችላላችሁ፤ ነገር ግን እምነታችሁን ማንም ሊነጥቃችሁ አይችልም። አሁንም አይዟችሁ፤ ቤተክርስቲያን እንደ ሁልጊዜው ትጸልይላችኋለች፣ ሰላምና ፍትህ እንዲሰፍንም የሚቻላትን ሁሉ ታደርጋለች" በማለት የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ መልዕክት እና ቡራኬ አስተላልፈዋል።
ብፁዕ ካርዲናል በአዲግራት ቆይታቸው ታሪካዊውን የቅዱስ ኣቡነ ያዕቆብ ገዳም፣ ሳሊዝያን ዶንቦስኮ ዓዲግራት ፥ ከውቅር ኣብያተ ክርስቲያን ኣንዱ የሆነው የውቅሮ ጨርቆስ ቤተክርስትያን ፥ የውቅሮ ቅድስት ማርያም ኮሌጅ እንዲሁም በመቀሌ የፍቅር ልጆች ደናግል፣ሳሊዝያን ዶንቦስኮ መቀሌ ጉብኝት አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ የሲታውያን ገዳም አባል በሆኑት በክቡር አባ ኤልያስ ከዚህ አለም ድካም ማረፍ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል።ጌታ ሆይ ለሞቱት ሰዎችየዘላለም...
09/06/2026

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ የሲታውያን ገዳም አባል በሆኑት በክቡር አባ ኤልያስ ከዚህ አለም ድካም ማረፍ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል።

ጌታ ሆይ ለሞቱት ሰዎች
የዘላለም እረፍት ስጣቸው
የዘላለም ብርሃን አብራላቸው
በሰላም አሳርፋቸው!

በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጋር ተገናኙ በዛሬው ዕለት ለሐዋርያዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ብፁዕ ...
02/06/2026

በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጋር ተገናኙ

በዛሬው ዕለት ለሐዋርያዊ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የገቡት ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጋር ተገናኝተዋል።

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ለቅዱስ ፓትሪያርኩ የርዕሰ ሊቃነጳጳሳት ሌዎ 14ኛ መልዕክት ያቀረቡ ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በመምጣታቸውም ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ እንግዶቹን በቢሯቸው በመቀበል በኢትዮጵያ ለሚኖራቸውም ቆይታ መልካም ምኞታቸውን በመግለጽ አባታዊ ቡራኬያቸውን ሰጥተዋል።

ብፁዓን ጳጳሳቱ በወቅታዊ የአለማችን ሰላም እና የክርስቲያኖች ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል። በተለይም በኢትዮጵያ እና በመላው አለም ክርስቲያኖች ላይ ለሚደርስ በደል በጸሎት ህብረት እና በጋራ የመስራት አስፈላጊነት ላይ ተወያይተዋል።

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉብኝታቸውን በመቀጠል በአዲስ አበባ ሀገረስብከት የእማሆይ ተሬዛ ገዳም ቆይታ አድርገዋል። ስድስት ኪሎ አካባቢ በሚገኘው ገዳም ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ከገዳማውያት ጋር ታካሚዎችን እና በተቋሙ የሚሰሩ ስራዎችን ጎብኝተዋል።

በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ ወደ ኢትዮጵያ ገቡ። ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያ...
02/06/2026

በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ኃላፊ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ ወደ ኢትዮጵያ ገቡ።

ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በቅድስት መንበር የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል (ዳይካስትሪ) ኃላፊ የሆኑት ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ ጉጀሮቲ፣ ክቡር አባ ድሚትሮ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ክፍል ዋና ጸሃፊ፣ ክቡር አባ ጃሮዝላቭ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት ተወካይ ወደ ኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ ገብተዋል።

ብፁዕነታቸው ወደኢትዮጵያ ሲገቡ በአዲስ አበባ አለም አቀፍ ኤርፖርት እና በቫቲካን ኤምባሲ በብፁዓን ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ገዳማውያን እና የምዕመናን ተወካዮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በመቀጠልም በልደተ ማርያም ካቶሊክ ካቴድራል በብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነኢየሱስ ሊቀጳጳሳት ዘካቶሊካውያን እና በአዲስ አበባ ሀገረስብከት ካህናት አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን የጉብኝታቸውን ማስጀመሪያ የጸሎት መርሃግብር ተካሂዷል።

ጉብኝታቸውን በአዲስ አበባ ሀገረስብከት የሴቶች እድገት የሙያ ማሰልጠኛ እና በቅዱስ ዮሃንስ ጳውሎስ ዳግማዊ የሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅ የጀመሩ ሲሆን ተማሪዎችንም በስልጠና ላይ ሰላምታቸውን አቅርበዋል።

ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ በኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በተቋሙ በመገኘትም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ሰራተኞችን አግኝተዋል። ብፁዕነታቸው በጠቅላይ ጽ/ቤቱ ያለውን የሥራ ሂደት እና ዘርፈ ብዙ የአገልግሎት ዘርፎች ገለጻ ተደርጎላቸው አጠር ያለ ጉብኝት አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ  የእመቤታችን ፍራንሲስካውያን ልዑካን ገዳም አባል የሆኑት ሲስተር በርናዴት ወልደማርያም ከዚህ አለም ድካም ማረፍ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገ...
01/06/2026

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ የእመቤታችን ፍራንሲስካውያን ልዑካን ገዳም አባል የሆኑት ሲስተር በርናዴት ወልደማርያም ከዚህ አለም ድካም ማረፍ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል።

ጌታ ሆይ ለሞቱት ሰዎች
የዘላለም እረፍት ስጣቸው
የዘላለም ብርሃን አብራላቸው
በሰላም አሳርፋቸው።

25/05/2026
የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ የመጀመሪያው ሐዋርያዊ መልዕክት ይፋ ሆነ።  “ማኚፊካ ሂውማኒታስ” የተሰኘው የመጀመሪያው ሐዋርያዊ መልዕክታቸው ሰብዓዊነት እና ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ሲሆን በ...
25/05/2026

የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ የመጀመሪያው ሐዋርያዊ መልዕክት ይፋ ሆነ።

“ማኚፊካ ሂውማኒታስ” የተሰኘው የመጀመሪያው ሐዋርያዊ መልዕክታቸው ሰብዓዊነት እና ቴክኖሎጂ ላይ ያተኮረ ሲሆን በዘመናችን እጅግ እየተስፋፋ የመጣውን የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በሰው ልጅ ላይ ያለውን ተፅዕኖ በጽሁፋቸው አመላክተዋል።

ቅዱስነታቸው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ ዘመን በዚሁ ከቀጠለ ሰብዓዊነትን በመጻረር የሰውን ልጅ ክብርን አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ የሁሉም ሰው አስቸኳይ ኃላፊነት መውሰድ ያስፈልጋል ብለዋል።
ቴክኖክራሲያዊ ርዕዮተ ዓለም የሰውን ልጅ ገደብና እና ደካማነት እንደተፈጥሮአዊነቱ ሳይሆን እንደሚስተካከል ስህተት በመቁጥር የሰውን ልጅ ድንቅ አፈጣጠር ሲያሳንስ ይስተዋላል ያሉት ቅዱስነታቸው አለማችንን በኃያላን አይን ሳይሆን ከታች ጀምሮ በሚሰቃዩት እና በተገለሉት ወንድምና እህቶቻችን አይን ልናይ ይገባል ብለዋል።
“ማኚፊካ ሂውማኒታስ” የሰው ሰራሽ አስተውሎት የትንታኔ ጽሁፍ ሳይሆን የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንን የማህበራዊ አስተምህሮ መርሆዎች በAI ዘመናችን ላይ የሚተገብር፣ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትን ዋና ዋና ነጥቦች የሚያጠናክር እና የሚያዘምን “ማጠቃለያ” ነው። ይህ ጽሑፍ በኢኮኖሚ ሥርዓት እና በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ፍጹም ነፃነት ላይ በመታመን፣ የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት የሰው ልጅ የጋራ አስተዳደር አስፈላጊነት፣ የተቀናጀ ሥነ-ምህዳር፣ “የኃጢአት መዋቅሮች” የሆኑ የኢኮኖሚ መዋቅሮች እና ጦርነትን አለመቀበልን በተመለከተ የሰጡትን ትምህርት ውድቅ የሚያደርጉ ሰዎችን የተሳሳተ ግንዛቤ የሚያቆም ጽሑፍ ነው።
ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሌዎ 14ኛ “ጦርነትን በሥነ ምግባር ተቀባይነት እንዲኖረው የሚያደርግ ምንም ስልተ ቀመር የለም” በማለት የ“ፍትሃዊ ጦርነት” ንድፈ ሐሳብ አላስፈላጊ መሆኑን በድጋሚ በማረጋገጥ፣ በጦርነት ውስጥ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ጥብቅ የሆኑ የሥነ ምግባር ገደቦችን እንዲጣልበት ጥሪ አቅርበዋል።
ቅዱስነታቸው ሰብዓዊ ክብርን ለማስጠበቅ የብዙዎችን ሕይወት ዋጋ የሚያስከፍሉ እና የጥቂቶችን ኃይል የሚጨምሩ ሞኖፖሊዎችን ማስወገድ አስፈላጊ ሲሆን ይህም ሥነ ምግባራዊ አስተዳደርን፣ ማህበራዊ ፍትህን እና የጋራ ጥቅምን ያጎላል ብለዋል።

ቅዱስነታቸው በመልዕክታቸው ከ135 ዓመታት በፊት በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ 13ኛ "Rerum Novarum" የተሰኘው በኢንዱስትሪ አብዮት ወቅት የወጣቶችን እና የሰራተኞችን መብት ለመጠበቅ ካወጡት መልዕክት ጋር በመያያዝ ባሁኑ ወቅት ምዕመናን በዲጂታል አብዮት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የመልዕክቱ ሙሉ ቃል በእንግሊዘኛው ትርጉም በቅድስት መንበር ድረገፅ https://www.vatican.va/content/leo-xiv/en/encyclicals/documents/20260515-magnifica-humanitas.html ይገኛል።

25/05/2026
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ብፁዓን ጳጳሳት የስደተኞችን ሰብዓዊ ክብርና ሕይወት እንዲጠበቅ ጥሪ አቀረቡየኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት በተለያዩ የዓለማችን አካባቢዎች የሚገኙ የኢትዮጵያውያን ...
22/05/2026

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ብፁዓን ጳጳሳት የስደተኞችን ሰብዓዊ ክብርና ሕይወት እንዲጠበቅ ጥሪ አቀረቡ
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት በተለያዩ የዓለማችን አካባቢዎች የሚገኙ የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ሰብዓዊ ክብርና ሕይወት ይጠበቅ ዘንድ ሐዋርያዊ ጥሪ አቅርበዋል።

ብፁዓን ጳጳሳቱ ግንቦት ባወጡት ሐዋርያዊ መልዕክት ኑሯቸውን ለማሻሻል የሚሰደዱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች የሚያጋጥሟቸው ፈተና ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ መምጣቱን መመልከታቸውን ገልጸዋል።
በመግለጫው ስደተኞች የሀገራት ሸክሞች ሳይሆኑ ሰብዓዊ ክብርና ጥበቃ የሚገባቸው የሰው ልጆች መሆናቸውን አፅንዖት በመስጠት በካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ክርስቶስ መሰረት ያደጉ አገራት ደህንነትና ሥራ የሚፈልጉ ሰዎችን የመደገፍ የሞራል ግዴታ እንዳለባቸው ተገልጿል።
ብፁዓን ጳጳሳቱ በመግለጫቸው በዋነኝነት ለአደጋ ተጋላጭ የሆኑትን የፍልሰት መንገዶችን እና ከእነዚህ ጋር የተያያዙ አደጋዎችን ዘርዝረዋል። እነሱም መካከለኛው ምስራቅ (ሳውዲ አረቢያ፣ የመን፣ ሊባኖስ፣ የባህረ ሰላጤ አገሮች)፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን እና ሊቢያ ይገኙበታል። ስደተኞች በእነዚህ ሀገራት እስር፣ በደል፣ ከጦርነት ጋር የተያያዙ አደጋዎች ያጋጥሟቸዋል፣ እንዲሁም በሳውዲ አረቢያ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሞት አደጋ ላይ እንደሆኑ ተገልጿል። በደቡብ አፍሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የውጭ ዜጎችን ከጥላቻ የተነሳ በዓመፅ፣ እና በግድያ ክቡር ሕይወታቸው እየጠፋ ነው። እጅግ በጣም አደገኛ ከሆኑ የስደት መንገዶች አንዱ የሆነው በሱዳን-ሊቢያ-አውሮፓ መንገድም በርካታ ስደተኞች በበረሃ መሻገሪያዎች ላይ በሕገወጥ ዝውውር አማካይነት ለእስር፣ ለጉልበት ብዝበዛ፣ እና በሃይማኖታቸው ምክንያት ለአደገኛ ስደት እና ለሞት መጋለጣቸውን ገልጸዋል።
መግለጫው ይህ በየቦታው የሚሰተዋለው የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ስቃይ ከቁጥርም በላይ ውድ እና የተከበረ ህይወት ያላቸው እና ቤተሰቦቻቸው በእንባና በተስፋ የሸኟቸው ልጆች በመሆናቸው የሚያጋጥሟቸውን ብዝበዛ እና ህልፈተ ህይወት እንደሚያወግዙ ተገልጿል።
“ምህረት ፍትህን አያዳክምም። ምህረት ፍትህን ከፍ በማድረግ ተስፋ ለቆረጡ ተስፋን ይሰጣል” ያሉት ብፁዓን ጳጳሳት በአሁኑ ወቅት በተለይም በሳውዲ አረቢያ መንግስት በኢትዮጵያ ዜጎች ላይ ያሳላፈውን የሞት ፍርድ እንዲያነሱ እና ምሕረት ፍትህን ከማዳከም ይልቅ እንደሚያጠናክር በማስታወስ ርህራሄ እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሰዎችን ድህነትንና፣ የማህበራዊ፣ የኢኮኖሚያዊ እና የከባቢ ችግሮችን ጨምሮ የፍልሰትን ዋና መንስኤዎች ከሥር መሰረቱ እንዲፈቱ ጥረት በማድረግ ሂደት ውስጥ እንዲተባበሩ ጥሪዋን በማቅረብ የሰብዓዊነት እና የሥልጣኔ መለኪያ በዙሪያችን ያሉ ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች በምናሳሳየው እንክብካቤ መሆኑን ገልፃለች።
በመጨረሻም መግለጫው ከሞት፣ ከጥላቻ እና ተስፋ ከመቁረጥ በላይ ምህረት፣ ጥበብ እና ውይይት እንዲነግስ፤ እንዲሁም እነዚህ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የእግዚአብሔርን ምህረት እና እገዛ ያገኙ ዘንድ ብፁዓን ጳጳሳቱ መላው ምዕመናን እና በጎ ፍቃድ ያላቸው ሁሉ በጸሎት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርበዋል።

Ethiopian Catholic Church Pastoral Appeal for the Protection of Human Life and Dignity of Ethiopian Migrants“Blessed are...
21/05/2026

Ethiopian Catholic Church Pastoral Appeal for the Protection of Human Life and Dignity of Ethiopian Migrants

“Blessed are the merciful, for they shall receive mercy”. (Mt 5:7)

To all political leaders, religious leaders, human rights organizations, local advocates, the media, and to all people of goodwill.
Dear brothers and sisters in our shared humanity,
We, the Ethiopian Catholic Bishops, wish to raise a pressing concern of our time regarding Ethiopian migrants. Across our nation, millions of young men and women leave their homeland not out of a lack of love for their country, but out of a desperate search for honest employment and a livelihood that honors their inherent worth. Their motivations are noble and sacrificial: to uplift their lives, sustain their families, and ultimately contribute to the flourishing of their nation. Tragically, instead of finding the dignity they seek, our migrants find themselves ensnared by structural exploitation, fear, isolation, and acute vulnerability. No matter how desperate their circumstances, their human dignity remains sacred and can never be ignored or erased by a border, a legal status, or an economic system.
According to the Catechism of the Catholic Church, “The more prosperous nations are obliged, to the extent they are able, to welcome the foreigner in search of the security and the means of livelihood which he cannot find in his country of origin” (CCC 2241). This teaching reminds us that migrants are not to be treated as outsiders or burdens, but as brothers and sisters whose dignity must be respected and protected.
However, many migrants encounter serious challenges and suffer greatly throughout their migration journeys. We have observed the following key migration destinations and the associated difficulties faced by our brothers and sisters:
1) Some Middle Eastern Countries:
a. Saudi Arabia: There are many Ethiopian migrants residing in the Kingdom of Saudi Arabia. The Catholic Bishops’ Conference of Ethiopia expresses deep sorrow, profound concern, and urgent hope regarding reports that hundreds of Ethiopian citizens currently detained in the Kingdom are facing the possibility of ex*****on.
We earnestly hope and appeal that the authorities of Saudi Arabia will show compassion and mercy to all those affected, upholding the dignity of human life.
b. Yemen: Many Ethiopian migrants pass through the Red Sea, Djibouti, or the Gulf of Aden in an attempt to enter Yemen or proceed onward to Saudi Arabia. Yemen is often used as a transit route to other Gulf countries; however, many migrants suffer greatly along the way, facing violence, abuse, and inhumane treatment. Tragically, a significant number lose their lives due to the perilous nature of the journey and the harsh conditions they endure.
c. Lebanon; Many Ethiopian migrants in Lebanon face constant danger due to the ongoing conflict and instability in the country. As a result, a considerable number are seeking repatriation, longing to return safely to their homeland and reunite with their families.
d. The Gulf Countries: Many Ethiopian migrants in these countries find themselves in situations of constant danger and uncertainty due to escalating regional tensions and conflicts involving the United States, Israel, and Iran.
2) The Republic of South Africa is another destination for many Ethiopian migrants. A significant number face serious threats to their lives and property. Some are detained in transit countries along the way, while others who reach their destination continue to live in fear and uncertainty. We have received ongoing reports that some migrants have been victims of violence and have even lost their lives due to recurring xenophobic attacks in the country.
3) The Sudan - Libya - Europe Route: This route has long been one of the most frequently used paths by traffickers, and it has brought immense suffering to countless migrants. Many have perished while crossing the harsh and dangerous desert terrain under inhumane conditions. At present, the ongoing conflict in Sudan has made this journey even more perilous. Those who reach Libya often face imprisonment, extortion, forced labor, and severe abuse. Some have even suffered persecution and lost their lives because of their Christian faith. Migrants who attempt to cross the Mediterranean Sea in unsafe boats risk drowning; many tragically lose their lives, while only a few manage to reach the shores of Lampedusa. There, Pope Francis once laid a wreath of flowers in memory of those who died at sea, and Pope Leo XIV is also expected to visit the island, continuing the Church’s mission of solidarity, compassion, and advocacy for migrants.
These Ethiopian migrants are not statistics. They are sons and daughters of families who often send them abroad with tears, hope, sacrifice, and desperation. Too often, migrants fall into systems of exploitation, fear, abuse, isolation, and vulnerability. Many endure conditions difficult to imagine.
In the spirit of Christian charity and international fraternity, we raise a specific and urgent plea to the authorities of the Kingdom of Saudi Arabia to suspend any planned ex*****ons involving Ethiopian nationals and to consider clemency and mercy in these cases. Mercy does not weaken justice. Mercy elevates justice and gives hope where despair seeks to prevail.

This painful situation must also challenge the international community to confront the deeper causes driving irregular migration. Socio-economic hardships, environmental degradation, and many other factors continue to force millions of people onto dangerous migration routes across the world. A world that ignores these root causes cannot resolve the migration crisis. Indeed, the true measure of our humanity of civilization itself lies in how we treat the most vulnerable among us.

As Bishops of Ethiopia, we continue to pray fervently that dialogue, mercy, and wisdom may prevail over despair and death. We entrust these vulnerable Ethiopian migrants, their families, and all decision makers to the mercy and guidance of Almighty God.

The Catholic Bishops' Conference of Ethiopia.
Addis Abeba.
18/05/2026

Address

Wawel Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Catholic Bishops’ Conference of Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share