አንዲት ዕምነት ተዋህዶ

አንዲት ዕምነት ተዋህዶ "ወዳጆች ሆይ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት "ወዳጆች ሆይ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ"፡፡ ይሁ 1:3

ከቤተ ክርስቲያን ላይ የጥፋት እጃችሁን አንሱ፡፡
09/09/2019

ከቤተ ክርስቲያን ላይ የጥፋት እጃችሁን አንሱ፡፡

ሠላም ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፣ በያላችሁበት የአግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቸርነት ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡ ውዶች ሆይ ከዚህ በፊት በአን...
26/02/2019

ሠላም ውድ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፣ በያላችሁበት የአግዚአብሔር አብ ጸጋ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ፍቅር የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቸርነት ከእናንተ ጋር ይሁን፡፡
ውዶች ሆይ ከዚህ በፊት በአንዲት ዕምነት ተዋህዶ እና በ ወደ ምስራቅ ተመልከቱ ገጽ በለቀኩት የመግባቢያ መልዕክቴ ላይ በገለጽኩላችኁ መሠረት የዛሬዎቹን የምንፍቅና ትምህርቶች በግልጽ እንድንረዳ ይረዳን ዘንድ አባቶች ውሃን ከጥሩ ነገርን ከስሩ እንዲሉ ከመጀመሪያዎቹ የመናፍቃን ጽንስ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በግብር ልጆቻቸው ሲተላለፍ የመጣውን አስተምህሮ ለመመርመር ከጉባኤ ኒቂያ በፊት ከነበሩት ጥንተ መናፍቃን ዋና ዋናዎቹን በአጭር በአጭሩ ወደ እናንተ ይዤላችሁ ቀረብኩ፡፡
1. Gnosticism/ ግኖስቲክ
ግኖስቲክ ማለት የዕውቀት ሰው (አዋቂዎች) ማለት ሲሆን ቃሉን የወሰዱት ግኖሲስ ከሚለው የጽረዕ ቋንቋ ነው፡፡ ግኖስቲኮች ክርስትናን ከተቀበሉ በኋላ አዋቂዎች ነን በማለት በዘመናቸው የነበረውን የጥንቆላና የምሕታት እንዲሁም ደግሞ የፍልስፍናን ትምህርት ከክርስትና ትምህርት ጋር በማደባለቅ የሚያስተምሩ፣ ከክርስትናው ይልቅ እምነታቸውን በፍልስፍና ላይ ለመመስረት ትግል ያደርጉ የነበሩ ‹‹ፍልስፍና በራሱ ጎጂ አይደለም›› የሚል ከአህዛብ ዕምነት ወደ ክርስትናው ከተመለሱት ክርስቲያኖች የወረሱትን የሐሰት ትምህርት የሚያስተምሩ Gnosticism religion የሚባለውን ተቋም ለመፍጠር የቻሉ ናቸው፡፡ ግኖስቲኮች ምንታዌን (Dualism) የሚያስተምሩ ናቸው፡፡ ስለ አምለክ ሲያስተምሩ:- ሁለት አማልክቶች አሉ እነሱም ክፉ አምላክና ደጉ አምላክ ይላሉ ከዚህም ጋር አያይዘው ሥጋንና የሚታየውን ግዑዙን ነገር የፈጠረው ክፉ አምላክ ነው፣ ነፍስንና የማይታየውን ረቂቁን ነገር የፈጠረው ደግሞ ደጉ አምላክ ነው፣ ጭለማን ክፉ አምላክ ብርሃንን ደግሞ ደጉ አምላክ ፈጠረ የሚል ፍልስፍና የተቀላቀለው ትምህርት ነበራቸው፡፡ ከስነ ፍጥረቱም ጋር አያይዘው ፈጣሪና ፍጡር በምንም አይነት ሁኔታ እንደማይገናኙ በመግቦቱም አለምን እንደማይመግብ ሲናገሩ ይህንንም አምላክ the silence or the depth በማለት ይገልጹታል፡፡ እነዚህም የመጀመሪያዎቹ የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት፣ የአምላክን ሰው መሆን የካዱ ርዕሰ መናፍቃን ናቸው፡፡ ስለ ሰው ልጅ ተፈጥሮ በሚያስተምሩት ትምህርታቸው የሰውን ልጅ በሦስት ደረጃ ከፋፍለው ያስቀምጣሉ፡፡ እራሳቸውን መንፈሳዊ፣ ክርስቲያኖችን ነፍሳዊ ሲሉ አህዛብንና አይሁድን ደግሞ ስጋዊ በማለት ያስቀምጣሉ፡፡ የግኖስቲክን የክህደት ተምህርት ካስፋፉ መናፍቃን መካከል ሲሞን መሠርይ፣ ሜናንድሮስ፣ ሳቶሪኖስ፣ ኬሪንቶስ፣ ኒቆላዎስ፣ በስሊድስ፣ ቫላንቲኖስ እና መርቂያን ይገኙበታል፡፡ የእነዚህን የምንፍቅና ትምህርት ምን እንደነበር በየክፍል በየክፍሉ እያነሳን ወደፊት ለማየት እንሞክራለን፡፡

2. ኢቦኒስት
ወንድሞች በአንጾኪያ ክርስቲያን የሚለው ስያሜ ከተሰጣቸው በኋላ ሐዋ 11፡26 በዚህ ጊዜ የተነሱት መናፍቃን ደግሞ ቢጽ ሐሳዊያን (ሐሰተኛ ወንድሞች) በመባል ይጠሩ ነበር፡፡ በትምህርታቸው ክርስቶስ በድንግልና መወለዱን ቢቀበሉም አምለክ ግን አይደለም፣ ክርስቶስ እሩቅ በእሲ ስለሆነ ማርያምም ወላዲተ አምላክ ሳትሆን ወላዲተ ሰብእ ናት በማለት ይናገራሉ፡፡ እነዚህ ኢቦኒስቶች ከአይሁድ ክርስትናን ከተቀበሉና ካመኑ በኋላም የመጡበትን የአይሁድን እምነት ይከተሉ ስለነበር የአይሁድን ሀይማኖት ያዙ ጥምቀት ያለ ግዝረት፣ ክርስቶስ ያለ ሙሴ፣ ወንጌል ያለ ኦሪት አይራባችሁም እያሉ በሚያስተምሩት የሐሰት ትምህርት የክርስቶስን ደቀ መዛሙርት ሲያስቸግሩ የኖሩ ዳሩ ግን በ50 ዓ.ም በመጀመሪያ ጊዜ በተደረገው የሐዋርያት ሲኖዶስ ጉባኤ ተወግዘው እንዲለዩ ተደርገዋል፡፡ ይህ ትምህርታቸው ዛሬ ላይ ላሉት ለብዙ የዕምነት ድርጅቶች በተለይም ለአረብ ሰዎች ዕምነት መሠረት የሆነ ቢሆኒም ኢቦኒሲዝም ግን በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጠፍቷል፡፡

3. Docetism/ ዶሴቲሰት
እነዚህ ቢጽ ሐሳዊያን ደግሞ ልክ እንደ ዛሬዎቹ መናፍቃን ህሙማንን እንፈውሳለን፣ ለምጻምን ከለምጹ እናነጻለን እያሉ በምትሀት እና በጥንቆላ መንፈስ የሚሰሩ፣ ነገር ግን ክርስቶስ በሥጋ አልመጣም፣ አልተገለጠም በማለት የውሸት ትምህርታቸውን የሚያሰራጩ እራሳቸውን ነቢያት እያሉ የሚጠሩ ናቸው፡፡ ለእነዚህ መናፍቃን ትምህርትም

በተለያዩ ክፍለ አለማት እና ክፍለ ሀገራት ዞርኩ የአለምን አነዋወር (ህልውና) ተመለከትኩ ወደ ተለያዩ የዕምነት ድርጅቶችና ተቋማት ገባሁ የማምለኪያ አጸዶቻቸውንም ቃኘሁ ስርዓተ አምልኮአቸውን...
21/02/2019

በተለያዩ ክፍለ አለማት እና ክፍለ ሀገራት ዞርኩ የአለምን አነዋወር (ህልውና) ተመለከትኩ ወደ ተለያዩ የዕምነት ድርጅቶችና ተቋማት ገባሁ የማምለኪያ አጸዶቻቸውንም ቃኘሁ ስርዓተ አምልኮአቸውንና የዕምነት መመሪያ ዶክትሪናቸውን ፈተሸኩ መረመርኩ፣ የምርምር ውጤቱንም በመጽሐፍ ቅዱስ ሚዛን ላይ አኖርኩ፣ በጣም ፈራሁ፡፡ እጅግ በጣም ፈራሁ!! ግን ደግሞ ኢትዮጵያዊነቴን ይልቁንም ሀይማኖቴን ከበፊቱ ይልቅ ወደድኩት፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያ የሀሰተኘ ነቢያቶች እንደ አሸን መፍላት (መብዛት) እጅግ ቢያስፈራኝም ሀይማኖቴን ግን እጅግ በጣም ወደድኳት፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ምዕመን ከእለት እለት በሐሰተኛ ነቢያቶች እንደ ጎርፍ መፍሰስ ቢያስፈራኝም ሀይማኖቴን ግን በጣም ወደድኩት፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ መምህራንና ዘማሪያን ወደ ፕሮቴስታንቱ አደራሽ መፍለስ እጅግ በጣም ቢያስፈራኝም ሐይማኖቴን ደግሞ እጅግ በጣም ወደድኳት፡፡ ‹‹ለምን በሚያስፈሩኝ ጉዳዮች ሀገሬንና ሐይማኖቴን እንደወደድኩ ከሰፊ ማብራሪያ ጋር ወደ እናንተ መጣለሁ እና በትዕግስት ጠብቁኝ፡፡››

አንድ የፕሮቴስታንቱ እምነት መመኪያ የነበረ (አሁን ፕሮቴስታንት ያልሆነ) በነገረ መለኮት ዕውቀት የላቀ ሰባኪ ፓስተር ዶ/ር ወዳጄነህ ፡፡ ‹‹እንዳያስተውሉ መጽሐፍ ቅዱስን ከእጆቻቸው ማን ወሰደባቸው?›› በማለት የተናገረው ንግግር ትዝ ብሎኝ በጣም ተገረምኩ::

ውድ ይህ መልዕክት የሚደርሳች እናት፣ አባት፣ እህት እና ወንድም ወገኖች በጠቅላላ ያለ ክፋት በቅንነት፣ ያለ ሀሰት በእውነት፣ ያለ ትዕቢት በትህትና፣ ያለ ጥላቻ በፍቅር ስሙኝ፡፡ ከክፉ አሰራር ተጠበቁ፣ እራሳችሁን በእግዚአብሔር ቃል አንጹ፡፡ በአንድ ወቅት ‹‹ማሕበረ ቅዱሳን›› ለተሐድሶ ፕሮቴስታንት ጥያቄዎች በሰጡት የቪሲዲ መግቢያ ላይ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀውስጦስ እያለቀሱ ‹‹ልጆቼ! እራሳችሁን እንዳታሰርቁ…. አደራ እራሳችሁን ጠብቁ›› በማለት አባታዊ ምክራቸውን እንደ ለገሱ አስታውሳለሁ፡፡ ዛሬ ላይ ክፉ መናፍስትን በሰዎች ላይ የሚረጩ ብዙ የሐሰተኛው ክርስቶስ አገልጋዮች በአለማችን ብሎም በቅዱሳን አጽም ታጥራ በምትጠበቅ፣ በዕምነት ሠረገላ ወደ አምለካ የምትገሰግሰዋን፣ እጆቿን ወደ አምላኳ ዘርግታ የጌታን መምጣት በተስፋ የምትጠባበቀዋን ኢትዮጵያን ሰይቀር የእምነት ጋሻዋን ከእጇ ለማስጣል በክፉ መናፍስ ሀይል የሚሰሩ ሀሰተኛ ነቢያቶች ጥቂት የሚባሉ አይደሉም፡፡ በመሆኑም የእነዚህን የሀሰተኛ ነቢያቶች ትምህርት ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር በመመርመር፣ ምግባራቸውንና የእምነት ፊሬዎቻቸውን በማጥናት ሰፊ ዝግጅት አድርጌ በቅደም ተከተል ከጥንት እስካሁን ድረስ ያለውን የዘንዶውን አሰራር ለናንተ ላቀርብ ወደድኩ፡፡ እናም ይህ ትምህርት በሳምንት ሁለት ቀን ማለትም ዘውትር ማግሰኞና ቅዳሜ በ‹‹አንዲት ዕምነት ተዋሕዶ›› እና ‹‹ወደ ምስራቅ ተመልከቱ›› በተሰኙ ሁለት ገጾች ላይ የሚተላለፍ ሲሆን ሁላችሁም እንድተከታተሉ ከወዲሁ ጋበዝኳችኁ፡፡ (ለወደፊትም እንደ አመላከ ቅዱሳን መልካም ፍቃድ ይህንን መርሃ ግብር በድምጽና በምስል በመታገዝ ዘጋቢ ፊልሞችን፣ ትምህርቶችንና መዝሙሮችን በሳባ ትዮብ እናቀርብላችኋለን ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡)

ማሳሰቢያ
ውድ የፈጣሪ ፍጡራን በዚህ መንፈሳዊ ገጽ ላይ ማንም በአስተያየት መስጫ ሳጥን የስድብ ቃል እንዳይናገር፡፡ ይልቁንም ብዙዎችከጥፋት ወደ እውነተኛይቱ ቅድስት ቤ/ክ ይመለሱ ዘንድ ገንቢ ሀሳባችሁን ብቻ አስቀምጡ፡፡

ፍቅረማርያም ፍቅረሥላሴ (ሃብታሙ ነጋሽ) ነኝ!!
‹‹ሼር በማድረግ ለሌሎች ያከፍሉ፡፡

የ"ወደ ምስራቅ ተመልከቱ" ሊንክ
https://m.facebook.com/ወደ-ምስራቅ-ተመልከቱ-149228232353692/?ref=opera_speed_dial

https://www.youtube.com/watch?v=wIBPE9Kpajc
22/12/2018

https://www.youtube.com/watch?v=wIBPE9Kpajc

ሁሉም ሰው ሊሰማው የሚገባ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ተዘጋጅቶ የቀረበ ድንቅና አዲስ የምስጋና መዝሙር በዘማሪት ቃልኪዳን ምስጋናው፡፡

17/12/2018
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡
17/12/2018

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡

ይሄን ፎቶ ፌስ ቡክ ላይ ባየሁ ጊዜ ውስጤን የተሰማኝ ደስታ ጥልቅ ነው፡፡እራስን ከብሔር እስራት መፍታት ማለት የመጣውን የሰው ዘር በሙሉ በፍቅር፣ በምህረትና በይቅርታ ተቀብሎ በእኩልነት ለማ...
10/09/2018

ይሄን ፎቶ ፌስ ቡክ ላይ ባየሁ ጊዜ ውስጤን የተሰማኝ ደስታ ጥልቅ ነው፡፡
እራስን ከብሔር እስራት መፍታት ማለት የመጣውን የሰው ዘር በሙሉ በፍቅር፣ በምህረትና በይቅርታ ተቀብሎ በእኩልነት ለማስተናገድ ልብን ንፁህ አዳራሽ አድርጎ ማቅረብ ነው፡፡
"የ58 ሰፈር ልጆች እረጅም እድሜ ለናንተ"
"በፊታችን የተጋረደው ድንግዝግዙ (ብሔር) ሲፈርስ ለይቶ ማየት የለመዱ ባለጌ ዓይኖች ይጠፋሉ፡፡ አጥርተን ፊትለፊት እናያለን፡፡ የዚያን ጊዜ ፍትህ የጎደለው "ሰው" ይሁን እንጂ ኬት መጣህ፣ ትውልድህ፣ የዘር አአጥንትህ ሳንል ጥብቅና የምንቆምለት እኛ እንሆናለን፡፡
ሀብታሙ ነጋሽ

03/09/2018

ሰው፡- ሰው ሆኖ የተፈጠረው የሰውን ስራ እንዲሰራ ነው፡፡ ሰይጣን ሰይጣን የሆነው የሰይጣንን ስራ ሲሰራ ነው፡፡ የሚገርመው ሰይጣን አንድም ቀን በስህተት የሰውን ስራ ሰርቶ አያውቅም፡፡ የሰው ልጅ ግን የሰይጣንን ስራ ያለ እረፍት ይሰራል፡፡ አስደናቂው ነገር የሰው ልጅ ሰው ሆኖ መኖር ሳይችል ቢቀር ጊዜ አምላክ ሰውን ሰው ሊያደርግ ሰው ሆኖ መጣ፡፡ በመሆኑም በእኔ እይታ ሰው ሆኖ መኖር አለመቻል የአምላክን ሰው መሆን በህይወታችን ዋጋ የለሽ የማድረግ ያህል ራስን ርካሽ ፍጥረት ማድረግ ነው ፡፡
ሀብታሙ ነጋሽ፡፡

Address

Yotor Zetewahedo ዮቶር ዘተዋሕዶ
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አንዲት ዕምነት ተዋህዶ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share